Thursday, October 2, 2025

የፋኖ ፖለቲካል ሃርለቶች ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 10/3/25

 

የፋኖ ፖለቲካል ሃርለቶች

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

10/3/25

ባለፈው ሰሞን ፋኖ ተብየው ማፈርያ ታጣቂ የወያነ ዘረኛ መፈከር ተበድሮ «ወላጆቻችን ተማርከዋል እኛም ተደግመናል» በሉ እያለ ከሙርከኛ አያያዝ ሕግ ውጭ ፣ የቆሰለና ጣዕር ላይ ያለን ሙርከኛ ሲያስጨንቅ  ስምተን መገረማችን ሳናቆም እንደጋና ሰሞኑን “ወሎንና ጎጃምን አልፋችሁ ትግራይ እና ኤርትራ ያሉት “የፖለቲካ ውሹማዎቻችንን” ትነኩዋቸውና እነሱን ከመንካታችሁ በፊት እኛ “እንደ ነብር እንከመርባችኋለሁ” የሚሉ ፖለቲካል ሃርለቶች ለኛ “ለኢትዮጵያዊያኒስቶች” አደጋ ናቸው!

በግሌ ተስፋ ጥየበት የነበረው የፋኖ የትጥቅ ትግል ገና ጥይት ሳይቶኩሱ ወደ የሀገር መሪነት ኩፈሳ የሚቃጣቸው በአዳዲስ የጫካ ነገሥታቶች ግቡን ስቶ ቃናውን አጎምዝዘውታልና ዲያስፖራዎች የፋኖ “ነቀዝ” መሪዎችን ከነ ውሸታቸው ፤ወንጀላቸውና ባንዳዊ ንግግራቸው ጭምር ማድነቅና መደገፍ ከቀጠላችሁ ፋኖዎች ከተማዎችንና አስፋልቶችን መቆጣጥር ከቻሉም  አዲሰ አበባ ከገቡም፤ ውሸታሞች፤ ወንጀለኞችና ባንዳዎች ትግሉን እሰከመሩት ድረስ የተመኙትን የሥልጣን ስግብግብነት ያገኛሉ የምትሉ ተከታዮቻቸው ብዙም ተስፋ ባታደርጉ እመክራለሁ ኣያልኩ ይልቁኑ መሪዎቹ በሰራዊትና በገልለተኛ ደጋፊዎች የተውጣጡ አጣሪ ኮሚቴዎች የሰሩት ወንጀል እና ጥንካርያቸው እየተጣራ ነቀዞችን የሚተኩ ሌሎች እንዲመሩት ቢደረግ መለካም ነው እያልኩ ወደ ዋናው-ጉዳያችን-እንግባ።

በዙዎቻችሁ እንደምታውቁት፤ አሁን የታጠቁት የፋኖ መሪዎችም ሆኑ የነዚህ “ክሪሚናልስቶች” አጨበጫቢ አጃቢዎቻቸው አሁን አለን፤አለን እንድሚሉት ሳይሆን ወላጆቻቸው ሲጠቁ ጀሮ ዳባ ብለው ጣፋጭ ኑሮ ሲኖሩ የነበሩ አንዳንዱም ከጸረ አምሐራው ከግንቦት 7 ጋር ሆነው በከፍተኛ አመራርነት፤ ካድሬነት እና ታጣቂዎች ሆነው የኢሳያስና የአንዳርጋቸው ጽጌ ፖለቲካ ሲያገለግሉ የነበሩ አማራዎች ፤ እኛ በቁጥር በጣም ጥቂቶች የአምሐራን ሕዝብ ጥቃት ለማስቆም ስንጮህ እኛን ከማገዝ ይልቅ ሲሰድቡን የነበሩ ሁሉ ፋኖ የሚባል ታጣቂ ከመከሰቱ በፊት የነበሩበት መጫወጫ ሜዳቸው የት እንደነበር ማሕደራቸውን ማየት በቂ ነው።

ዛሬ የምንመለከተው ስለ የጎጃም ፋኖ አስረስ ማረ ፤ በሚስቱ በኩል የተመለመለው “የሻዕቢያው ፋኖ” ተፈራ ማሞ እና “ካፒተን ማስረሻ ሰጤ” የተባለው ባንዳዎችን ባንዳ በማለቱ ያልወደደለት የፖለቲካ Neophyte የሆነው የሸዋ ፋኖ ተዋጊ መሪ መከታው ማሞ እና የመሳሰሉ የፋኖ መሪዎች እየተጓዙበት ያለው “ስትራተጂ የሳተ” ጨዋታቸውን እንነጋገራለን።

መጀመሪያ እሰኪ Political Prostitution “የፖለቲካ ሽርሙጥና” ከመመልከታችን በፊት የፋኖ መሪዎች ነጸብራቅ የሆነው በጎጥ እየተዘላለፈ ሰላለው ሰለ የዲያስፖራው አማራ ማሕበረሰብ እንመልክት። እነዚህ ኮሚኒቲዎች የፖለቲካ ሽርሙጥናም ሆነ ስድነት፤ ውሸትና ባንዳነት በፋኖ ውስጥ የለም ባዮች ናቸው። ሰለ ነሱ ስትተችም ይንጨረጨራሉ፤ ያብዳሉ፤ስብዕናህንም ማሕደርሕንም ይጋፋሉ።

እውነታውን እያዩ በመሸሽ ላይ ያሉት እነዚህ “በኮግኒቲቭ ዲሶናንስ እሾሕ” የተሸነክሩት እነዚ እነ ማን እንደሆኑ ልንገራችሁ።

ባለፉት አመታት የብርሃኑና የአንዳርጋቸው ግንቦት 7 ባንዳነትና ዘረኛነት እያሽሞነሞኑ «ፓቶክ» ውስጥ ገብተው ጀሮአችንን ሲያደነቁሩን የነበሩት ግንቦት 7 ምን እንደነበር ስንጮህ አንሰማም ብለውን ወያነ ሲወድቅ ፤ የግንቦት 7 ማንነት ተገለጠላቸውና በቆምንበት ፊት ቆመው በአጫፋሪነታቸው ኮሸሽ ብለው ያፈሩ ፡

 ከዚያም ወደ አብይ አሕመድ አጫፋሪነት ገቡና እንደገና ዛሬ በፋኖ ደጋፊነት ግልብጥ ብለው አወራጃ ባወራጃ እየተሰዳደቡ በለመዱበት ባሕሪያቸው የሚያመልኩዋቸው የፋኖ መሪዎችን ላለማጋለጥ በፋኖ ውስጥ ዝርፍያ፤ ርሸና (ግድያ/ቶርቸር/ጠለፋ) ፤ እርሰ በርስ መገዳደል፤ ስድነትና “የፖለቲካ ሽርሙጥና” እየተፈጸመ እያዩ “የነፃነት መላዕክቶች የሚመሩት ድርጅት” ነው ብለው ፋኖ የፈለገው ጥፋትና ወንጀል ቢያደርግም መዳኚያችን ነው የሚሉ የዲያስፖራ አማኞቻቸው” (nationalist cult) አገር ውስጥ ላለው የትጥቅ ትግል ተጨማሪ አስናካዮች ናቸው

 ለመሆኑ “የፖለቲካ ዝሙትነት” ምንድ ነው?

የፖለቲካ ዝሙትነት ማለት፤ በኛ ሀገር እንመልከት፡ የባሕር በሮቻችንን ለዘጋብን ፤ እንድንዘጋም ፈርሞ ከሰጠ አካል፤ ሀገርን፤ ባሕልን ለማኮላሸት በሚደረግ አፍራሽ ትወና ውስጥ እዚህም እዛም አለሁ እያለ ዥዋዥዌ እየተጫወተ “ከተገነጠለ እና ለመገንጠል ለሚጥሩ ቡድኖች” ጋሻ (Shield) ለመሆን «የሀገር ጦር ሰራዊት እና መሪዎች መለየት ያቃተው ፋኖ» ወያነ እና ሻዕቢያን ትተናኮል “የእኔ ሬሳ ተሸጋግረህ እንጂ እነሱን መንካት አትችልም” የሚል ይፋ አዋጅ የሚያውጅ ልክ እንደ (የሻዕቢያው ፋኖ ‘ተፈራ ማሞ’) የጠላት ቀላጤ ሆኖ የሚያገልግል የፖለቲካ ድርጅት/ግለሰብ/ብድን/ማለት-ነው “የፖለቲካ ዝሙትነት” ማለት።

እዚህ ላይ እያወራን ያለነው ሰለ ወንድና ሴት ወሲብ አይደለም። እያወራን ያለነው፤ “የብሔር ብሔረሰቦች” አምላኪዎች ባጭሩ “ተገንጣዮች እና ግዛት አስመላሾች Secessionists and Irredentists የወጠኑትን የመገንጠልና ግዛት የማስመለስ ጥረታቸው በጦርነት ሞክረው አልሆን ሲላቸው አልፈርስ ብሎ የቆመን ግድግዳ (ሃገር) የሚያነቃንቁለትን ሰለ «የፖለቲካ ሸርምጦች (Political Harlots)» ተዋናይነትን ነው።

የፋኖ ጎጠኛ ትርኪምርኪዎች እያደረጉት ያሉት «የተለመደው የፖለቲካ ዝሙት ነው»። መልማዮቻቸው እስራተጂ አላቸው። የአቀራረቡ ስልት ደጎሞ “የብሔር ብሔረሰቦች ጥምረት” (Interethnic coalition) የጋራ ጠላት በጋራ የማጥቃት “ስም/ሽፋን” ተጠግቶ የፖለቲካ ሸርሙጦችን (Political Harlots)» ይቀጥራል። ይህ ስልት በ60ዎቹ በተማሪዎች እንቅስቃሴ የታየ ነው። ኤርትራኖች የተጫወቱት እንቅስቃሴ ስንመለከት ኤርትራኖች «የአዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትግራይ ተማሪዎች “የፖለቲካ ሃርለቶችን” እንዲሁም ከአማራ ተማሪዎች ዋለልኝ መኮነንን {ልክ እንደ የዛሬዎቹ የጎጃም ፋኖው አስረስ ማረ እና የወሎው “ጀነራል” (ተብየው) ተፋራ ማሞ ፤ ከዚያም ትግራይ ውስጥ የዳበረው “የፖለቲካ ሃርለቶች ስብስብ” 17 አመት ሙሉ ተጉዞ  ኤርትራን ለማስገንጠል ትግራይ ውስጥ ያየነው “የፖለቲካ ሃርለቶች ባሕሪ” ማለት ነው “የፖለቲካ ዝሙትነት” የምንለው ።

ወሎንና ጎጃምን አልፋችሁ ትግራይ እና ኤርትራ ያሉት “የፖለቲካ ውሹማዎቻችንን” ትነኩዋቸውና “እከመርባችኋለሁ” የሚሉ የፋኖ  “ፖለቲካል ሃርለቶች” ለሽፋን የሚጠቀሙበት ቃል  የፖለቲካ ውሽሞቻቸውን “ሻዕቢያ እና ወያነ” የሚለውን ስማቸውን ላለምጥቀስ ሲሉ የሚጠቀሱት የማምለጫ ቃል ሕዝብ የሚል ቃል ነው። «የትግራይ ሕዝብና የኤርትራ ሕዝብ» በሚል ሽፋን ነው

ሕዝብ ምን ማለት ነው?

 የትግራይ ሕዝብ መስሎኝ በየሚዲያው እያስተጋባ “አማራ የወሰደበንን የራያና የወልቃይት ርስታችንን ፈቅዶ ይመልስልን ካልሆነ አስገደደን በጉልበት እናስመልሰዋለን» እያለ ያለው “የትግራይ ሕዝብ” መስሎኝ?!!። (ኤርትራ ሕዝብ የሚባለውም እንደዛው ነው፡ ባሕራችን ትነኩና የሚከመሩባችሁ የኛ “ሃርለቶች” አዘጋጀተንላችኋል ወዮላችሁ የሚሉን እኮ ናቸው፡  አይደሉም እንዴ??)፤ ሰለዚህ ተፈራ ማሞ የአማራን ሕዝብ ወጣት ትውልድ እንዲሞትለት እያደረገ ያለው “ፖለቲካዊ ዘሙትነት”  ሃገርና “ኤርትራ” የተባለ ባዕድ ነኝ ብሎ የተገነጠለ ሕዝብን ነው የአማራ-ፋኖ ወጣት መስዋዕት እንዲሆን እያዘጋጀው ያለው።

 (ለሱዳንም፤ ለግብጽም ያንን ያደርጋል)። ትግሬዎች እኮ ኢትዮጵያ ሱዳን ብትወር ከሱዳን ጦር ጋር እንሰለፋለን ብለው ማስታወቂያ ለጥፈው ሰልፍ አድርገዋል። ወይ ዘንድሮ!!

ሕዝብም ይሁን ወያነና ሻዕቢያ አንድም ሁለትም ናቸውና “ፖልቲካዊ ዘሙትነታችሁን አቁም።

ሌላው ሽፋን “የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው» የሚባለውን እንመልከት።

“የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው» የሚል የፖለቲካ ዝሙተኞች የሚልክሰከሱብት ስልት ነው።ህ የከሰረ ለብዙ አመታት ሞግተነው በተግባር ከስሮ  ያየነው “የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው፡ በሚል የፖለቲካ ሽርሙጥና ፤ አክራሪ ውሃቢስቶቹን ፤ እሰላማዊ አባጃራዎችን ፤ እሰላማዊ ጃዋሮችን፤ ማሞካሸት የሻዕቢያ ፤ የነ ብርሃኑ ነጋ እና ተገንጣይ ኦሮሞዎችን (ኦንጎችን፤ ከማል ጎልቹዎቹን፤ ሌንጮ ባቲዎችን ፤ ሌንጮ ለታዎችን፤ ፤ የኦጋዲን ኦብነጎችን እንዲሁም “አማራ ተወካይ እንዳይኖረው የጣረ “ቪዥን ኢትዮጵያየተባለ አማራን ያገለለ ግንቦት 7 (ኢሳት) የሚመራው የኦነግና የሻዕቢያ አድናቂዎች ስብስብ እንዲሁም፤ ስየ አብርሃዎችን ወዘተ፣ ወዘተ-በማሞካሸት “የፖለቲካ ዝሙት” ሲፈጽሙ “የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው» በሚል ነበር።

ወዳጅነትና የየጋራ ጋጋታ ፈጥረው ሲያደንቁሩን ፤ እኔ ራሴ በግባር ቀደም  እና ጥቂት አገር ወዳዶች ታግለን የጣልነው ስልት ነው (ይህ ጉራ አይደለም-የዛው ጊዜ ጽሁፎች ቪድዮዎችን መፈተሽ ነው) ።  በእዛን ወቀት “የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው»  በሚለው ጋጋታ እኛን እየሰደበ የነበረ ደጋፊና አዳማቂ  ዛሬ ስሜቱን መለጎም አቅቶት ፤ የፋኖ ፖለቲካ ዝሙተኞችን በመደገፍ የሚከንፈው በዙውን የዲያስፖራው አምሐራ ማሕበርሰየዛኑ ጊዜ የፖቲካ ዝሙት ፈጻሚ ቡደኖች አጨባጫቢ ነበር።

 አሁንም እየተደገመ ያለው ያው ነው። የገረመኝ ነገር፤ በጎጃም እና በጎንደር ውስጥ ፋኖ ለፋኖ በተደጋጋሚ እይተታኮሱ እርሰ በርስ ሲጋደሉ እያዩ ከወያነ እና ከሻዕቢያ ጋር ተጠርንፈው  ለነዚህ ታሪካዊ ጸረ አማራ ጠላቶች ለመሞት ዝግጁ መሆናቸው አንዳንድ የፋኖ መሪዎቹ ሲገልጹ፤ እነዚህ ዲያስፖራዎች ደግሞ “የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው» ዘላቂ ሰላም ያመጣል ብሎ የፖቲካ ዝሙት ፈጻሚ ፋኖዎችን “ምንም ወንጀል ይፈጽሙ ፤ ለጀሮ የማይጥም ምንም ነውር ይናገሩ” ያለምንም ማመንታት ፤ ያደጉበትና የለመዱበት ጭፍን ድጋፍ ሲሰጡ ማየት የሚገርም ነው። ድመት መንኩሳ አመልዋን አትረሳ!!!!

አሁን ወደ ማስረሻ ሰጤ እና መከታው ማሞ ንግግሮች እናምራ፡


ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ጎጃም ውስጥ ካሉት ፋኖዎች ውስጥ ራሱን የቻለ የፋኖ ድርጅት መሪ እና  እስክድር ነጋ ከሚመራው “የሸዋ ፋኖ” የ አ. ፋ. ሕ. ድ.  አመራር አባል ነው። ትናንት ያደመጠኩት በካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በወሎ እና በጎጃም ፋኖ “የፖለቲካ ሃርልቶች” የፈጸሙት “ፖለቲካዊ ዝሙትን” አስመልክቶ የሰማውና (ማስረጃ አለኝ) ያለው ለኛ “ለኢዮጵያኒስቶች” ያስተላለፈለንን ካንድ ሀገር ወዳድ ኢትዮጰያዊ የሚጠበቅ አርበኛዊ መልእክት  የሰማሁት በደስታና አከብሮት ነበር።፡ 

በተቃራኒ የሰጠው የ “አ. ፋ. ሕ. ድ.” ምከትል እና የ “አ. ፋ. ሕ. ድ.” ሰራዊት አዝማች የሚባለው “የፖለቲካ Neophyte” (የፖለቲካ ጀማሪ) የሆነው መከታው ማሞ የሚባለው ለማስረሻ የሰጠው መልስ አሳፋሪ ነበር።

ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ  ያንን ካስተላለፈ ወዲህ  ወደ አብይ ሊገባ ነው እያሉ ሲዝምቱበት ነበር። ቢገባም አባባሉ የሚሻር መልዕክት አይደለም።

ያም ሆኖ ማስረሻ ስለ “የፖለቲካ ሀርለቶቹ” የባንዳነታቸው እንቅስቃሴ በማስረጃና መረጃ አቀርባለሁ ሰላለ ያንን በጉጉት እንጠብቃለ

ካፒቴን ማስረሻ እንጀምር።


ሩ እንዲህ ይላል።


« ከተማ ውስጥ ከወያዎች ጋር በከተሞች ወጣ ገባ እያሉ በባንኮች በር ቆሞ ፎቶ መነሳትን እንደ ድ የሚቆጥሩ ፤ ከ2018 ጀምሮ የአማራን ሕዝብ ትግል ፍሬ እንዳያፈራ እና ተዳፍኖ እንዲቀር  በታሪካዊ ጠላቶቻችን እጅ ተጠልፎ መውደቁንና በዚያው የሚንቀሳቀስ ሃይል መኖሩን በተወሰነ መልኩ በግልጽ አይተናል። ከወያኔዎች ጋር ተሰለፎ የአማራን ሕዝብ ጥያቄ እመልሳለሁ የሚል ፤ የአማራን ሕዝብ ጥያቄ እንዳይመለስ ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር የቆመን አካል በጠላትነት ፈርጀን እኩል የምንታገለው መሆኑን በዚህ አጣሚ ለምግለጽ እፈለጋለሁ።......

ይልና

«እኛ ኢትዮጵያን እንወዳለን፤ እንደ ሀገር ኢትጵያ እንድትቀጥል እንፈልጋለን፤ ነገር ግን የወያነ ዓላማ አንግቦ ኢትዮጰያ እንድትበታተንና  ደካማ ሀገር እንድትሆን የሚፈልግ አውዳሚ ስብስብ በሕዝብ ትግል ወደ አንድ አካባቢ እንዲመሽግ እንደተደረገ የሚታወቀ ቢሆንም ....የዚህ  አጋርና የዚህ ፈረስ ሆኖ መምጣት ክሕደት በመሆኑ ማቆም እንዳለባቸው “በፋኖ ስም የሚንቀሳቀስ ባርበኛነት ስም የሚንቀሳቀስ  ማንኛውም አካል፤ ሊያቆም እንደሚገባ ለመግለጽ እፈልጋለሁ።

ዝርዝር ሁኔታዎች በማስርጃና በመረጃ ለሕዝባችን የምናሳውቅ መሆኑን  እየገለጽኩ ስለዚህ በግራም በቀኝም ያሉ የፋኖ አመራሮችና የፋኖ አባላት የማንም ዕርዳታ ሳንፈልግ “በራሳችን መቆም  እንችላለን”። «በበሰበሰ ቁምባላ» የሚሸወድ  የአማራ ወጣት የሚታለል እንደሌለ መታቅ አለበት። ስለዚህ በራስችን እንቁም.......በራሳችን እንደንቆም እንጂ ከታሪካዊ ጠላቶቻቸን ጋር ያውም እንደ ሕዝብም እንደ ሃገርም በኢትዮጵያ ላይ የሚቆምር አካል ጋር መቆም አሰፋላጊ አለመሆኑ አውቆ ወደ ድርጅታችን እንዲመጡ ጥሪ ማድረግ እፈልጋልሁ። አመሰግናለሁ። (ማሰርሻ ሰጤ) (የጎጃም ፋኖ ጠ/ግዛት ዕዝ አዛዥና የአፍሕድ የውጭ ጉዳይ ሓላፊ)»። ይላል።

የመከታው ማሞ ያለመብሰል በልሹነትና ለባንዳዎቹ ድጋፍ ሰጪ ንግግሩ እንዲህ ይላል፦

«ምናልባት አርበኛ ካፕቴን ማስረሻ  በተለቀቀው (ንግግር) ሙሉ በሙሉ አላዳመጥኩትም ፤ሙሉ በሙሉ ባልሰማውም ዞሮ ዞሮ  በደረሰኝ መረጃ እንደ አመራር ፤ እንደ አፋሕድ ሥራ አስፈጻሚም የሚወክል እንደ ድረጅትም ምንም ዕውቅና የለውም። እንደ ድርጅትም እንደ ግልም ምንም የምናውቀው የለም። «(መልዕክቱም) አፍሕድን የሚወክል አደለም» ብየ ነው የምገልጸው። አንዳን ሰዎች ባስረዱኝ እንጂ በተሰጠው መልዕክት ላይ የአፍሕድ አቋም እንዳሆነ ለመግለጽ እወዳለ»። የላል መከታው ማሞ።

አንደኛ ፤ ...ሙሉ በሙሉ አላዳመጥኩት ፤ሙሉ በሙሉ ባልሰማውም” ይላል; በጆሮው ባላዳጠውም በክፊል አድምጫለሁ ይላል፤ ያቺ  4 ደቂቃ የማትሞላ ንግግር ግማን አድመጦ ግማሹ ላይ ሲደርስ ለማድመጥ የድረገጽ ሞገድ ችግር  እንዴት ሊገጥመው ቻለ? ለማድመጥ ሙሉውን እንዳደመጠው አልጠራጠርም፡ ቢሆንም ባላዳመጠውና በሁለተኛ ስማ በለው መረጃ (በሰከንድ-ፓርቲ) መረጃ ተንተርሶ መስ መስጠቱ ምን ይባላል? ምንስ አስቸኮለው? በካፒቴን ማስረሻ የተላለፈው መልዕክት ግለጽ እና አርበኛዊ  መልዕክት ነው። በሚገርም ነገር መልዕከቱ መከታ ማሞና ድረጀቱ በመገለጫ ሳይቀር በተደጋጋሚ ሲያስተላለፈው የነበረ መልዕክት ነው፡ (ማስረጃውም በዚህ ፌስ ቡኬ ባለፈው ሰሞን የተለጠፈው አበበ ያነበበው የድርጀቱ መግለጫ እንደገና አድምጡት) ምንም ልዩነት የለውም« ከወያኔዎች ጋር እየተላላሱ ያሉ የፋኖ አመራሮች አሉ፤ በራሳችን እንቁም.......በራሳችን እንድንቆም እንጂ ከታሪካዊ ጠላቶቻቸን ጋር ያውም እንደ ሕዝብም እንደ ሃገርም በኢትዮጵያ ላይ የሚቆምር አካ ጋር መቆም አይገባም።ከ2018 ጀምሮ የአማራ ሕዝብ ትግል ፍሬ እንዳያፈራ እና ተዳፍኖ እንዲቀር  የሚጠሩ የፋኖ አካላቶች አሉ» የሚለው  «የተላለፈው መልዕክት አፍሕድን ሚወክል አይደለም» የሚለው የመከታ ሞሞ ምክንያት ምንድ ነው?  

የሚሸት ነገር አለ። የድሮው የብርሃኑ ነጋ የግንቦት 7 አሸከር *ታጣቂ?* የነበረው የዛሬ የጎጃም ፋኖ የጦር አዝማች ሆኖ ለብዙ ነገር ተጠያቂ የሆነው

ዝናቡ ከተባለው ጋር ለመነጋገር ጎንደር ድረስ ተጉዞ እየተመካከረ ቢሆንም ማስረሻን ለማስራቅ መልስ መስጠቱ ማስረሻ እንዳለው የሚሸት ነገር አለ ማለት ነው።

ዕድሜ መስተዋቱ

ጌታቸው ረዳ

 

 

 

 

 

 


No comments: