Sunday, February 23, 2025

በወያኔ ታጋይ ምስል የጎጃም ፋኖን ማሸብረቅ ለምን ተፈለገ? ከጌታቸው ረዳ 2/23/22

 

በወያኔ ታጋይ ምስል የጎጃም ፋኖን ማሸብረቅ ለምን ተፈለገ?

 

ከጌታቸው ረዳ

2/23/22

ሌባው የፌስቡክ ዘራፊ Gizachew Menber Hi ይባላል ከድረገጼ የዘረፈው ምስል ታሪክ ላውጋችሁ!

በስዕሉ የምታዩት ፎቶግራፍ የወያኔ ታጋይ <<አማረ ታረቀ>> ይባላል። ስለ አማረ ታረቀ ታሪክ በፌስቡኬና በድረገጼ ላይ ያቀረብኩበት ምክንያት

<<ኡር-ፋሺዝም የወያኔ ታጋዮች እውነተኛ መገለጫ>> በሚል ርዕስ12/23/2022 ኡር ፋሺዝም (Ur Fascism) ባሕሪ ምንነት ለመግልጽ የተጠቀምኩበት ምስል ነበር። ምስሉን ያገኘሁ በወያኔዎች ከሚታተሙ ከጋዜጣና ከመጽሔቶቻቸው ለብዙ አመታት ካጠራቀምኩዋቸው ከቆየው የፎቶ ማጠራቀሚያ ሰነዶቼ ላይ ነው።በራሴ መጽሐፌ ላይም ታትሟል።

ታዲያ አለመታደል ሆኖ ሞራለ ቢስ የሆነ አዲሱ ትውልድ ሌባና አጭበርባሪ በብዛት የተፈለፈለበት ወራዳ ትውልድ በመሆኑ የዘመኑ ጥበብ ይዞት የመጣው “ፌስቡክ” ለዘራፊም ለሌባም ለአጭበርባሪም ሁሉ በነጻ የተፈቀደ መድረክ ስለሆነ ፤ <<ኦርቶዶክስ ተከታይ መስሎ>> <<የማርያምን ስዕል>> በፌስቡክ ፕሮፋይሉ (መለያ) ለጥፎ አትስረቅ የሚለውን ትዕዛዝ ተላልፎ በሃይማኖት የሚነግድ አስመሳይ የፌስቡክ ሌባና ዘራፊ <<Gizachew Menber Hi>> የተባለ <<የዘመነ ካሴ የጎጃም ፋኖ ደጋፊ>> እኔ ከሦስት አመት በፊት የለጠፍኩትን የወያኔው ታጋይ የሟቹ <<የአማረ ታረቀ>> ፎቶግራፍና ታሪክ ዛሬ February 21/2025  <<Gizachew Menber Hi>> የተባለው ይህ ሌባ በፌስቡኩ ላይ <<ሜጫ ያልከፈለችው ዋጋ የለም 💔💔>> በሚል ርዕስ 

<<አንዱአለም ምህረት>> በውግያ ተሰዋ የጎጃም ፋኖ ጀግና በማለት በሚያሳፍር የበታች ስሜትነትና ሌብነት ከራሴው ፌስቡኬ ያገኘውን የወያኔው <<አማረ ታረቀን> ታሪክ <<አንዱአለም ምህረት>> ለተባለው የጎጃም ፋኖ ተዋጊ በመስጠት የሚከተለው አስገራሚ ጀግናን የማጣት ስሜት ያመጣው ስርቆትና የሞራል ዕርቃን (ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?) እነሆ እንዲህ ይላል።

Gizachew Menber Hi 

https://www.facebook.com/gizachew.menberhi

February 21/2025

<<ሜጫ ያልከፈለችው ዋጋ የለም 💔💔

የሰው ፍጡር ሆነህ ለማመን የሚከብድ ጀግንነት ፋኖ አንዱአለም ምህረት የመራዊ ተወላጅ ሲሆን በውጊያ ላይ እያለ ከጠላት በተተኮሰ ከባድ መሳርያ አንድ እግሩን ካጣ በኋላ የተቆረጠው እግሩን በማንሳት

#ድል ለአማራ

#ድል ለፋኖ

እያለ ሲፎክር ስታይ አማራ በአለማችን ላይ ያለ አስገራሚ ህዝብ መሆኑን ትገነዘባለህ ታሪካችን በአግባቡ ይሰነዳል !!

ይህን ትግል ነው እንግዲህ ለግል ጥቅም የሚሮጡት ለመጥለፍ የሚሯሯጡት። ጋዜጠኛ ኤልያስ ደባሱ ያስታውሰኝ እንጅ ከአመት በፊት ይህን መረጃ አጋርቸው ነበር ‼️> 

በማለት ለዓላማ የተሰዋ አማራ  ፈልጎ አጥቶ የወያኔዎችን ታጋይ አሟሟትና ምስልና ታሪክ “በመጥለፍ” (የራሱን ቃል ልዋስና ) ከላይ ያነባችሁትን  “የዘመነ ካሴ የጎጃም አምሐራ ፋኖ” ደጋፊዎች ዝርፍያ  ይህንን ይመስላል።

እኔን እንዳስደነገጠኝና እንዳስገረመኝ እናንተም ይህንን አስገራሚ የበታችነት ስሜትና ጀግና ፍለጋ ወደ ትግሬ ታጋዮች መለጠፍ  በወያኔ ታጋይ ምስል የጎጃም ፋኖን ማሸብረቅ ለምን ተፈለገ? ብላችሁ እንደምትገረሙ ገምታለሁ።  

ወያኔ ትግሬዎች አማራውን ለምን ይንቁታል ብትሉ “በምደረ አምሐራ ጀግና የታጣ ይመስል” እንዲህ ያሉ ደደቦችን የዝቅተችነት ስሜት ያጠቃቸው የትግሬዎችን ጀግንነት የሚመኙ <<የራሳቸውን ፈልገው ያጡ>> አንዳንድ ተምበርካኪ አምሐራዎችን ስለሚታዘቡ ነው።

የሚገርመው ደግሞ በፌስቡኩ ላይ የተሰጡት “አስተያየቶች” ብዙ ደንቆሮ እንዳለ ማሳያ ምልክት ያየሁበት ነው። አንዳንዱ በበዳሜ ኢትዮ ኤርትራ ጦርነት የተሰዋ ምስል ነው ሲል አንዱ ደግሞ “ጅግናው አማራ ለታሪክ ሰነድ አስቀምጬዋለሁ” እያለ የሚጃጃል ከንቱ ትውልድም አለ። ያም ሆኖ ትዝብታችሁን በትክክል ለማስጨበጥ እውነተኛው የለጠፍኩት የወያኔው አማራ ታረቀ ምስልና ታሪክ በድጋሚ እነሆ  የሚከተለው ነው

ኡር-ፋሺዝም የወያኔ ታጋዮች እውነተኛ መገለጫ
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
12/23/2022

 https://www.facebook.com/photo/?fbid=860159945291867&set=pob.100038936079701

ኡር ፋሺዝም (Ur Fascism) ባሕሪ ምንነት የነገረን ተመራማሪው 7 የውጭ አገር ቋንቋዎች አጣርቶ መጻፍና ማንበብ ችሎታ ያለው ጣሊያናዊውኡምቤርቶ ኤኮነው። በትርጉም ካልተሳሳትኩኡር ፋሺዝምዘላለማዊ ሺዝም ማለት ይመስለኛል አንግሊዞች cult of tradition የሚሉት።

ኡር-ፋሺዝም ምንም ብንሰለጥንም አገዛዞች የተለያዩ ልዩነቶች ቢኖራቸውም የኡር ፋሺዝም ባሕሪ ዛሬም በተለያዩ ተዋጊ ቢድኖችና መንግሥታት ተኮልኩሎም ሆኖ በይፋ የሚታይዛሬምየሚገኝልዩየሆነ ፋሺስታዊ ባሕሪ ነው። ዳሰስ ብታደርጉት ታገኙታላችሁ ይላል ተመራማሪውኡሜርቶ ኤኮ” ኡምቤርቶ ኤኮ በመጽሐፉ መግቢያ እንዲህ ይላል። 1942 በአሥር ዓመት ዕደሜየለሙሶሎኒ ክብር እና ለኢጣሊያ ዘላለማዊ እጣ ፈንታ እንሙት?” በሚለው የጥያቄ ርዕስ ላይ በኢጣሊያ ወጣት ፋሺስቶች መካካል በተደረገው የንግግር ውድድርብልህ ልጅነበርኩና ባደረግኩት ንግግር አዎንታዊ አድናቆት በማግኘቴ የብልህ ተናጋሪ ወጣት ሽልማት ተቀዳጀሁ። ይላል።

ኡምቤርቶ ኤኮ << ህይወት>> ለኡር-ፋሺዝም <<የህይወት ትግል የለም>> ይልቁንም << ህይወት ለትግል ነው የምትኖረው>>ይላል።

ስለዚህ-ይልና

<<
ህይወት ዘላቂ ጦርነት ስለሆነ በጸጋ ይቀበለዋል። ይህ ግን

የአርማጌዶን ስብስቦችን ያመጣል። ጠላቶች መሸነፍ ስላለባቸው የመጨረሻው ጦርነት ሊኖር ይገባል ስለሚል፤ በዛው ቦግ እልም እያለ ያልተቋረጠ የጸብና የጦርነት ጫሪነት የእንቅስቃሴው ሂደት ዓለምን በመቆጣጠር ወርቃማ ሰላምን ማምጣት ይቻላል የሚል ባህሪ አለው>> ይላል። ነገር ግን እንዲህ ያለው ሁሉንም ተቆጣጥሮ ሰላም የሚያመጣ ተስፈኝነት የተሳካለት ፋሽስት መሪ የለም>>

በማለት የኡር ፋሺዝም ባሕሪ ርቀት ይገልጽና መጽሐፉን ሳነበው፤ ከጠቀሳቸው የኡር ፋሺዝም 14 ባሕሪያቶች ውስጥ ቀልቤን የሳበው ከርዕሴ መግቢያ የለጠፍኩት በመጀመሪያው 17 አመት የወያኔ የጫካ ጦርነት ዘመንአማረ ታረቀየተባለ የወያኔ ታጋይ በውግያው ውስጥ ቀኝ እግሩ በከባድ የጥይት አሎሎ ተመትቶ ተቆርጦ በመውደቁ የተቆረጠውን እግሩ አንስቶ ወደ ሰማይ በመቀሰር የሞት ብስራቱን በጸጋ በመቀበል ወዲያውኑ ህይወቱ አልፏል።

እንዲህ ያለ ሞት ኡምቤርቶ ኤኮ አንዲህ ሲል ይገልጸዋል።

<< …
በእንደዚህ ዓይነት አመለካከት ሁሉም ሰው ጀግና ለመሆን ይማራል፡ በእያንዳንዱ አፈ ታሪክ ውስጥ ጀግና ልዩ ፍጡር ነው። ነገር ግን በኡር-ፋሺስት ርዕዮተ ዓለም ውስጥ ጀግንነትብርቅአይደለም የተለመደ ነው። ይህ የጀግንነት አምልኮከሞት አምልኮጋር በጥብቅየተያያዘነው። የፈላንግስቶች መሪ መፈክርቪቫ ሙርቴ” ("ሞት ለዘላለም ይኑር!") ይላሉ። ይህ የሞት አምልኮ ባሕሪ በአጋጣሚ አይደለም፡ ፋሺስትባልሆኑማህበረሰቦች ውስጥ ምእመናንሞት ደስ የማይልአንደሆነ ይነገራቸዋል። አማኞች ከተፈጥሮ በላይ የሆነ ደስታ ላይ ለመድረስአሳማሚው መንገድእንደሆነ ይነገራቸዋል። በአንፃሩ የኡር-ፋሽስት ጀግናየጀግንነት ሞትንይመኛል፣ ለጀግንነቱሞት” “ምርጥ ሽልማት ተብሎ ይታወጃል። የኡር-ፋሽስት ጀግናለመሞት ትዕግስት የለውም”” ትዕግስት በማጣቱምሌሎች ሰዎችንወደሞትይልካል። >>

በማለት ኡር ፋሺሰቶችቪቫ ሙርቴ” - "ሞት ለዘላለም ይኑር!" እያሉ የሞት ቅድስና በመስበክ በጦርነት ወቅት እኔ ልሙት እኔ ልሙት እየተሽቀዳደሙ ወደ ጦርነት እሳት በመግባት ይሰዋሉ። ይህ የኡር ፋሺዝም 14 ባሕርያቶች አንዱ ሞትን በቅድስና እንዴት እንደሚያመልኩት ስንመለከት የወያኔ እና የሻዕቢያ ተዋጊዎች ባሕር ኡር ፋሺዝም ባሕሪ እንደተላበሱ ከሚዘግብዋቸው የታሪክ ማሕደሮቻቸው ለማወቅ ችለናል።

የኡር ፋሺስት ተከታዮች ሞትን ስለማይፈሩ የሰው ልጆች የሞት ምንጭ በመሆን በራሳቸው ሞትን በቅድስና ስለሚቀበሉ በጦርነት ወቅት አስቸጋሪ (ጠንካራ ተዋጊዎች) ሆነው ይታያሉ። ጠንካራ ተዋጊነታቸው ምንጩለመሞት ትዕግስት የላቸውም ሌሎች ሰዎችን በመረሸንም ሆነ ወደ ሞት ለመላክ ግድ የሌላቸው ገራፊዎችና ጨካኞች ናቸው። በሁለመናዊ መልካቸው ከኡር ፋሺዝም ገንዳ የተቀዱት የኦነጉ የአብይ አሕመድኦሮሙማእና የመለስ ዜናዊህወሓትከኢትዮጵያ የፖለቲካ ሱታፌ መታገድ አለባቸው እያልን የምንወተውተው ለዚህ ነው።

ሰላም-ሰንብቱ
ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 

No comments: