Monday, August 12, 2019

የጀኔራሉ ባለቤት በኮለኔሉ የግፍ እስር ቤት ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ) ሰኞ ነሐሴ 6/2011 (8/11/2019)


የጀኔራሉ ባለቤት በኮለኔሉ የግፍ እስር ቤት
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)
ሰኞ ነሐሴ 6/2011 (8/11/2019)
  Photo 1- The pregnant wife of General Asaminew languishing in jail with no justice under the Oromo Apartheid leader Colonel Abiy Ahmed
Photo #2- ኦነግ በእርጉዝ አማራ ሴቶች በጎሳዳ ወረዳ ሞጆ ሀርጊቲ ቀበሌ ውስጥ ያፈጸመው ጭፍጨፋ (ምንጭ አባ ዱላ ገመዳ _የኦሮሞ ሕዝብ ትግል ከየት ወዴት? (ኢትዮጵያ ሰማይ ብሎግ የተለጠፈ 2012 በፈረንጅ)


Photo #3-Amhara father and son victims of Oromo extremists in Ethiopia in Eastern Wellega region  ምስራቅ ወለጋ እናቱ በኦሮሞ አክራሪዎች የተገደለበት ህጻን ከአባቱ ጋር ኢትዮጵያ ሰማይ ብሎግ የተለጠፈ (2012 Euro-Calendar)
Photo-4-Women prisoners in Ethiopia incarsireted with their children

ኢትዮጵያ በዘመነ ወያኔ ትግራይ እና በዘመነ ኦፒዲኦ/ኦነግ/ጃዋራዊ የኦሮሞ አፓርታይድ ስርዓት የሆነውጸረ አማራውኮለኔል፤ በነብሰጡሮች ላይ ወያኔ ሲያካሂደው የነበረው ጭካኔ ዛሬም እንደ አዲስ ቀጥሎበታል። በቅርቡ ባለቤቷን ገድለውባት ለቀብር እንኳ እንዳትገኝ እስር ቤት አስገብተው ጭለማ ክፍል ውስጥ ብቻዋን አስረው እያሰቃይዋት ያለችውነብሰ ጡርየሆነቺውየዳግማዊው በላይ ዘለቀየአይበገሬው የጀኔራል አሳምነው ጽጌ ባለቤት/ ደስታ አስፋውጭለማ ውስጥ ዘግተው፤ብርሃን እንዳታይ እርስዋን እና በከርሰማህጸንዋ ውስጥ የተሸከመቺውቅዱስ ነብስከብቃላ የመነጨ አረመኔአዊ እርምጃ እየሰቃይዋት ይገኛሉ።

እናቶች ሲታሰሩ ህጻናትም አብረው የሚታሰሩባት አገር ኢትዮጵያ 28 አመት በዘመነ ትግሬዎች ስርዓት ውስጥ ከዚያ በፊት አይተነው የማናውቅ ጭካኔ በእናቶች እና ህጻናት ግፍ ታይቷል (በተለይ አማራ እናቶችና እህቶች) በጎ አድራጎት ድርጅቶች የሚዘግቡት ጥዋት ጥዋት በማለዳ የሚታየው ትዕይንት አብረው የታሰሩ የህጻናት ዕንባ ሲያፈስሱ እናቶች በጭንቀት አብረው ሲያለቅሱ እንደሚታይ  መዘገባቸው 3 አመት በፊትየማለዳ ዕምባበሚል የውጭ አገር ተራድኦ ያወጣው ዘገባ አንብቤ መኖሬን አስታውሳለሁ። ቡዙዎቹ እስር ቤቶች ማጎርያዎች እንጂ ለእናቶች እና ህጻናት እንዲሁም ነብሰጡሮች የማይመች መሆኑን ዘግበው የተሻለ የሚባለው ማሰሪያ ክፍል 47 ሴቶች 16 ልጆቻቻው ጋር 24 አልጋ ይኖራሉ።


በባሰ መልኩ ኮለኔሉ የትናንት ትውስታችን ገና ጸሓይዋ ሳትጠልቅ ያልዘነጋነውኦጋዴን ጀይልተብሎ የሚታወቀው አብዲ ኢሌ ሲያካሂደው የነበረው እስር ቤት ውስጥ በሴቶች ላይ የተደረገውን ግፍ ረስቶ ዛሬም የኦሕዴድ መሪው ኮለኔል አብይ አሕመድ እርጉዝ ሴቶችን ጭለማ ውስጥ አስገብቶ ማሰቃየት ጀምሯል። ታስታውሱ እንደሆነ ስለ ኦጋዴን ጀይል  የቀረበው 88 ገጽ ዘገባእኛ እንደ ሙታን ነን”: - በሚል ርዕስ በሶማሌ ክልል መንግስት በኢትዬጵያ ኦጋዴን ውስጥ የተፈፀመ ግፍ እና ሌሎች የሰብአዊ መብት ረገጣዎችበጭካኔ የተሞላ እና አላግባብ የመጠቃት የማሰቃየት አስገድዶ መድፈር እና ውርደትን በሰፊው እንደተዘገበ ታስታውሳላች።ዛሬ ተቀናቃኞቼ ናቸው በሚላቸው ላይ በባለቤቶቻቸው ላይ የብቀላ ጥቃት እያካሄደ ነው።


ኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ብሎ ራሱን የሚጠራ ይህየፋሺሰት ርዕዮትአጠናካሪ እራሱ ሰኔ 9 ቀን በራሱ ፓርላማ ቀርቦ ፊት ለፊት ባደረገው ንግግርየፀጥታ ኃይል ሰራተኞች በማሰቃየት እንደሚሳተፉ አምኖ ከዚያ በሗላ ማንም እስረኛ ለስቃይ እንደማይዳረግ በመበጥረቅ መናገሩን ታስታውሳላችሁ ሆኖም ፋሺዝም እና ናዚ-ዝም የፈለገው ቅቤ ብትቀባው መልኩ መለወጥ ስለማይችል ኣኦሖዴዱ ዛረም ተመልሶ ጭቃ ገብቶ እርጉዞችን በማሰቃየት ማንነቱን በግሃድ እየነገረን ነው።

በወያኔ ዘመን ብዙ የተማሩ እና ያልተማሩ አማራ ማሕበረሰቦች በገፍ ተጨፍጭፈዋል፤ተሰድደዋል፤ ታስረዋል፤ ጥፈራቸው ተነቅሏል። ዛሬም አብይ አሕመድ የሚመራው የኦሮሞ ኦሕዴድ/ኦነግ/ጃዋራዊ  ስርዓት አማራዎችን ምንም ማስረጃ ሳይዝ በጅምላ እስራት በማከሄድ ቁም ስቅላቸው እያሳያቸው ይገኛል። ዛሬም እንደ ዘመነ ደርግ እና ዘመነ መለስ ዜናዊፍርድ ቤቶችም ፖሊሶችም የሚጠይቋቸው እና የሚሰጥዋቸው የፍትሕ ብይን ተመሳሳይ ነው” “15 ቀን ለምርመራ ተጨማሪ ቀን ቀጠሮ ይሰጠን! “እሺ ተፈቅዶላችሗል 15 ቀን የተሠጠው ቀን የሚያልቀው/ሚኒስትራችን ክቡር / አብይ አሕመድን ትደግፋለህ ወይ?” በሚል ያቺው ቀን ታልቃለች። ቀጠሮ ሲደርስ አሁንም ተጨማሪ 15 ቀጠሮ ይሰጠን! በሚል መርማሪ ፖሊስ የንጹሓን ታሳሪዎች ስቃይ እያራዘመ ይገኛል። የአገሪቱ ጠቅላላ ፍርድ ቤቶች ፕረዚዳንት ተብላ የተሾመቺው የወያኔ አለቅላቂ ገረድ የነበረው አማራውን ሲያስጠቃ የነበረው የክፍሌ ወዳጆ አሞጋሽ የነበረቺው ዛሬ ደግሞየፍናፍንት ጠበቃነኝ የምትል ማዓዛ የተባለቺውም ሴትበዚህ ጉዳይ ያለቺው ምንም ነገር የለምእንዲህ ያለ የፋሺሰቶች ፍትሕ በእርጉዞች እና በጋዜጠኞች እንዲሁም በፖለቲካ ተቃዋሚ ድርጅት መሪዎች እና አባሎች እየተካሄደ ነው።

ኮለኔል አብይ አሕመድ ባለቤት አለቺው ልጆችም አሉት። ይህ ግን የዕርጉዞች እምባ አንጀቱን ሊያረራው አልቻለም። ሰውየው ወለጋ በተባለ ክፍለ ሃገር (ዛሬ በአፓርታይዶቹ አጣራር ክልል) ገና በለጋ ወጣት ዕድሜ እያለ በጨካኙ ጸረ አማራውኦሕዴድድርጅት ጎሪላ (የሽምቅ ተዋጊ) አባል ሆኖ ታጥቆ ሰው ሲገድል እና ሲያገደል ብዙ ጭካኔ ስላየ ፓርላማ ውስጥ ስለ የሴት እናቶች ከበሬታ አለኝ ብሎ ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ቢመጻደቅም አንጀቱ በጣም ቂመኛ፤ በጭብጨባና በሙገሳ የሚመረቅን በአንጻሩ የሚቃወመው ሰው ሲያደምጥ  በጭብጨባ የሞቀውን መንፈሱ ተሎ ቀዝቅዞ በራስ መተማመን ስስነትተሎ የሚገነፍል የተደበቀ የጨካኝነት መንፈስ የተላበሰ አለማዊ ሰው ነው። በባድሜ ጦርንት ጊዜ አጋጠመኝ ብሎ በይፋ የተናገረው የጭካኔ ትዕይንት ሕሊናው ሰብኣዊ ሊያደርገው አይችልም። ጀርመን ውስጥ ሰው ሲገደል እያዩ ልምድ የወሰዱ ጨካኞች በሴት እርጉዞች ላይ ግፍ ፈጽመዋል።

በወያኔ ዘመን (አብይ ወታደር ሆኖ የስለላ እና የደህንነት መሪ ሆኖ ሲሰራ በነበረበት) በወያኔ ስርዓት የአማራ ሴቶች እንዳይወልዱ (ልክ ፈላሻ ኢትዮጵያውያን ወጣት ሴቶች እስራል አገር እንደተፈጸመባቸው) ወያኔ የሚያመክን መድሃኒት እየወጋ አምክኖአቸዋል። ለስቃይም ተዳርገዋል። ዛሬ የኮለኔሉ ፖሊሶች በጀኔራል አሳምነው ጽጌ ባለቤት እና ባልተወለደ ህጻን ነብስ ጭካኔ ቢፈጽሙ ኦሕዴድ ካሁን በፊት ሲፈጽመው ስለነበር ዛሬም የአማራ ነብሰ ጡር ብትሰቃይም ምኑም አይደል፤ ምንም አይሰማውም። የወያኔ/ኦሕዴድ እና የጀርመን ናዚ በሴቶች ላይ ተመሳሳይ ባሕሪ አሳይተዋል። በሓረር፤በወለጋ፤በባሌአማራ ሴቶች ጡታቸው እየተቆረጠ፤ አንዳንዱም ነብሰ ጡሮች በቢላዋ እና በገጀራ ሆዳቸው እየተቀደደ ለሞት ተዳርጓል። ጡታቸው እየተቆረጠ ብሉት እየተባሉ የሚታወስ ነው። ከለላይ በፎቶ አስደግፌ ያቀረብኩላችሁ አማራዊት ሴት በኦነግ/ኦሕዴድ የተገደለቺው ዕርጉዝ በነዚህ ድርጅቶች የተገደለች ነች። ስለዚህ ኦሕዴድ/ኦነግ ለአማራ እናቶች እና ወጣት እህቶች ያለው ጥላቻ ዛሬም በጀኔራል አሳምነው ጽጌ ባለቤት ላይ መፈጸሙ የሚያስገርምን ቢሆንም አዲስ ሊሆነን አይችልም።ይህችን ልብ በልዋት እና ልጨርስ።

በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ታይተው የማያውቁ ዘግናኝ ወንጀሎች ተፈጽመዋል ፡፡ በመካከለኛው አውሮፓ በናዚዎች የወሰደውየአይሁድ ጥያቄ የመጨረሻ መፍትሄስድስት ሚሊዮን የአይሁድ ወንዶች ሴቶችና ሕፃናት ተገደሉ። የአማራ አጥኚዎችም 28 አመት ውስጥ ያለቀው አንዳንዱ ልክ ከአይሁዶች ጭፍጫፋ ጋር በቁጥር ብዛት መዝነው ሲዘግቡት፤ አንዳንዱ ደግሞ በእርግጣነነትግማሹን  በወያኔ መንግሥታዊና በኦሮሞ ድርጅቶች ጭፍጫፋ እንደተፈጸመ ይከራከራሉ። የናዚ ርዕዮተ ዓለምዕድሜም ሆነ ጾታሳይለይ ሁሉም አይሁዶች ሙሉ በሙሉ እንዲጠፉ ያበረታታል። ኦነጎች/ወያኔዎች/ኦሕዴድ  እና መሰሎቻቸው ባስቀመጡት ፕሮግራምም ሆነ በጻፉዋቸው ጽሑፎች እና ቃለ መጠይቆች ያንን ያስተጋባሉ (የአሰፋ ጃለታ እና / ዲማ ነገዎ ንግግርና ጽሑፍ አዲስ አበባ ከያዝን አራቱን መዓዝናት ዘግተን አማራውን ባንድ የመውጫ በር ከፍተን  ወደ አገሩ እናስወጣዋለን ያሉትን ይታወሳል) ጀርመን የተደረገውም ነው።

የናዚ የኤስኤስ እና የፖሊስ ኃላፊዎች ያንን ፖሊሲየመጨረሻ መፍትሄ” (ፋይናል ሶልሽን) በሚል ስያሜ አውጥተው የማጎሪያ ካምፖች አዘጋጅተው በግምት ከአንድ ሚሊዮን ተኩል በላይ የሚሆኑት ግድያዎች “… በቀለሞች በልጆች መልክ ወንዶችና ልጆቻችንን እና የልጅ ልጆቻችንን እንዳያሳድጉ ለመከላከልእርጉዞችን ጭለማ ውስጥ አስገብተው አሰቃይተዋል/ጨፍጭፈዋቸዋል። ይህ ያደረጉበት ምክንያት የተወለዱ አይሁዶችአድገውየወላጆቻቸውን ግፍ አውቀውቂምቋጥረው በነጭ አውሮጳውያን ላይ ብቀላ እንዳይፈጽሙ በሚል ነው። በዚህ ምክንያት መሥራት የቻሉት ነፍሰ ጡር ሴቶች እንደደረሱ ወደ ነዳጅ /ጋዝ/ ማደያ ክፍሎቹ ይልኳቸዋል (በመረዝ እንዲታፈኑ)፡፡ እርግዝናቸውን ለመደበቅ ከቻሉ አዲስ የተወለዱ ሕፃናት በሞት መርፌ (መርዝ) ወይም በመጥለቅ (ውሃ ውስጥ በመድፈቅ) እንዲገደሉ ተደርጓል። ካልሆነም እናት የሞት ፍርዱን ለማምለጥ ብቸኛ መንገድ ምስጢራዊ ውርጃ በማካሄድ ወይም አራሱ ሕፃኑን በማጥፋት ትገደዳለች። አሁንም የጄኔራሉ ባለቤት የታዋቂ ሰው ባለበት ሆና ዜናው በይፋ በመሰራጨቱ እንጂ ሌሎች ምስኪን እርጉዝ ታሳሪ ሴቶች ተመሳሳይ ወይንም የባሰ ነገር እንደማይፈጸምባቸው እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም። ስርዓቱ ልክ እንደ ወያኔ ምስጢራዊ ነው። መርማሪዎቹም፤ዳኞቹም፤ ስልቱም ፤ተቋሙም ሕገ መንግሥቱም ሰዎቹም ያው እነዚያ የምናውቃቸው 28 አመት የቀን ፀሐይ ጅቦች ናቸው።

ስለዚህ እንዲህ ያለ ጭካኔ በወ/ አሰፉ ደስታ ሲፈጸም የኮለኔሉ መንግሥት አልተፈጸመም ካለ፤ እውነትነት ካለውፍርድ ቤት ቀርባ የምትናገራቸው ቅሬታዎች እና አቤቱታዎች ለሕዝብ በድመጽዋ በቪዲዮ ተዘግቦ በመንግሥት ተብየው ሚዲያዎችና በነፃ ሚዲያዎች እስካልተብራራ ጊዜ የስቃዩ መነሻ ቀጥተኛ ምክንያት አድርገን የምተረጉመው በኮለኔል አብይ አሕመድ የሚመራው የኦሮመው/ኦነግ/ጃዋራዊ -(የኦሕዴድ መንግሥት) እንደ ዱሮው ዛሬም በሴት አማራዎች ላይ የማጥቃቱ ዘመቻ የቀጠሉበት መሆኑን እንደ ቀጥተኛ ትርጉም አድርገን እንወስደዋለን። ይህ ድርጅት እና ይህ ኮለኔል ለሕግ መቅረብ ያለባቸው እንጂ አገር ማስተዳዳር እንደማይችሉበት በአንድ ረዢም አመት የስራ ብቃት ማሳያ ጊዜ ለማረጋገጥ ችለናል። የጀኔራሉ ባለቤት በኮለኔሉ የግፍ እስር ቤት በቂም በቀል መሰቃየት የለባትም! ፍትሕ ለወይዘረዋ፤ እሰር ለግፍ ፈፃሚው ለኮለኔሉ!
አመሰግናለሁ
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)



No comments: