Wednesday, June 29, 2022

መንግሥት አልባዋ ኢትዮጵያ የምትገኝበት የታሪክ አጣብቂኝ! ይነጋል በላቸው Ethiopian Semay 6/29/22

 

መንግሥት አልባዋ ኢትዮጵያ የምትገኝበት የታሪክ አጣብቂኝ!

ይነጋል በላቸው

Ethiopian Semay

6/29/22

ዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2014ዓ.ም ከምሣ በኋላ ቢሮ ገብቼ አንዳንድ ድረ ገፆችንና የዩቲብ ቻናሎችን እመለከት ያዝኩ፡፡ ንዴት ብስጭቴን እንደምንም ተቆጣጥሬ የተወሰኑትን ዝግጅቶች ከያይነቱ ተከታተልኩ - እንደምንጊዜውም ሁሉ፡፡ አንደኛውን ግን መጨረስ አልቻልኩምና ስለመንግሥት አልባዋ ሀገራችን የአሁንና የወደፊት ዕጣ ፋንታ የተሰማኝን ልጫጭር ብዬ ብዕሬን ከወረቀቱ አዋደድኩ፡፡

ያ ለዚህ ማስታወሻየ መነሻ የሆነኝ ጉዳይ ከሀገር ምሥረታ አኳያ ከዳዴም ያላለፈችው የትናንቷ ደቡብ ሱዳንም ወግ ደርሷት ኢትዮጵያን ወርራ 170 ኪሎ ሜትሮችን በመዝለቅ የወርቅ ማዕድናችንን ተቆጣጥራ ወርቃችንን በግላጭ እያፈሰች የመገኘቷን መርዶ የሰማሁበት ዝግጅት ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ብቻውን ኢትዮጵያ መንግሥት እንደሌላት በግልጽ የሚናገር አስደንጋጭ ክስተት ነው፡፡

ወዲያውኑ “ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ” የሚለው ነባር ብሂል ታወሰኝ - የጄኔራል ጃጋማ ኬሎን ሀገር፣ የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴን ምድር አንድ እዚህ ግባ የማይባል የሽፍታ ቡድን ሲወርረውና ሲቆጣጠረው ምን ዓይነት የታሪክ ምፀት ላይ እንምንገኝ ታዬኝና ቁጭቱን አልችለው አልኩ፡፡ የሚገርመው ደግሞ የአካባቢው ባለሥልጣን ደቡብ ሱዳን ወርራን የወርቅ ማውጫ የማዕድን ሥፍራችንን መቆጣጠሯን ለመንግሥት ቢያሳውቅም መልስ አለማግኘቱ ነው፡፡ ነገሩ በዚያም ብቻ አላበቃም፤ መንግሥት ተብዬው የአቢይ ጎራ የሚሰጠው ማስተባበያ ሁሉ አንድም እውነት የሌለበት በውሸት የታጨቀ ዕብለት መሆኑም በግልጽ ታይቷል፡፡ የተወረረው አካባቢ የብልጽግና የወረዳ ኃላፊ በተደጋጋሚ ችግሩን ቢያሳውቅም በርሱ ስም በፋና በወጣ ማስተባበያ ካለሰውዬው ዕውቅና ፎቶውን በመጠቀም ምንም የደረሰ ችግር እንደሌለና የሚባለው የደቡብ ሱዳን ወረራ ሀሰት እንደሆነ ቅንጣት ሳያፍሩ መግለጻቸው ነው፡፡ ምን ጣለብን ጎበዝ!

እነዚህ ሰዎች ጥቂት ጊዜ ከቆዩ ግዴላችሁም ለፊጂና ለሲንጋፖርም ከኢትዮጵያ መሬት እየጎመደሉ ኑና ውሰዱ ሳይሏቸው አይቀርም፡፡ ጠያቂ ጠፍቶ እንጂ እነማሊም እነጊኒ ቢሳውም መውሰድ ይችሉ ነበር፡፡ ሶማሊያና ጂቡቲማ ተለምነው እምቢ ብለው ይሆናል እንጂ እስካሁን ድረስ አዋሽ አርባ ድረስ በመጡ ነበር፡፡ እንዲያው ግን ፈጣሪን ምን ብንበድለው ይሆን ይህን የመሰለ በላዔሰብ ሰውዬ የላከብን? ኧረ እንጸልይ ምዕመናን!!

በነገራችን ላይ ሀገራችንን በአንክሮ ለተመለከተ ኢትዮጵያ ለብቻዋ የታወጀ የ3ኛ ዓለም ጦርነትን እያስተናገደች ያለች ሀገር ትመስላለች፡፡ የማኅበራዊ ሣይንስ ምሁሮቿ በሙሉ የሰውን ደም እየመረመሩ ነገድን ከነገድ በማበላለጥ “ይህኛው ደም ገዢ ሊሆን፣ ያኛው ነገድ ግን ተገዢ ሊሆን ይገባል፤ አለበለዚያ አንክቶ አንክቶ መጨረስ ነው” በሚል ምርምር ተጠምደዋል፡፡ የጦር ምሁሮቿ በሙሉ ጦርነት በመንደፍና በማቀድ ላይ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ ገበሬዎቿም ዶማና ሞፈር ቀምበር ሰቅለው ወደጦር ዐውድማ እየተመሙ ናቸው - “ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ” በሚል መፈክር ታጅበው ለዚያውም፡፡

ወጣቶች በሙሉ አንድም በልዩ ልዩ ሱስና በመጠጥ ተጠምደው ጊዜያቸውን በወርቃማ የተዝናኖት ፕሮግራም እያሳለፉ ነው ወይንም የጦር ልምምድ እያደረጉና ያደረጉትም በተለይ ኦሮሙማዎቹ የወገኖቻቸውን በተለይም የአማራውን አንገት ሕጻን ዐዋቂ ሳይሉ ባገኙበት ቦታ እያረዱ ነው - ለዚህም ግዳጃቸው እንደወሮታ ተቆጥሮላቸው በአዲስ አበባ ማለቴ በፊንፊኔ የተገኘ ባዶ ቦታ ሁሉ እየታደላቸው - ከባለሦስት መኝታ ቤት ኮንዶሚኒየም ምርቃት ጋር ነው ታዲያ - መምነሽነሻቸውን በስፋት ቀጥለዋል፡፡ የዚህ ሁሉ ድል ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ ልትኮራ ይገባታል፡፡ የእያንዳንዱ ክልልና መስተዳድር ዋና ሥራ ልማትና እንደሚባለው ብልጽግና ሳይሆን የሌት ከቀን ስብሰባው አጀንዳ “እነእንትናን እንዴት እናጥፋ? ሕዝቦቻችንን እርስ በርስ አቃርነን ስናበቃ እነሱን በማፋጀት ሥልጣናችንን እንዴት እናራዝም?” የሚል ነው - “ሀኪም ቤት፣ ትምህርት ቤት፣ መንገድ፣ ጤና ኬላ፣ ወዘተ. ለሕዝባችን እንገንባለት” የሚል ወሬ ዕርም ነው፤ ከጦርነት የሚተርፍን በጀት ባለሥልጣኖቹ ይንደላቀቁበት እንጂ ሰፊው ሕዝብማ አየሩንና  ፀሐይዋንም በነፃ በማግኘቱ ዕድለኛ ነው፡፡ ኢትዮጵያ እኮ መጠናት ያለባት ልዩ ሀገር ናት፤ ሕዝቧም አብሮ ይጠና ታዲያ፡፡

ለሀገር የጦርነትና የርስ በርስ ፍጂት ስኬት ሲባል የሚመለከተው የዘረኛው መንግሥት አካላት ሁሉ በመቶ ሽዎች የሚገመት ልዩ ኃይልና ሚሊሻ፣ መከላከያና ደኅንነት፣ ፌዴራልና ክልላዊ ፖሊስ፣ ኮማንዶና ሪፓብሊካን ጋርድ …  እያሰለጠኑ ማሰማራት ዓይነተኛው ተግባራቸው ሆኗል፡፡ ይህ ወርቃማ የጦርነት ዕድል እያለ ማን ወደ ምርት ይግባ? ይህን ሁሉ የሰው ኃይል ለልማት አሰልጥኖ ወደግብርናውና ወደሜካናይዝድ እርሻው፣ ወደ ፋብሪካውና ኢንዱስትሪው ማን ያስገባው? ተመልከትልኝ - የኦሮሞ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ፣ የአቢይና ሽመልስ ሸኔ፣ የኦነግ ልዩ ኃይል፣ የትግራይ ልዩ ኃይል፣ የትግራይ መከላከያ፣ የአማራ ፋኖ፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ የአማራ ሚሊሻ፣ የሶማሊያ ልዩ ኃይል፣ የቤንሻንጉል ልዩ ኃይል፣ የአፋር ልዩ ኃይል፣ የጋምቤላ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ፣ የደቡብ ልዩ ኃይል፣ የቅምብቢት ታጣቂ፣ የሆሮጉድሩ ሸማቂ…. ፐፐፐፐፐፐ…. እንዴት ዕድለኞች ነን ግን!! “ሁሉ አረሰ ማን ይሸምት” አትልልኝም?

ሀገር የታጣቂዎች መፈንጫ፣ የአምራቾች ማፈሪያና መሳቀቂያ ሆነች፤ ስም የሌለው ድድብና፤ ድንበር ያጣ ድንቁርና፡፡ ታዲያ ማን አምርቶልን ነው ለመዋጋትስ የሚሆን እህል ውኃ የምናገኘው? እያስለቀሰች የምታስቅ ሀገር፡፡ ሁሉም ለውጊያ ከተሰለፈ ማን ይረስ? ማን እህል ያምርት? ይህን አስከፊ ምስል የሚለውጥ አንድ ኔልሰን ማንዴላ እንዴት ይጥፋ? ይህን የተንሸዋረረ የዘርና የቋንቋ ምድራዊና ኃላፊ ጠፊ ልዩነት የሚያረግብና ወደልማት የሚመልሰን አንድ ማኅተመ ጋንዲ እንዴት እንጣ? ከ120 ሚሊዮን ሕዝብ መካከል እነዚህን ዕብዶች በተገኘው መንገድ ሁሉ ታግሎ የሚጥል መጥፋቱ በርግጥም ሀገራችን የመረረና የከረረ ዕርግማን ውስጥ እንዳለች መረዳት አይከብድም፡፡ መጥኔ ለወጣቶች - እኛስ መጓዛችን ነው፡፡ ለማንም አይመከርም እንጂ መሄድ ደስ ሲል!! “ተኖረና ተሞተ!” ይሉ ነበር አሉ ባላምባራስ እርገጤ የድሃ ሰው ቀብር ላይ ሲገኙ፡፡

የአቢይ ቡድን ገና ለገና ለቅዠት ሀገር ለኦሮምያ ግዛት የሠሩ መስሏቸው ኢትዮጵያን ብቻ ሣይሆን ምሥራቅ አፍሪካን ባጠቃላይ ማተረማመሳቸው ገሃድ እየወጣ ነው፡፡ መጨረሻው ለሁሉም አያምርም፡፡ ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነውና የዚህ ጅምራቸው መጨረሻ በኢትዮጵያ ብቻ አይቆምም፡፡

አቢይ በርካታ የሀገር አመራር ሪከርዶችን እያስመዘገበ መሆኑ ይነገርለታል፡፡ ይህችን ደቡብ ሱዳን ራሱ ጎትጉቶና ጎትቶ እንዳመጣት መረዳት አይከብድም፤ ዝም ብላ መቼም ይህን ያህል አትዳፈርም፡፡ ይሄው ጉደኛ ሰውዬ ወደ ሥልጣን በወጣ ሰሞን ሰሜን ሱዳን ሰፊ የአማራ ግዛት እንድትወርና እንድትይዝ በውጤቱም አማራን እንድትወጥርለት በምሥጢር ተስማምቶ የኢትዮጵያን መሬት በገዛ ፈቃዱ አስያዘ፡፡ ይህ ደግሞ የአንድ ሀገር መሪ የሌላ ሀገር መሪን ለምኖ “ በሞቴ ግዛቴን ውሰድልኝ” በሚል ያልተለመደ ተማፅኖ አዲስ ሪከርድ አስመዘገበ፡፡ ቀጠለና ራሷን የቻለችን የቀድሞ የኢትዮጵያ ግዛት ኤርትራን ወደ ትግራይ ገብታ አዳዲስ መሬቶችን እንድትወርና እንድትይዝ ተስማማ፡፡ ይህም ሁለተኛው የ“እባካችሁ አገሬን እየቆረሳችሁ ውሰዱልኝ” ዓይነት ተጨማሪ ሪከርድ ነው፡፡ ሦስት አላችሁልኝ? ኧረ ጉዱ ብዙ ነው!!

በሀገር ውስጥ ያየን እንደሆነ የአማራን ነባር ግዛቶች ወልቃይትንና ራያን ለትግራይ ለመስጠት ቀን ከሌት እየለፋ ነው፡፡ ምን ዓይነት ቀትረ ቀላል ሰውዬ እንደሆነ ሳስብ ግርም ይለኛል፡፡ በተለይ በአማራ መሰቃየትና መሞት፣ መሰደድና መፈናቀል፣ መቸገርና መንገላታት ፈጽሞውን የሚረካ አልሆነም፡፡ አማራ ለዚህ ሰውዬ እርካታ ሲል ምን ይሁንለት? የሚደንቀው ሚስቱና ልጆቹ ጥሎባቸው አማራ ናቸው አሉ፡፡

እንግዲህ ይህንና የመሳሰለውን ክስተት ስንታዘብ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት መንግሥት እንደሌላት ለመረዳት ማንንም መጠየቅ አይገባንም፡፡ አሁን ሕዝቡ እየኖረ ያለው በኪነ ጥበቡ ነው፡፡ ፈጥሮ የማይረሳው ጌታ እየጠበቀን እንጂ እንደኦሮሙማው የአራት ኪሎ መንግሥት ተብዬ ዘረኛ ስብስብ ቢሆን ኖሮ አንድም ቀን ማደራችን ራሱ እንደህልም በተቆጠረ ነበር፡፡ መንግሥት ሲያምረን ይቀራል፡፡ የለንም ወንድማለም፡፡

ነገረ ሥራችን ሁሉ ዕብድ እንደያዛት ብርሌ ወይንም ብርጭቆ ነው፡፡ “የዕብድ ቀን አይመሽም” ስለሚባል እስካሁን ቆየን እንጂ ከሞትን ሰነበትን፡፡ በሌላ ሥነ ቃላዊ አገላለጽ ደግሞ “የዕብድ ቅል ማንጠልጠያው ክር” ይባላልና ዛሬ ማታ ወይንም ነገ ጧት ምን እንደምንሆን አናውቅምና ያን ማሰቡ ራሱ  ጭንቅላትን ያዞራል፡፡ ስለሆነም ተሰሚነት ያላችሁ ከሁሉም ጎሣና ነገድ የምትገኙ ትልልቅ ሰዎች እንቅልፍ ባይዛችሁ ጥሩ ነው፡፡ ዳኛ በሌለበት፣ ፖሊስ በሌለበት፣ ህግም ህግ አስፈጻሚም በተጓደሉበት፣ እንደልቡነት በሰፈነበት፣ ጉልበተኞች በገነኑበት፣ ዘረኝነት በተንሰራፋበት፣ የማይም አገዛዝና የውሸት ዲግሪ ከግርጌ እስከራስጌ በነገሠበት፣ በአእምሮ ሳይሆን በሆድ ማሰብ በተስፋፋበት፣ በእግር ተሄዶ ሳይሆን በእጅ ስንዘራ ብቻ የትኛውም ዓይነት ጉዳይ በሚፈጸምበት በዚህ የብላ ተባላ ዘመን በደቂቃዎች ውስጥ ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት ይከብዳል፡፡ በመሆኑም እውነተኛ ምሁራንና ለሀገርና ለወገን ተቆርቋሪ የሆናችሁ ጤናማ ዜጎች በኅቡዕም ቢሆን እየተገናኛችሁ በመነጋገር ይህ አሁንም ቢሆን እንዳለ የማይቆጠረው የወሮበሎች መንግሥት በቅርብ ፍርክስክሱ በሚወጣበት ጊዜ የሽግግር መንግሥት ሊመሠረት የሚችልበትን ብልሃት ከወዲሁ ቀይሱ - ግን የምትተማመኑ እንጂ አስመሳዮችንና ለጥቅምና ለዘር ሐረግ የተንበረከኩትን እንዳታስጠጉ ተጠንቀቁ፡፡

እንዲህ ካልተደረገ ሶማሊያና ሦርያን የመሆን ዕድላችን እጅግ ሰፊ ነው፡፡ አሁንም ራሱ ወደዚያ ሁኔታ ውስጥ የገባን ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም የአቢይ ወለፈንዴው መንግሥት እንኳንስ ከአዲስ አበባ ውጪ አዲስ አበባ ውስጥም ምንም እየሠራ አይደለም፡፡ ከአዲስ አበባ አሥር ኪሎ ሜትርም ሳትወጣ ለምሣሌ አማርኛ መናገርና የኢትዮጵያን ባንዲራ መያዝ አይፈቀድልህም፡፡ እንዲያ ብታደርግ እሥር ቤት ይወረውሩሃል፡፡ አላምነኝ ካልክ የኢትዮጵያን ባንዲራ ወይንም አፄ ምኒልክ የተሳሉበትን ቲ-ሸርት ለብሰህ ለገጣፎ ሂድ፡፡ ምድረ ቄሮ ፖሊስ ተሸክፎ ሰደቃህን ያወጡልሃል፡፡ ለበላይ አመለክታለሁ ብትል ደግሞ ይስቁብሃል፤ ለምን ብትል ጃዝ የሚባሉት ከላይ መሆኑን ያውቃሉና፡፡ የክልሉን እንተወውና ፌዴራል ተብዬውም፣ የአዲስ አበባ መስተዳድርም ምን አለፋህ ሁሉም የሥልጣንና የኃላፊነት ቦታ በኦነግ/ኦህዲድ በመያዙ የትም ልሂድና ላመልክት ብትል “ሰባራ ዶሮ ሳትቀድምህ ሂድና አመልክት!” ትባላለህ - ሊያውም በኦሮምኛ፡፡ ገባህ? ስለዚህ ዋናው አትቀደም ነውና ጊዜ እስኪያልፍ ጠንቀቅ በል፡፡

“ጉድ ነሽ ያንኮበር ቅጠል፤ የተሠራሽው ቂጥ ለማቃጠል” ያለው ሰውዬ ወዶ አልነበረም - የደረሰ ደርሶበት እንጂ፡፡ ይብላኝልሽ አሁን ፀጥ ብለሽ እንቅልፍሽን የምትለጥጭ የአዲስ አበባና የትላልቅ ከተሞች ነዋሪ ሁላ!! እማይደርስ መስሎሻል፡፡ የ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ኦሮሙማ በጭካኔውና በዐረመኔነቱ ዕጥፍ ድርብ ተሻሽሎ የቀደሙ አባቶቹን ስህተትም አርሞ በአዲ ጎራዴ መጥቶብሻል፡፡ ዛሬ ተራው የአማራ ይሁን እንጂ ነገ ደግሞ የቀሪዎቹ ቤርቤረሰቦችና ሂዝቦች መሆኑ በጣም ግልጥ ነው፡፡ ከሌሎቹ መጀመር ልፋትና ድካምን ስለሚያበረታበት ነው አያ ኦሮሙማ አማራ ላይ የጀመረው፤ እሱን ከጨረሰ ግን “ዕዳው ገብስ ነው” ብሎ ያምናል፡፡ እንደነሱ እምነት ሌሎቹን በቀላሉ ያንበረክኳቸዋል - በቆንጨራ ወይንም በሞጋሣ፡፡

ምኞት አይከለከልም፤ በዚህ መንገድ ግን የትም አይደረስም፡፡ እናም ኦሮሙማዎችዬ ማሰብ ጀምሩ፡፡ ማሰብ ከጀመራችሁ አሁን የተነጠቃችሁትን ሰው የመሆን ዕድል የሚከለክላችሁ የለም፡፡ ሁሉም ልብ ይበል! ሳይወድ በግዱ ከአማራ ወላጆች በመፈጠሩ ብቻ የሦስት ቀን ዕድሜ ሕጻን ልጅ አንገት ከነእናቱ በሠይፍ መቁረጥ እንኳንስ ደራሳውንና ዳዋሮውን፣ እንኳንስ ደቡቡንና ሰሜኑን፣ እንኳንስ ትግሬውንና ከምባታውን፣ እንኳንስ ጉራጌውንና በርታ - ሙርሲውን፣ ወገናችን ነው የምትሉትን ዜጋ ሳይቀር ስሜት ያጨፈግጋልና ከገባችሁበት የጨቀዬ የአስተሳሰብ ዐውድ በቶሎ ውጡ - ለናንተው ነው፡፡ ነግ በኔ የሚባል ብሂል ስላለ በአንዲት አስጠሊታ ኦፕሬሽናችሁ 120 ሚሊዮኑን ሕዝብ ነው ቋቅ እንዲላችሁ ያደረጋችሁትና ወደፊትም በዚሁ ከቀጠላችሁ የምታደርጉት፡፡ ከገዳይ ይልቅ ሟች ረጂም ዕድሜ እንዳለው የምነግራችሁ በማያወላውል እርግጠኝነት ነው፡፡ የምትገድሏቸው ሰዎች የእናንተን መቀበርያ ዘላለማዊ ጉድጓድ እንደቆፈሩ ካልገባችሁ እውነትም ከሰውነት ተራ የወጣችሁ ሰው መሳይ ዐውሬ ናችሁ፡፡ አቢይና ሽመልስ የእናንተን ዘላለማዊ ሞት አይሞቱላችሁም - የነሱንም በቻሉት፡፡ አቢይና ሽመልስ የአጋንንት ልዑካን ናቸው - ይህንንም እነሱና ላኪያቸው ያውቃሉ፡፡ እናንተ ግን በበሬ ወለደ ፕሮፓጋንዳ ተጠምቃችሁና በጥቅም ታውራችሁ፣ ባለመማር  የማይምነት ጥቁር መጋረጃም ተሸብባችሁ የነሱ ባርያ ሆናችኋል፡፡ እናም ልብ በይ - ምድረ ሸኔ ቁንዳላ ፀጉርሽን እየፈተልሽ ሕጻንና አሮጊት መግደልን እንደጀብድ ቆጥረሽ አሁን ብትሞላፈጪ የነገው ቀን ለእያንዳንድሽ ከተራው የቀኑ ጨለማም የበረታ ድቅድቅ ጽልመት ነው፡፡ ለነገሩ እኔን ምን አገባኝ!!

Ethiopian Semay

 

 

Tuesday, June 28, 2022

ከዐማራ ጋር ጦርነት የገጠሙ ኃይሎች ስም ዝርዝር እነሆ! ዳግማዊ ጉዱ ካሣ ETHIOPIAN SEMAY 6/28/2022

 

ከዐማራ ጋር ጦርነት የገጠሙ ኃይሎች ስም ዝርዝር እነሆ!

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ETHIOPIAN SEMAY

6/28/2022

የዛሬውን ጽሑፌን ማን እንደሚያስተናግድልኝ ከወዲሁ ሳስበው ይጨንቀኛል፡፡ ባህላችን ባብዛኛው የመሸፋፈንና እውነትን የመደበቅ በመሆኑ ትንሽ ገለጥ ያለ ነገር ሲገጥመን በ“ከነገሩ ጦም እደሩ” ብሂላችን እየተጋረድን ብዙዎቻችን ከእውነቱ እንርቃለን፡፡ እውነት ግን ምን ጊዜም እውነት ናትና የትም አትሄድም፤ እኛ ብንሸሻትም እርሷ ግን እኛኑ ትከተለናለች፤ ከኛው ጋርም ትኖራለች፡፡ ይህ ሁሉ ዳር ዳርታ አንዲት አይነኬ ጉዳይ ልናገር ስላቆበቆብኩ ነው - ወረድ ሲል ታገኟታላችሁ፡፡

እንደውነቱ ዐማራ ያልታደለ ሕዝብ ነው፡፡ ምናልባት እርግማን ይኖርበት ይሆናል፡፡ እርግማን ደግሞ ጊዜውን ጠብቆ ቢነሳም እስከዚያው ግን አሣርን ያበላል፤ እያየነው ስለሆነ ማስረጃ መጥቀስ አያስፈልገንም፡፡ እኔ ሳውቅ እንኳን ላለፉት 40 ዓመታት ገደማ ዐማራ በገጠርም በከተማም ፍዳውን ሲቆጥር እንጂ አንድም ጊዜ እፎይ ሲል አላስተዋልኩም - በአንጻራዊነት አንዱ አገዛዝ ከሌላው ሻል ሊል ቢችል እምብዝም አትታዘቡኝ፡፡ ይሄ መከራና ስቃዩ ደግሞ ለዐማራ የሚሞቀው የሚበርደው አይመስልም፡፡ በጣሙን ተለማምዶታል፡፡ እንደበግ መታረዱንም፣ እንደፍልስጥኤም መሳደዱንም፣  በሀሰት ትርክት የተነሣ እንደ አይሁዳውያን መጠላቱንም … ተለማምዶት ደንዝዟል፡፡ “ለዚህ ሕዝብ ይህ ሁሉ ይገባዋል ወይ?” የሚለው ጥያቄ ትልቅ ጥያቄ ነው፡፡ ዕውቀቱ ያላችሁ ፈትሹና ንገሩን፡፡

የዐማራ ጠላቶች በስም ይታወቃሉ፡፡ የተወሰኑትን አሁን በዚህ አጋጣሚ መጥቀስ ይቻላል፡፡ በክፋት ደረጃቸው ቅደም ተከተል ስለመጥቀሴ እጠራጠራለሁና ደረጃ ውስጥ አልገባም፡፡

1. ኢሕዲን - ብአዴን - አዴፓ፡፡ ይህ ሳይወለድ የጨነገፈ ሕወሓት ሠራሽ የሆዳሞች ጥርቅም ላለፉት 40 ምናምን ዓመታት በዐማራ ስም በወያኔ ተሰፍሮና ተለክቶ ለዐማራ በተሰጠው ክልል ውሰጥ ዐማራን እንደሚወክል የክልል መንግሥት ተቆጥሮ በዐማራ ላይ ጢባጢቤ ሲጫወት ከረመ፤ አሁንም በዐማራ ስም የዐማራ አለኝታዎችን እያሳደደ በመግደልና በማሰር መላውን የዐማራ ሕዝብ ለተረኞች አስረክቦ ዐማራን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት እየተጋ ይገኛል፤ የጭራቁ አቢይ ኦነግ-ሸኔ አማራን አርዶ እንዲጨርስ ከተፈለገ ለአማራ የሚቆረቆር አንድም ኃይል የትም ሥፍራ መኖር የለበትም፡፡ ስለዚህም ዐማራን የሚያርደው ሸኔ እየፋፋና እየለመለመ፣ አርፎ የተቀመጠው ፋኖ ግን መወገድ አለበት፡፡ ከዚህ መሪር እውነት በተጓዳኝ ያለው ሃቅ ደግሞ አንድ የብአዴን አባል ሆዱ አይጉደልበት እንጂ የዐማራ ማለቅ ሲያሳስበው አይታይም፡፡ እንደምገምተው የዚህ ቡድን አባላት የሰውነትን ቅርጽ ተላብሰው በሰው አምሳል የተፈጠሩ ዓሣሞችና ጅቦች ይመስሉኛል፡፡ በዚህን አሳሳቢ የኅልውና ወቅት እንኳን ከአራጆቹ ጋር ተባብረው ዐማራን እያሳደዱት ነው - የሚገርም ተፈጥሮ ነው፡፡ ለወደፊቱ ቢቻል በሕይወት ተይዘው አለበለዚያም ሬሣቸው/አፅማቸው ተለይቶ መመርመርና ሥነ ተፈጥሯቸው መታወቅ አለበት፡፡ ዓለም እስከዛሬ እንደነዚህ ያለ ጉግማንግ ፍጡር አይታ አታውቅም፡፡ ሁሉም በመጨረሻ ከነዘር ማንዘሩ ዋጋውን ማግኘቱ ባይቀርም አሁን ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ዐማራውን ከውስጥ ሆኖ እያስጠቃና የዐማራን የነጻነት ዐውደ ግንባር በአንድ ቁጥር ጨምሮ ሀገራችንን እያወደመ ያለው ብአዴን ነው፡፡ ይህ ድርጅት ከሁሉ አስቀድሞ መጥፋት ያለበት መሆኑን ላስምርበትና ወደሌላ የጠላት ጎራ ልለፍ፡፡

2. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን - ይህች ቤተ ክርስቲያናችን በመሠረቱ በብዙ ቁም ነገሮችና በሀገር ባለውታነት ትጠቀሳለች፡፡ እኔም ከዲቁና እስከ አርሶ ፈረስ አወዳሽነት አገልግያታለሁና ባውለታነቷን አልረሳም፡፡ አሁንም በርሷው ሥር ነኝ - አማራጭ በማጣት ጭምር፡፡ እንጂ የዚህች ተቋም በደል ተነገሮም ሆነ ተዘርዝሮ አያልቅም፡፡ የሚታወቅን መናገር ኃጢኣትም ነውርም አይደለምና እባካችሁን ልደመጥ፡፡ ዝም ብሎ የሚያወግዝ - ሳይገባው የሚቃወም - ብልኅነቱን አልገለጠም፡፡

2.1 ከግብጽ እንደመጣ በሚነገር የበዓል አከባበር የወሩ 30 ቀናት ሁሉምና እንዲያውም በድራቦሽ የሚከበሩ በዓላትን በመደረት ሕዝቡ ሰነፍ እንዲሆን አድርጋለች፡፡ እግዚአብሔር “በላባችሁና በወዛችሁ ለፍታችሁ ደክማችሁ ብሉ፤ ጠጡም” ያለውን ህግ ወደጎን በመተው በሕዝብ ላይ ብዙ የስንፍናና የሥራ ማቆም አድማ እንዲሰፍን ተደርጓል፡፡ በዚህም ምክንያት ከወር እወር በማያቋርጡ የበዓላት ጋጋታዎች ርሀብና ችግር እንዳይለቀን ከመደረጉም በተጨማሪ ህገ እግዚአብሔርን ጥሰናል፡፡ ምዕመናንን በረጃጅም የጸሎት መርሐ ግብሮች ሌት ተቀን እያደከምን እንቅልፋምነትን አበረታትተናል፡፡ አላስፈላጊ ድግሶችንና የፍትሃት ሥነ ሥርዓቶችን በመተግበር ዜጎችን አደኽይተናል፡፡ ሁሉን ነገር በአንተ ታውቃለህ ለፈጣሪ እየሰጠን ከእኛ የሚጠበቀውን ልፋትና ጥረት እንድንቀንስ ተገደናል፡፡ ….

2.2 በአምልኮት ደረጃ ካየን ብዙ ህፀፆችን መንቀስ ይቻላል፡፡ መነሻችንም መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ራሷን ከሀዲስ ኪዳን ጋር ማስተካከል አቅቷት ወይም ለማስተካከል ባለመፈለግ በብሉይ ኪዳን ብቻ እየተጓዘች ሕዝቡን አደንቁራና ከእውነተኛው አምልኮ እንዲያፈነግጥ በማድረግ ኮድኩዳ አስቀምጣዋለች፡፡ በዚያም ምክንያት ራሷ ተፈረካክሳ ለሌሎች መጤ ሃይማኖቶች ዋና መጋቢ ሆነ ትገኛለች፡፡ የርሷን ዶግማ የሚቃወም ሁሉ እንደጴንጤ ወይም እንደመናፍቅ እየተቆጠረ በዐውደ ምሕረት ላይ ስለሚሰደብና ስለሚሳቀቅ በርካታው ሊቅ በየቤቱ ቀርቷል ወይንም ቀልቡ ወዳልፈለገው ሌላ ቤተ እምነት እየሄደ የሌላ ቀማኛ ቡድን አድማቂ ሆኗል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ግትር ባትሆንና ለውጥና ዕድሳት ቢያውቃት ኖሮ፣ ሰዎቿም ከምዕመኑ የበለጡ አንባቢና ተመራማሪ ቢሆኑ ኖሮ፣ ከተራ አቡነ ዘበሰማያትና “ይምሃረነ ይሰሃለነ…”  ባለፈ ቀሳውስቷ በሃይማኖቱ ገፋ ያለ ዕውቀትና ግንዛቤ ቢኖራቸው ኖሮ፣ የኦሪትን ብቻ ሣይሆን የሀዲሳት መጻሕፍትን የኢየሱስ ክርስቶስ አስተምህሮዎች ብንከተል ኖሮ ….ይሄኔ ቤተ ክርስቲያናችን ኅልውናዋን የሚፈታተን ነገር ውስጥ ባልገባች ነበር፡፡ ምዕመናን ጠያቂ አእምሮ አላቸው - የሚያድግ የሚመነደግ አንጎልም አላቸው፡፡ ያን የሚመጥን የሃይማኖት አመራርና አገልጋይ ደግሞ ያስፈልጋል - ዘመናዊ ማኅበረሰብን ባረጀ ባፈጀ ሥርዓተ ቀኖና ለማገልገል መሞከር ውኃ መውቀጥ ነው፤ አይሆንም፡፡ ሕዝብ ይጠይቃል፡፡ በዱሮው በሬ እያረሱ፣ ፈታኝ ጥያቄዎችን ሲጠየቁ ደግሞ በ“ትቀሰፋለህ!” ጥንታዊ የሞኝ ፈሊጥ እያስፈራሩ በልብሰ ተክህኖ በተጀቦነ አላዋቂነት ማገልገል ሃይማኖትን ለማጥፋት ካልሆነ ለማልማት እንደማይጠቅም ካህኖቻችን ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ ይህን የምለው የሚሉትን የማይሆኑ ጳጳሣትንና ቀሳውስትን ውስጣዊ ችግር እዚህ ላይ መጥቀስ ባለመፈለግ ነው፡፡ እንጂ ወደዝርዝሩ ብገባ ጨዋው ከሊቅ ተብዬው የሚበልጥባቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ፖለቲካና ቤተ እምነት በተስተካከለ የማጭበርበርና የማስመሰል ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ማሳየት ይቻላል፡፡ ይቅር ይበለን፡፡

2.3 ቤተ ክርስቲያን ለእግዚአብሔር ሳይሆን ለገንዘብ ካደረች ቆየች፡፡ በቤተ ክርስቲያን ገንዘብ አፍ አውጥቶ ይናገራል፤ እግር አውጥቶም ይራመዳል፡፡ በገንዘብ የሚጸደቅ ይመስል ስብከቱም ዐውደ ምሕረቱም ብዙ ጊዜያቸውን የሚያባክኑት ስለገንዘብ በማውራት ነው - ያቺን የፈረደባትን ከመቀነቷ ያላትን አውጥታ የሰጠች የመጽሐፍ ቅዱስ ባልቴት በመጥቀስ፡፡ ካህኑም ሆነ ደብተራው በገንዘብ ፍቅር ተጠምዶ ቃለ እግዚአብሔርን ዘንግቷል፡፡ በየቦታው የሚተከሉ ቤተ ክርስቲያናት ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ነው፡፡ “ሕዝቡ የትኛውን ጽላት ይፈልጋል?” ተብሎ የሚተከል ቤተ ክርስቲያን ምን ዓይነት ጽድቅ እንደሚኖረው እግዜር ይወቅ፡፡ አንድ አካባቢ ለምሣሌ የቅዱስ ገብርኤል ጽላት ሊገባ ቢል በአካባቢው የሚገኝ የሌላ የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ይከለክላል፡፡ ምክንያቱ ሲጠየቅ “ሕዝብን ይወስድብናል” ነው፡፡ በዚህና በመሰል ርዕሰ ጉዳዮች የምንሰማው ሁሉ ይሰቀጥጣል - የካህናቱንና የአድባራቱን በጠብ መናከስ፣ የደባትሩን የድግምትና የአስማት ቱማታና የደብር አለቆችን የሙስና ባህርና ውቅያኖስ ትተነው ሊያውም፡፡ ሠጋር በቅሎና አምባላይ ፈረስ በነበሩበት ዘመን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በውርንጭላ አህያ የሄደው ለዛሬዎቹ ካህናትና ጳጳሣት በቪ8 እና በፕራዶ መሄድ ሃይማኖታዊ ጽድቅን እንደሚያስገኝ(ላቸው) ለማስገንዘብ አልነበረም፡፡ የኞቹ አባቶች ብዙዎቹ አልታደሉም፡፡ ያሳዝናሉ፡፡ አንድ እንኳን ጴጥሮስን ፈልጌ በመሃላቸው አጣሁባቸው፤ አንድ እንኳን ጳውሎስን ዳስሼ አጠገባቸው አላገኘሁም፡፡ እምነት በገንዘብ ከተለወጠ አዲዮስ ፈጣሪ፡፡ በዚህ ረገድ ተበለሻሽተናል፡፡ በዚህ በዚህ ሁኔታችን ጴንጤ ጥርሱን ተነቅሶ ቢስቅብን መብቱ ነው፡፡ ሃይማኖት ሸቀጥ ከሆነ የለየላቸው ኢአማኒያን (ኤቲስቶች) ይሻላሉ፡፡ ኤቲይስት ሁኑ እያልኩ ግን አይደለም፡፡ የእግዚአብሔርን መንገድ አስተካክለን እንያዝ፤ አለበለዚያ ተሳስተን እናሳስታለንና የሥራ መስክ እንቀይር ማለቴ ነው፡፡ አሁን ያለነው ደግሞ በቸርነቱ ብዛት እንጂ በቤተ እምነቶቻችን ጥረትና ፆም ጸሎት አይደለም፡፡ እንዲያ ቢሆን ኖሮ በየቀኑ የዐማራን ደም ካልጠጣ በሕይወት የሚቆይ የማይመስለው ጭራቅ (ቫምፓየር) ጠ/ሚኒስትር አይኖረንም ነበር፡፡ መጽሐፉ አስቀድሞ “ሁሉም በኃጢኣት ሥር ወድቋልና አንድስ እንኳ ፃዲቅ የለም” ስለሚል ይህ ዓይነቱ ክስተት ለኔ ምንም ማለት አይደለም - ሀገርን እያጠፋ መሆኑ ግና ይሰመርበት፡፡ ይህ ሁሉ ነውረኝነት የመጨረሻው ዘመን ምልክት ነው፤ በዘመኑም ውስጥ እንገኛለንና ብዙ አንደናገጥ፡፡ ይልቁንስ ራሳችንን በቶሎ እንፈትሽና ወደ ደገኛይቱ መንገድ እንመለስ፡፡

2.4 ጽላትን በተመለከተ ብዙ ገፍቼ አልናገርም፡፡ ነገር ግን ይታሰብበት፡፡ ትምህርተ ክርስቶስን እናስታውስ፡፡ ሕዝብን አደንቁረን አንያዘው፡፡ ስግደትን ለፈጣሪ ብቻ እንዲያደርግ ሕዝብን እናስተምር፡፡ ከመጽሐፍ ቃል አናፈንግጥ፡፡ ከሃይማኖታዊ ባህልና ልማድ ፈጥነን እንውጣ፡፡ በጸሎት እርዝመትም የሚገኝ ጽድቅ እንደሌለ ከኢየሱስ ክርስቶስ አስተምህሮ እንማር፡፡ አሁን ክርስቶስ ቢመጣ በምድር ሳለ “የአባቴን ቤት መሸቀጫ አደረጋችሁት” በማለት ቤተ ክርስቲያንን በካልቾ ብሎ ሁሉን ነገር እንደበታተነው የኛንም አብያተ ክርስቲያን በመነቃቀራቸውና ጉዳችንን አደባባይ አውጥቶ ባሰጣው ነበር፡፡ በዚህ ነጥብ ዙሪያ ብዙ ገባ እንዳላልኩ ይታወቅልኝ፡፡ ቤቴን ሰድቤ ለሰዳቢ አልሰጥም፡፡ ግን ውስጣችንን እንመርምር፡፡ የሰው መሣቂያም አንሁን፡፡ ከእውነተኛው መንገድ በእጅጉ መውጣታችንን እንረዳ፡፡

3. ሕወሓት - ሕወሓት አብዛኛውን የትግራይ ሕዝብ በመርዘኛ ፕሮፓጋንዳ ጠልፋ ፀረ ዐማራ አድርጋዋለች፡፡ በዚያም ምክንያት ለዐማራ አንዱና ትልቁ ተግዳሮት ከትግራይ ምድር ይፈልቃል፡፡ እነዚህ አንድ ሊሆኑ የሚገባቸው ሁለት ማኅበረሰቦች ዕርቅ ቢያወርዱ ግን ማንም አይፈነጥዝባቸውም ነበር፡፡ የሀገራችንም ችግር በቀናትና በወራት ውስጥ በተፈታ፡፡ ይህ ደግሞ የጊዜ ጉዳይ እንጂ አይቀርም፡፡ ነቀርሣ ነቀርሣው ይቆረጥና ሣምራውያን ዐማሮችና ተጋሩ ወደፊት ከሌሎች ደጋግ ዜጎች ጋር በመቀናጀት  የዚህችን ሀገር መፃዒ ዕድል ያሳምሩታል፡፡ አሁን ግን እውነቱ ሌላ ነው፡፡ አንድዬ ይማረን፡፡

4. ሻዕቢያ - ዐማራ ጠሉ ኢሳይያስ በሰጠን የመቶ ዓመት የቤት ሥራ ውስጥ እንደምንገኝ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ኦነግ ወለዱ ጭራቅ ጠ/ሚኒስትርም ለአያቱ ሻዕቢያ አድሮ ኢትዮጵያን በሻዕቢያ ወሮበሎች እያስፈነጨባት ነው - የትግሬና የዐማራ በሤራ ፖለቲካ መፋጀት ለሻዕቢያና መሰል የሀገራችን ጠላቶች ሠርግና ምላሽ ሆኖላቸዋል፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ የነፃነት ትግል ከሻዕቢያም ጋር ነውና እንዘጋጅ፡፡  ድራማዎቹን ተዋቸው፡፡ ጭራቁ አቢይም ሆነ ኢሳይያስ በድራማ የሰለጠኑ፣ እውነተኛ ተፈጥሯቸውን ግን በምንም መንገድ የማይቀይሩ እባቦች ናቸውና በትያትር አትጠለፉ፡፡ እውነቱን ተገንዝባችሁ ለማይቀረው አርማጌዴዖን ተዘጋጁ፡፡ የአርማጌዴዖን ሰዓት ቀርባለች - በየበራችንም ደርሳለች፡፡ ወለጋ ጊምቢ ቶሌ ቀበሌና አጣዬ ተወስና የምትቀር ከመሰለህ ክፉኛ ተጃጅለሃልና ከጮቤ ረገጣህ ተመለስ፡፡

5. ኦነግ - ኦህዲድ - ኦሮሙማ፡፡ አንድም ብዙም የሚመስሉት የኦሮሙማ ቤተሰቦች ቀላል እንዳይመስሏችሁ፡፡ በ27 ዓመት የሰለጠኑትን ዐማራን የማረድ “ጥበብ” በአራት ዓመታት ውስጥ እንዴት እያቀላጠፉት እንደሆነ ታውቃላችሁ፡፡ የሥልጠናቸው ግዝፈት ደግሞ ቦርቀው ያልጠገቡት አቢይና ሽመልስ በዚህ ለጋ ዕድሜያቸው ስንቱን ዶክተርና ፕሮፌሰር ነኝ ባይ ሁላ በንክኪ በሚተላለፍ አፍዝ አደንግዛቸው እያነሆለሉና በግሩም ንግግር እያማለሉ ከጎናቸው ማቆማቸው ዋና ምሥክር ነው፡፡ አሁን ድረስ ለነሱ የሚንሰፈሰፍ ዐማራና የሌላ ነገድ አባል ሞልቷል፡፡ በቀደምለት ወለጋ ላይ ከ3000 የማያንስ ዐማራ በኦነግ-ሸኔ ጦር ተከብቦ እንደዐይጥ ሲጨፈጨፍና ለዚያም ዕውቅና በመንፈግ የኅሊና ጸሎትም እንደብርቅ ተቆጥሮ ሲከለከል እያዩ “ዐቢይ ብቻውን ምን ያድርግ? ከሥሩ ያሉት እኮ ናቸው ሥራውን የሚያበላሹበት …” የሚሉ አሽቃባጭ-አሸርጋጆችን ማየት ከዐቢይ ሰይጣናዊ ዕኩይ ድርጊት ይበልጥ ያሳምመናል፡፡ ጊዜያቸው ነው ብለን ግን ተቀምጠናል - ፍርዱን ለፈራጁ ሰጥተን፡፡ እንጂ አያያዛቸው ሁላችንንም ሳይፈጁ አካላዊም ሆነ ኅሊናዊ ዕረፍት የሚያገኙ አይመስሉም፡፡ ለማንኛውም ይህም አንዱና ትልቁ ዐውደ ግንባር ነውና ይታሰብበት፡፡ ከታሰበበት ቀላል ነው፡፡ አለማሰባችን ነው ችግሩ - ዝምታችን፡፡

6. ግብጽና ልጆቿ፡፡ ይህም የታወቀ ነውና ዝርዝሩ አያስፈልግም፡፡ የግብጽ እጅ በጣም ረጂም ነው፡፡ ወጥነት ያለው አቋም የሌላቸውን ሱዳንን የመሰሉ ሀገራትን እንደልቧ የምታዘውና ከአሜሪካ ዓመታዊ የበጀት ድጋፍ የሚደረግላት ይህች የመርገምት ፍሬ ግብጽ ለኢትዮጵያ ተኝታ አታውቅም፤ ወደፊትም ቢሆን መቼም አትተኛልንም፡፡ ኢትዮጵያውያንን በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች በመግዛት ከመከፋፈሏ በተጨማሪ በሱዳኖችና በሌሎች ሀገራት በኩልም የምትከፍትብን ጦርነት በቀላሉ የሚታይ አይደለምና ጠንቀቅ ነው ደጉ፡፡ የዐዋጁን በጀሮ አትሉኝም መቼም፡፡ ለማስታወስ ያህል ብቻ ነው፡፡

7. ምዕራባውያን - በአሜሪካን መንግሥት የሚመራው ይህ ኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠረ ዐውደ ውጊያ እጅግ ከባድ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያና አሜሪካ ማለት ጎልያድና ዳዊት እንደማለት ነው በመሠረቱ፡፡ በዚያ ላይ በዚሁ ጎራ ውስጥ የምትገኝን እንግሊዝን የመሰለች ማሽንክ ሀገር በጠላትነት ይዘን ትግላችን ፈጣሪ ካልታከለበት አደጋ ውስጥ ነው፡፡ እርግጥ ነው ዳዊትን አንረሳም፡፡ ጦርነትን እግዚአብሔር ካልተዋጋ ወታደር በከንቱ ይደክማል፡፡ የሆኖ ሆኖ ይህ የምዕራቡ ዓለም የኢሉሚናቲዎች ስብስብ በሀገራችን ወቅታዊና መፃዒ ዕድል ላይ የሚኖረውን ተፅዕኖ ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ የጦር መሣሪያንና ሌላውን ሎጂስቲክስ ጨምሮ በገንዘብም በማቴሪያልም በሰው ኃይልም በሥልጠናም በመረጃም ጠላቶቻችንን እያስታጠቁ ስለሚያሰማሩብን ብፁዓን የሃይማኖት አባቶች ኖረውን በምህላና በፆም በሱባኤ ባንታገዝም ጸሎትን ጨምሮ ሁል-አቀፍ ዝግጅት ማድረግ አለብን፤ አለበለዚያ ትግላችን ረጂም ጊዜ ሊወስድ ይችላል፡፡ “ረጂም ጊዜ ሊወስድ ይችላል” ነው ያልኩት - ሌላ አላልኩም፤ አልልምም፡፡

8. የኑሮ ውድነቱ - ሆን ተብሎ በየቀኑ የሚያሻቅበው የኑሮ ውድነት ትልቅ ዐውደ ግንባር ነው፡፡ ሰዎች በኑሮ ውድነቱ እየተጠበሱ ነው፤ በርሀብ እያለቁ ነው፡፡ የብር አሥር ሽህና 20 ሽህ ደመወዝ ሊቋቋመው ያልቻለ የኑሮ ውድነት ገጥሞናል፡፡ የግል ህክምናውና ንግዱ እሳት ሆኗል፡፡ በእግርህ ወይ በመኪና ሮጠህ የገባህበት የግል ሆስፒታል በህክምና ስህተት ከገደለህ በኋላ ቤተሰቦችህን “ የታከመበትንና የዋለ ያደረበትን 700 ሽህ ብር ካልከፈላችሁ ሬሣችሁን አንሰጥም” ሲላቸው በተዓምር ብትሰማ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆንህ ይገለጥልሃል፤ ነጋዴውም የአንድ ሽህ ብሩን ዕቃ “20 ሽህ ብር ካልሸጥኩ ምኑን አተረፍኩ!” ብሎ ቡራ ከረዩ የሚለው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው - የጉዶች ሀገር፡፡ የአብዛኛው የመንግሥትና የግል ድርጅት ተቀጣሪ ደሞዝ ደግሞ ግፋ ቢል ሁለትና ሦስት ሽህ ነው - ይህ ማለት ደግሞ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ዘመን አንድ ብርና ሁለት ብር፣ የደርግ ዘመን ሃያና 30 ብር እንደማለት ነው፡፡ በ1969ዓ.ም በወር ስድስት ብር የነበረው የበየቀኑ አንድ ሊትር ግሩም የላም ወተት አሁን ጥራቱ የተጓደለ ዝንቅ ወተት በወር 2000 ብር ነው፡፡ ስድስት ብር ወደ 2000 ብር ማደጓን አስላና ሌላውንም ሁሉ በዚሁ ስሌት አስቡት - በ1957ዓ.ም በሰባትና በስምንት ብር ይገዛ የነበረው ሠንጋ በሬ አሁን ከ50 ሽህ ብር በታች አታገኘውም - በቅርቡ እኮ የደለበ በሬ በብር 250 ሽህ እንደተሰሸጠ ሰምተናል፡፡ የዐርባ ሣንቲም ምሥር ክክ 140 ብር መግባቷንም አትዘንጉ ታዲያ - የሃምሣ ሣንቲሙ የአፄው ዘመን የብሩንዶ ቁርጥ አሁን ከ1000 እስከ 1500 ብር መግባቱን ጭምር፡፡ አንድ ኪሎ ቡና ብር አምስት መቶን መታከኩንም አትርሱ፡፡ መብራት ኃይልም በበኩሉ ወብርቶ በወር ሃምሣና ስልሣ ብር እከፍል የነበርኩትን ሰውዬ አሁን ብር 2400 ገደማ ሰቅሎታል፡፡ ጉድ ነው ብቻ፡፡ የአምስት ብሩ አንድ ማዳበርያ ከሰል ብር 550 መሆኑን ደሞ ማንም እንዲያስታውሳችሁ አትጠብቁ፡፡ የአርባ ሣንቲሙ ቢራም በትንንሽ መሸታ ቤቶች ከ40 ብር በታች አታገኙትም፡፡ ይሄው ነው፡፡ ሰው እንዴት እየኖረ ነው ታዲያ ብለህ ብትጠይቀኝ መልስ የለኝም፤ ባጭሩ “በተዓምር እየኖርን ነው” ብልህ አታምነኝምና፡፡ ሲዖልም ገነትም ያሉት ሌላ ሥፍራ ሣይሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡ ኦሮሙማዎችና ጥገኞቻቸው ግን በዊስኪ ሲራጩና ልጆቻቸውን በዓመት 2 ሚሊዮን ብር ገደማ በሚከፈልባቸው አይሲኤስን በመሳሰሉ ትምህርት ቤቶች እንደሚያስተምሩ አውቃለሁ፡፡ የምትገርም ሀገር ከሚገርም በቁሙ የሞተ ሕዝብ ጋር፡፡ በነገራችን ላይ አሁን ቤት የሚሠራው፣ መሬት የሚቀማውና የሚዘርፈው፣ ሕንጻ የሚገነባው ኦሮሞነቱን ካለሀፍረት እስከጥግ እየተጠቀመበት ያለው የኦሮሙማ ደቀ መዝሙር እንጂ ሌላው ልትወድቅ የደረሰች ዛኒጋባውን እንኳን ማደስ አይችልም፡፡ ሁሉም የሥራ ዘርፍ፣ ሁሉም የሥልጣን ቦታ፣ ሁሉም የጥቅም ሸጥና ሰርጥ… የኦሮሞና በኦሮሞ የተያዘ ነው፡፡ ወያኔ-ትግሬዎችን የሚያስመሰግን ዘመን መጣና አረፈው፡፡ የሚመጣ ግን አይመስለኝም ነበረ፡፡ ግሩም ነው፤ ዕድሜ ሰጥቶት መጨረሻውን ያዬ፡፡ አይቀርም - የቆዬ ያያል፤ የኦነግ/ኦህዲድ/ብአዴን መጨረሻ ከወያኔ መጨረሻም ይብሳል፡፡ ግልጽ እኮ ነው!! በቃኝ፡፡

ETHIOPIAN SEMAY

Sunday, June 26, 2022

ለኢትዮ 360ው ኤርሚያስ ለገሠ አፍን መቆጠብ ያስፈልጋል! አዎ የኦሮሞ ሕዝብ አማራን በመገደልና በማባረር ተባበሪም ተጠያቂም ነው! ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 6/25/2022

 

ለኢትዮ 360ው ኤርሚያስ ለገሠ

አፍን መቆጠብ ያስፈልጋል!

አዎ የኦሮሞ ሕዝብ አማራን በመገደልና በማባረር ተባበሪም ተጠያቂም ነው!

ጌታቸው ረዳ

(Ethiopian Semay)

6/25/2022

“አገሬው ነው እጃችን እየያዘ ያስገደለን ያስበላን” ይላሉ ተጠቂዎቹ። እነሆ ማስረጃው! ቪዲዮውን ለማየት እዚህ ድረገጽ ላይ የተለጠፈውን ወደ ቀኝ የቪዲዮ ማከማቻ ያለውን ፎዶራ ይመልከቱ ወይንም የተያያዘ መስኮት በመክፈት ቪዲዮውን ይመልከቱ፡

ኢትዮ 360ው በጎንደር ... ወቅቱን የዋጀ ጥሪ!" Friday June 24, 2022 በሚል ርዕስ የተላለፈው የውይይት ርዕስ ላይ ኤርሚያስ ለገሰ እንዲህ ይላል፦

 “በተለይ በተለይ አማራ የሆናችሁ ሰዎች ብትጠነቀቁ ይሻልል! ሌለው ላይ ጀኖሳይድ እያወጃችሁ ነው! Sure አማራው ሲጨፈጨፍ ኦሮሞውም አብሮ ነው የተጨፈጨፈው፤ “ፓርቲን እና ሕዝብን ማስተሳሰር ነው። በጣም በጣም አደገኛ ነው። አንዳንዶቹ እሰማቸዋለሁ ፡የኦሮሞ ሕዝብ ፣…ሊያደርግ ነው..ይሉኛል” የኦሮሞ ሕዝብ አልገደለም!!” “ኦሮሞ ሕዝብ ገደለ ብየ የምናገርበት ሞራልም የለኝም” “እንደዚያ ከሆነ ብ አ ዴ ን ሲገድል አማራ ገደለ ልል ነው? “Yes ኦ ሕ ዴ ድ ኦሮሞ ናቸው ግን ኦሮሞ ሕዝብ ይወክላሉ ማለት ስሕተት ነው።ማን ጨፈጨፈ ለሚለው እኮ እያየን ነው ‘አብይ አሕመድ እኮ ነው እየጨፈጨፈ ያለው” ኢትዮጵያ ውስጥ ሕዝብ ለሕዝብ ቅራኔ ተፈጥሮ አያውቅም አብይ የፈጠረው ቅራኔ ነው”……….. ወዘተ እያለ አማራና ኦሮሞ የተዛባ ግንኙነት ኖሮ አያውቅም አሁን ነው አብይ የተዛባ ቁርሾ እየፈጠረ ያለው…….ወዘተ እያለ እሳት የጎረሰ ቁጣው በማስጠንቀቂያ “ብትጠነቀቁ ይሻልል” በማለት ይዘባበታል። በመጨረሻም አማራ እና ኦሮሞ ጥቅም መሃከል መቸውም የጥቅም ፍላጎት ተቃርኖ የለም። የሚገርም ደግሞ “በትግራይና በአማራ ሕዝብ መካከል የጥቅም ፍላጎት ተቃርኖ የለም”

 እያለ ቁጣውን በድንፋታ ሲቀጥል ያኔ ጣቢያውን መከታተል አላስችል ብሎኝ ዘጋሁት።ትችቱን ካደመጥኩ በላ ንዴትየን መቆጣጠር ስላልቻልኩ  የተቀረውን ውይይታቸው ምን እንዳሉ አላዳመጥኩም ዘግቼ መልስ ለመስጠጥ አመራሁ።

ኤርሚያስ

 ወደ መጨረሻ የሰጠውን  “በአማራ እና ኦሮሞ ጥቅም መሃከል መቸውም የጥቅም ፍላጎት ተቃርኖ የለም። በትግራይና በአማራ ሕዝብ መካከል የጥቅም ፍላጎት ተቃርኖ የለም”… በሚለው ላይ ልጀምርና “ብትጠነቀቁ ይሻልል” ወደ እሚለው ዛቻውን ልመለስ ነው።

 

እንዴት ሲሆን በአማራ እና ኦሮሞ ጥቅም መሃከል መቸውም የጥቅም ፍላጎት ተቃርኖ ፤ በትግራይና በአማራ ሕዝብ መካከል የጥቅም ፍላጎት ተቃርኖ የለም ማለት ይቻላል? ኦሮሞው 3/4ኛ የማይገባውን መሬት ነጥቆ (ዕድሜ ለወያኔ) ወደ ራሱ ባለቤትነት አድርጎ የኔ ነው ብሎ አማራውን ከቦታው እያስወጣ እየገደለ ነው (31 አመት)። ኬኛ የሚለው ፖለቲከኛው ጀመረው ሕዝቡ አክብሮ ተቀበለው። ላቲን ነው ፊደልህ ተባለ አርሱም አዎ ብሎ አክብሮ ይኸው መላቅጡ የማይታወቅ ለማንበብም እርስ በርሳቸው የማይደማመጡ Latine Spelling እየተጠቀሙ የራሳቸው አድርገውታል። የቋንቋ ተቃርኖ፤ የመሬት ይዞታ ተቃርኖ አለ። ሕዝብ ካልደገፈው ኦሮሞማው እንዴት ዕድሜ ኖሮት ከወጭ አገር እስከ ውስጥ አገር ደረስ በጥላቻ የታጠበ ማሕበረሰብ ሊወጣ ቻለ? ለማ መገርሳ ምን ብሎ ነገረን? ሕዝቡ ኢትዮጵያዊ  አይመስልም፤ በጭካኔ በጥላቻ በትምክሕት የተበከለ ነው። ከታች ማስረጃ አቀርባለሁ፡

ወያኔ የወልቃይትን ለም መሬት በጠምንጃ ነጥቆ አማራውን ሕዝብ ጨፍጭፎ ለወገኖቹ ትግሬዎች በሚሊዮኖች ሲያስፍርበት፤ “ትግሬዎች” መሬታችን ነው ብለው ሰፍረው ይኸየው እየተዋጉ ነው፡ አይደለም እንዴ?  የመሬት ይዞታ ተቃርኖ ካልሆነ ጦርነቱ እና ጭፍጨፋው የምን ተቃርኖ ነው ሊባል ነው?

ለማ መገርሰ እንዲህ ይላል። ከኤርሚያስ ለገሰ በተሻለ ለማ መገርሳ እውነታወን ግልጽ ያደረገልን እውነታውን እነሆ፤

“ የኢትዮጵያ ሕዝብ እውነቱን ማወቅ ይገባዋል፡ፍርሃት አለኝ! እዚህ አገር ውስጥ፤ ባሕር ደር ፤ አባ ገዳዎችን ይዤ የሄድኩት ለሴራ ለተንኮል ኣይደለም፡ ተውት ሌለውን ነገር! ስጋት አለኝ፤ ያውም የዚህ ሕዝብ መሪ ሆኜ እኔ ባለሁበት ዘመን ደም እንዲፈስ አልፈልግም። ታሪኬን ማቆሸሽ አልፈልግም፤ ፍርሃት ነበረኝ ፤ስጋት ነበረኝ። እዚህ አገር ውስጥ እስካፍንጫው ድረስ ጥላቻ ነበረ! ጥግ የደረሰ ጥላቻ! እነኚህ መፈናቀል ፤ ‘ምን አምንላቸው’ (ግድያ ማለቱ ነው ለማ) የምንላቸው ዝምብለው እኮ የመጡ አይደሉም። ለዘመናት በጠላቻ ላይ የጥላቻ “ድሪቶ” ስንምግበው የኖርነው ትውልድ ነው ይኼ ትውልድ። ጠላትህ፤ የገደለህ፤የበዘበዘህ ጡትህን የቆረጠ፤ዘርህን ያጠፋ፤እየተባለ የተሰበከ በዚህ እየተሞላ የኖረ  ትውልድ ነው፤ ይህ ትውልድ ። ተራ ድሃ ሰው እንኳ ተራ ድሃ እንኳ በሰውነቱ ሰው መሆኑን እስኪክድ ድረስ ‘ገዳይ አስገዳይ” ሆኖ እንዲታይ፤ ጠላት ሆኖ እንዲታይ ነው ሲጫንበት የኖሮው። ፍርሃት ነበረኝ፡ አምና በነበርንበት ዳመና ብንቀጥል ኖሮ እዚህ አገር ላይ ሊከሰት የሚኖሮው ጥጋት ቀላል አልነበረም። አውቀዋለሁ፤ አይቸዋለሁ። በተለይ በአማራ እና ኦሮሞ መካከል አንዱ ያንዱ ጠላት ሆኖ እንዲተያይ የተተከለው ተክል ቀላል አይደለም። መርዙ  ቀላል አይደለም፡ አኔ አሱ አስፈርቶኛል። አሳስቦኛል! ይኼ ጉዳይ መልኩን ካልቀየርን፤ ኢንቫይሮንመንቱን ካልቀየርን፤ እንደዋዛ የሺዎችን ህይወት ይጠፋ ነበር፡ ደም ይፈስ ነበር፤ ሌላ ሩዋንዳ እዚህ ይከሰት ነበር! እኔ እሱ ነው ባሕርዳር ተሎ እንድሄድ የወሰደኝ ምንክያት።…” (የለማ መገርሳ ንግግር)

ሲል ከላይ የጠቀስኩትን የሕዝቡን የትውልዱን በጥላቻ መመረዝ በግልጽ የነገረንን አንባቢዎቼን ላስታውሳችሁ እፈልጋለሁ።

(የለማ “በሺዎች ይጠፋ ነበር” የሚለው “ነበር” የሚለው  ስሕተቱን ላርመውና ይኸየው ትናንት በሺዎች ኦሮሞ “አገር” ውስጥ ታርደዋል) አገራችን ወደ ሩዋንዳ የተለወጠቺው ኦሮሞ “አገር” ውስጥ ነው። አማራ ግን ለማ መገርሳ በሄደበት የባሕር ዳር ተማጽኖ አማራው ቃሉን አክብሮ አንድንም ኦሮሞ ሳይነካ በሰላም ኦሮሞዎች አማራ “ክልል” ውስጥ እየኖረ ነው። አማራው ኢትዮጵያም ሆነች “አማራ ክልል ኦሮሞዎችን እያረዱና እያባረሩ “ሩዋንዳ” ከመሆን አድነዋታል (አማራው እግዚሓር ይታደገውና እሱ እየታረደም ቢሆን ከጥላቻ የጸዳ ሰላሙን አያሳይቷቸዋል)። አማራ በነሱ ፈለግ ቢሄድ በእርግጠኛነት አገር ይፈርስ ነበር!

ስለዚህ ኦሮሞ ሕዝብ ስንል በኤርሚያስ የቁጥር ስሌት ስንት እንደሆነ ባይነግረንም፤ ለማ መገርሳ ግን አዲሱ ትውልድ በጥላቻ የታወረ በመርዝ ጥላቻ የሰከረ ፤አማራ የወላጆችህን ጡት ሲቆርጥ የነበረ ነው ብለን ሰብከነው ‘ተራ ድሃ አማራው እንኳ’ እንደ ‘ገዳይና አስገዳይ’ ሆኖ ባዲሱ የኦሮሞ ሕዝብ ትውልድ እንዲታይ ሆኗል፡ እያለ ለማ መገርሳ ስጋቱን የነገረን ዛሬ ኦሮሞዎች አማራን በማፈናቀልና በማረድ ኦሮሞ ምድር ልክ እንደ የ “ሁቱዎች” መንደር ሆና እንደ “ሩዋንዳ” ይኼው አማራዎች ወደ አገራችሁ ሂዱ እየተባሉ  በሺዎች እታረዱና እየተባረሩ ነው።

ኤርሚያስም ሆኑ ባልደረቦቹ የኦሮሞና ይትግሬ ፖለቲካና ፖሊሲ አያውቁትም ሆነው አይደለም። ይህ አጉል መለሳለስ የባሰውን ፖለቲካው እንዳይገለጥ እንዲደበቅ የሚረዳ ነው። ትግሬ ተጠቃሚ ነበር ስንል “አትበሉ ሲሉን ነበር” (ያንን በማስረጃ አቅርብን ሊያፈርሰው ማንም ሰው እስካሁን አላየሁም።) ፖለቲካቸው ኦሮሙማ ነው የትግሬውም ፋሺዝም ነው ብለናል።

ሁለቱ በናዚ እና ሙሶሊኒ ርዕዮት የሚመራ ከ40 አመት በላይ ያስቈጠረ ፖለቲካቸው ነው። የናዚ ፓርቲ፤ የፒፒ ኦነግ የወያነ፤የሻዕቢያ የአ ዴ ፓ በሕዝብ አልተወከሉም፤ ሆኖም በነዚህ ስብከት ሕዝቡ አሜን ብሎ ፖለቲካቸው ሰንደቃላማቸው አቅፎ ቋንቋቸው መፈክራቸው ትምህርታቸው፤ያነጋገር ዘይቤአቸው ተቀብሎ በዛው በቀየሱለት በመንገዳቸው ጎርፎ የተበከለ ማሕበረሰብ /ሕዝብ ሆኖ አሁን ያለበትን ሁኔታ ደርሷል።

ሙሶሎኒ በወቅቱ ሕዝቡን አስጨፍሯል፡ መጨረሻ ዘቅዝቀው ሰቀሉት; ሂትለር ጀርመንን አሳበደው (ጥቂት ተቃውሞ ቢሮውም)  መጨረሻ እራሱን ገደለ። ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራ ሕዝብን አሳበደው አስጨፈረው፤ ጨርቁን አስጥሎ ከቦ አስደለቀው፤ እስክስታው በየተራራው ምግብ እየቀረበ አንድ ወር ሙሉ ነፃነት መጣ ብሎ  ሙዚቃው በማይክሮፎን እየተስተጋባ በየመንደሩና አስመራ ጎዳናዎች ፤ እንዲሁም አስመራ ዙርያ ኮረብታዎች እስኪደነቁሩ ድረስ እረፍት አጥተው የዛፍ ቅጠሎች እየረገፉ እየተዋዛወዙ “ለረፍት ሲማጸኑ” ሕዝቡ  አብዶ ሲጨፍር አይተናል፤ መጨረሻ የሆነውን አየን።

 ኦሮሞዎችም ትግሬዎችም በጥላቻ የታጠበ ማሕበረሰብ እንደሆነ የሚከተሉትን የፖለቲካው አይነት ማየት ነው (ሁለቱ ማሕበረሶበች ባንድ ዘር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት የሚከተሉ ናቸው)። ከለማ መገርሳ ምስክርነት ሌላ የተያየዛው የተፈናቀሉ አማራዎች ምስክርነታቸው  በራሳቸው አንደበት ከኤርሚያስ እንዴት እንደሚለይ ማስረጃ ላቀርብ ነው ‘ወደ መጨረሻ’።

“በተለይ በተለይ አማራ የሆናችሁ ሰዎች ብትጠነቀቁ ይሻላል! የሚለው ኤርሚያስ የማደንቀውን ትንተናው ዛሬ ምን እንደደገጠመው አላወቅኩም። አሮሞው አማራ ክልል መብቱ ተጠብቆለት እየኖረ ነው፤ ይባስ ብሎ በገዛ ክልሉ ኦሮሞዎች የአጣየን እና የመሳሰሉትን ከተሞች እንዲቃጠሉ ያደረጉት እራሳቸው የክልሉ ኗሪዎች የሆኑት ኦሮሞዎች ናቸው (ቪዲየዎች ምስክር አለን)። ስለዚህ አማራው ኦሮሞ በጎንደርም ፤በጎጃምም፤ በወሎም በሸዋም በሰላም እየኖረ ነው። ይሉቁኑ “በተለይ በተለይ ኦሮሞዎች የሆናችሁ ሰዎች ብትጠነቀቁ ይሻልል!” ብለህ ማስጠንቀቂያህን ኦሮዎቹን ዘንድ ላክ።

“በተለይ በተለይ አማራ የሆናችሁ ሰዎች ብትጠነቀቁ ይሻልል! ሌለው ላይ ጀኖሳይድ እያወጃችሁ ነው! Sure አማራው ሲጨፈጨፍ ኦሮሞውም አብሮ ነው የተጨፈጨፈው” ብሏል አርሚያስ።

መቸ ነው ደግሞ አማራ በተጨፈጨፈ ቁጥር ኦሮሞ የተጨፈጨፈው፤ ቁጥሩ ስንት ነው፡ አብይ የነገረህን ኦሮሞ በብዛት ሞተ ያለውን ነው? ጀርመኖች እኮ አይሁድ ጀርመናዊ ነው አይገደል ብለው ስለተናገሩ በሂትለር ናዚ ተገድለዋል። ምን አዲስ ነገር አለ!? ቤትም መልካም ሰው አይታጣም፤ ተፈጥሮ ነው! አነጋጋሪ የሆነው የደጋፊውና የዝምታው ብዛት ሰንት ነው? ነው አነጋጋሪው ጥያቄ!

እስኪ በመጨረሻ በዚህ በለጠፍኩት ቪዲዮ “አገሬው ነው እጃችን እየያዘ ያስገደለን ያስበላን” ብለው የነገሩን የተባረሩት እና በቆጨራ አንገታቸው ተወግተው ደማቸው በወጊዎች “ሲጠጣ” ያዩ  የአማራ ተፈናቃዮች ምን እንደሚሉ አንባቢም ኤርሚያሰም ፍረዱ።

ይሕ  ቪዲዮ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በተሻለ በግልጽ የሚናገሩ በርካታ ተፈናቃዮች የኦሮሞ ሕዝብ ከገዳየቹ ጋር አብሮ የጨፈጨፈን ሕዝቡ ነው የሚሉ ማስረጃዎች በተከታታይ አቀርባለሁ።

“አገሬው ነው እጃችን እየያዘ ያስገደለን ያስበላን” ይላሉ ተጠቂዎቹ። እነሆ ማስረጃው! ቪዲዮውን ለማየት እዚህ ድረገጽ ላይ የተለጠፈውን ወደ ቀኝ የቪዲዮ ማከማቻ ያለውን ፎዶራ ይመልከቱ ወይንም የተያያዘ መስኮት በመክፈት ቪዲዮውን ይመልከቱ፡

ሕዝብ እንደ ሕዝብ በጅምላ በፖለቲካ ተብክሎ ያብዳል፤ ወንጀል ውስጥ እጁን ያስገባል (ሩዋንዳ ውስጥ አይተናል፤ ጀርመን እና የሌሎች ሕዝቦች የጋራ ዕብደት አይተናል.. ሕዝብ ወረበላ መሪዎችን በመከተል ጥፋት ውስጥ ይገባል፤ ካጠፋም ይወቀሳል!!ሕዝብ አይወቀስም አያጠፋም የሚል ብሂል በኔ ዘንድ ቦታ የለውም!!)። እንደ ትግሬነቴ ለእውነት ስል ብዙ ዋጋ ከፍያለሁ፤ትናንትም ዛሬም ለወደፊትም እውነት ምርኩዜ ናት።

Amhara Genocide by the Oromo Testimony of victims interview Cannibalism involved in the attack አገሬው

https://youtu.be/Eh7h0YgsZp0

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

Friday, June 24, 2022

ይቺ ያንድ ደቂቃ የኅሊና ጸሎት ዋጋዋ ስንት ቢሆን ነው ፓርላማው የቆጠባት? ዳግማዊ ጉዱ ካሣ Ethiopian Semay 6/24/22

 

ይቺ ያንድ ደቂቃ የኅሊና ጸሎት ዋጋዋ ስንት ቢሆን ነው ፓርላማው የቆጠባት?

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Ethiopian Semay 

6/24/22

ጆሮ ፀጥታን፣ አንደበትም ዝምታን አይወዱምና ስለሀገራችን ጥቂት እናውራ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ከመሆን የሚያግደው ነገር ባይኖርም በወቅዊ ጉዳዮች ዙሪያ ትንሽ መብሰክሰካችንን እንቀጥል፡፡ ለነገሩ ተስፋ በመቁረጥም ይሁን በሌላ ምክንያት በጣም ብዙው ሰው ስለሀገሩ መከታተልን ጅባት ብሎ የተወ ይመስለኛል፡፡ ሁኔታው ያስፈራል፤ ስለኛ ካለኛ ማን ሊጮህልንና ሊደርስልን እንደሚችል አላውቅም፡፡ ዝምታችን አስደንጋጭ ነው፡፡ የግዴለሽነታችን መጠን ለኅልውናችን መቀጠል ራሱ አሳሳቢ ነው፡፡ ለማንኛውም ጥቂቶችም ብንሆን ተስፋችንን በአንድዬ ላይ የጣልን ዜጎች አንዴውኑ ፈርዶብናልና እስካሁን ጩኸታችንን አልተውንም፤ ወደፊትም አንተውም፡፡ አንባቢና አድማጭም ቢጠፋ ለታሪክ ፍጆታ በየደረጃው ተሰንዶ የሚቀመጥ በመሆኑ ስለምናየውና ስለምንሰማው ግፍና በደል እንጮሃለን፡፡

የሀገራችን ጉዳይ ከድጡ ወደማጡ እየገባ ስለመሆኑ በየቀኑ ከምንሰማቸው ጉድ የሚያሰኙ ገጠመኞች መረዳት እንችላለን፡፡ ኢትዮጵያ በምን መሰል እጆች ውስጥ እንደገባች ልናምነው በሚቸግረን ሁኔታ እያየን ነው፡፡ “በጌታዋ የተማመነች በግ ላቷን ውጭ ታሳድራለች” እንዲሉ ሆኖ ሰሞኑን የአቢይ ፓርላማ ተብዬ አፈ ጉባኤ ያደረገውን ስንሰማ ደግሞ በእጅጉ ተገርመናል፡፡ አብኖች ወለጋ ውስጥ ሰሞኑን በሸኔ ለተገደሉ በሽዎች የሚቆጠሩ ወገኖች የኅሊና ጸሎት እንዲደረግ ቢጠይቁ የገዳዩ አቢይ ዕንባ ጠባቂ የሆነው ወያላው ታገሰ ጫፎ በቁጣ እንደከለከለ ሰማን፡፡ አንዲት ደቂቃ የኅሊና ጸሎትም እንደቁም ነገር ተቆጥራ በዚያ መልክ በንዴት ጦፎ መከልከሉ በርግጥም “ስልብ አሽከር በጌታው ብልት መፎከሩ”ን አረጋገጠልን፡፡ “ያዝልቅለት፤ መጨረሻውንም ያሳምርለት”  ከማለት ውጪ ምን ሊባል ይችላል?

ይህ የኅሊና ጸሎት ክልከላ ብቻውን እጅግ ብዙ ነገሮችን ይናገራል፡፡ ሲጀመር የኅሊና ጸሎት ለማንም ሊከለከል የማይገባውና በፈጣሪ የሚያምን ሁሉ ለጠላቶቹም ሳይቀር የሚቸረው ምንም የማይከፈልበት ነገር ነው፡፡ “ነፍስ ይማር” ማለት ለጠላትም ለወዳጅም የሚባል ለነፍስ ድኅነት የሚሰነዘር ምኞት ነው፡፡ ነፍስ ይማር ተብሎ ስለተነገረም ነፍስ ይማራል ማለትም አይደለም - ቢማርም ያስደስታል እንጂ አያስቆጭም፡፡ ነፍስን የሚያስምረውና የሚያስኮንነው ሥራችን እንጂ የሰዎች ልመናና ጸሎት ብቻም አይመስለኝም፡፡ አንዲት ነፍስ ብትማርስ እስከዚህ አገር ትንዳለች እንዴ?

ታገሰ ጫፎ አቢይ ጌታውን ላለማስቀየም ሲል ወይንም ያስደሰተ መስሎት በማሙሽ አቢይ የሚመራው ፌዴራል መንግሥቱ ላስገደላቸው አማሮች የኅሊና ጸሎት ከለከለ፡፡ ይህ ደግሞ በየትኛውም ዓለም ያልታዬ የመጨረሻ ወራዳ እደግመዋለሁ ወደር የማይገኝለት ወራዳ ተግባር ነው፡፡ ከአንድ አገር መሪ እንዲህ ያለ አድልዖና ጭፍንነት አይጠበቅም፡፡ አንድን ትልቅ ሕዝብ ለማዋረድ የተሞከረበት ይህ ክልከላ ብቻውን ይህን መንግሥት በሌላ መንግሥት የሚተካ ነውረኛ ድርጊት ነው፡፡ አቢይ አህመድ በመሠረቱ የአማራን ሕዝብ ገድሎ ለመጨረስ እንደመነሳቱ ከሥሩ የኮለኮላቸው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሟሎች ሁሉ ፀረ አማራ ሊሆኑ መቻላቸው አይገርምም፡፡ ታገሰ ጫፎም በግልጽ ያስመሰከረው ይህንኑ ነው፡፡ ስለሆነም ከእንግዲህ ይህ ፓርላማም ሆነ የመንግሥት ሹመኞች ሁሉ አማራን እንደማይወክሉ መታወቅ አለበት፡፡ እንጂ ለይምሰልም እንኳን ቢሆን ለሁለት ሽህ ሟች አይደለም ለአንድም በግፍ ለተገደ ሰው የአንድ ደቂቃ የኅሊና ጸሎት ሲያንስ እንጂ አይበዛበትም፡፡ በሌሎች ሀገሮች እኮ እያየን ነው፡፡ ለምሣሌ በአሜሪካ ለጆርጅ ፍሎይድ የተደረገውን እናስታውሳለን፡፡ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ራሱ ተንበርክኮ አይደለም እንዴ እናቱን ይቅርታ የጠየቀው?27 ሚሊዮን ዶላርስ አይደለም እንዴ ለቤተሰቡ የተሠጠው? ታዲያ ለነዚህ ምስኪን አማሮችስ ቢያንስ ነፍሳቸውን ይማር ተብሎ የኅሊና ጸሎት ቢደረግ ክፋቱ ምንድን ነው? እስከዚህን ይሉኝታቢስ መሆንንስ ከየት ተማሩት? አበስኩ ገበርኩ!!

እንደውነቱ አብኖችን ሳይጨምር ራሱንና ጌታቸውን አቢይን ትዝብት ውስጥ ከመክተት ባለፈ ይህ የአቢይ አሻንጉሊቶች የሞሉበት ፓርላማ ጸሎት አደረገ አላደረገ የሚመጣ ለውጥ የለም፡፡ እንኳንስ የነሱ ጸሎት የበቁ አባቶች ዕጥረት ባጋጠመን በዚህ የኃጢኣትና የክፋት ዘመን የብዙዎቻችን ጸሎትና ምህላ ከዳመና በታች እየቀረ ችግሮቻችን ከመቀነስ ይልቅ እየከበዱና ይበልጥ እየተወሳሰቡ መጥተዋል፡፡ እንደጸሎቱማ ቢሆን ኖሮ በየአብያተ ክርስቲያን ቀን ከሌት የሚደረገው ሰዓታትና ማኅሌት እንዲሁም ቅዳሴና ሽብሽባ ከአንዲት ደቂቃ የኅሊና ጸሎት አይበልጥም ነበርን? በየመስጂዱ የሚደረገው ሶላትና ስግደትስ ከአንዲት ደቂቃ ጸሎት መብለጥ አቅቶት ነውን? ስለዚህ አቢይ ምንም ሳይቸግረው እንዲሁ ነው የደከመው፡፡ ለነገሩ እንኳንም የነሱ ጸሎት ለሟቾች ቀረባቸው፡፡ ምን ሊጠቅማቸው? ከወንጀለኞች ዋሻ የሚወጣ ጸሎት ለመብረቅ እንጂ ለጽድቅ አያበቃም፡፡ ከአቢያውያን የኅሊና ጸሎት ይልቅ በንጹሓን ደም የጨቀየው የተራሮችና የወንዞች ጩኸት የፈጣሪን ልብ ይበልጥ ያራራል፡፡ ከወንጀለኞቹ አብያውያን የማስመሰልና የታይታ የኅሊና ጸሎት ይልቅ የታራጆቹ ሕጻናት የዋይታ ልቅሶ በጽርሃ አርያም ዘንድ ቀጥተኛ ተቀባይነት አለው፡፡ ስለሆነም አቢይና ታገሰ ጫፎ ሰይጣናዊ ባህርያቸውን ገለጡ እንጂ፣ የክፉ ክፉ ጠባያቸውን አሳዩን እንጂ የከለከሉን ነገር የለም፡፡ መጥፎ ጠባይ ደግሞ ሳያስቀብር አይለቅምና እንዲሁ እንደተጃጃሉና ዓለምን እንዳሳቁ ቀናቸው ትደርሳለች፡፡

አማራም ሆነ ኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ያለው ሁሉ ከዚህ የክፋት ድርጊት ብዙ መማር ይገባዋል፡፡ ከኅሊና ጸሎት ያነሰ ዋጋ የማይጠይቅ ስጦታ የለም፡፡ ለዚህች ስጦታ ይህን ያህል ትዝብትንም ንቀው እንዲህ ከሆኑ አማራ ላይ ያላቸውን ጥላቻ በሚገባ መገንዘብ እንችላለን፡፡ ከዚህ አኳያ ለአማራ የሚመደብን በጀትና መሰል ቁሳዊና መዋቅራዊ ድልድል በተመለከተ አማራን እንዴት ሊበድሉበት እንደሚችሉ መገመት አይከብድም፡፡ አንዲት ደቂቃ የኅሊና ጸሎት የነፈጉትን ሕዝብ ለአንድ ከረጪት ማዳበሪያ አራትና አምስት ሽህ ብር ቢያስከፍሉት አይገርምም፡፡ እነሱ ጸልየው ገና ለገና ፈጣሪ ነፍሳቸውን ይምራል ብለው የፈሩት እነዚህ ጉዶች አንዲት ደቂቃ የኅሊና ጸሎት የከለከሉትን ሕዝብ ለወደፊቱ በያለበት እየሄዱ በጠራራ ጸሐይ እንደማይረሽኑት ማንም እርግጠኛ አይደለም ብቻ ሳይሆን ይህን ታሪካዊ ተልእኳቸውን በቅርቡ በሁሉም የአማራ አካባቢዎች ጭምር እንደሚያቀላጥፉ ከምልክት በዘለለ በተግባር እያየን ነው፡፡

ስለሆነም አማራው ላለመጥፋት ከፈለገ በተለይ በየከተማው “ያዝ እጇን፣ ዝጋ ደጇን” እያለ ዳንኪራ የሚረግጥ የአማራ ወጣት ሁሉ ጮቤ ረገጣውንና ሼሼ ገዳሜውን አቁሞ መታገል ይኖርበታል፡፡ የፋሲካው በግ በገናው በግ እየሳቀ ነገሮች በዚህ ከቀጠሉ ሁሉም አማራ ለማለቅ ጥቂት ወራት ብቻ ይበቃሉ፡፡ አንድ እረኛ አንድ ሽህ ከብቶችን እንደሚነዳ ሁሉ ሽመልስና አቢይ የሚመሯቸው ጥቂት ሸኔዎች ይህን ሁሉ ሚሊዮን አማራ ሁሉንም ግን በየተራ አርደው አይጨርሱም ብሎ ማሰብ የዋህነት ነውና አማራ በየተራ ላለማለቅ አሁኑኑ ይነሳ፡፡ ሌላው ይደረስበታል፡፡ ኅልውናን ማስጠበቅ ቅድሚያ ይሰጠው፡፡ ዛሬ ወለጋ ያለው ሸኔ በመንግሥት ሁለንተናዊ ድጋፍ ነገ ጧት ጎንደርንና ባህር ዳርን እንዲሁም ደሴንና ወልዲያን አያነድም ማለት አንችልም፡፡ አያያዛቸው ሲዖላዊ ይዘት ያለው ነውና አማራ በቶሎ ከእንቅልፉ ይንቃ፡፡ አማራ እያለቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሙዚቃ ከፍተው የሞንታርቮው ላንቃ እስኪበጠስ ድረስ እያስጮሁ የሚጨፍሩና የሚደንሱ አማሮች ደንቆሮ ናቸው፡፡ እውነቴን ነው እልም ያሉ ደናቁርት  ማይማን ናቸው፡፡ እንኳንስ አማራና ሰው ነኝ ብሎ የሚያስብ የሌላው ነገድ አባል ሁሉ እግዚኦ እያለ ወደላይ መጮህ ይገባዋል፤ የተላከብን የአጋንንት ኃይል ቀላል አይደለምና፡፡ ነገ ደግሞ ተረኛውን ሟች አናውቀውምና፡፡ ያም ከአሁኑ ያስጨንቃልና፡፡ እንዳለ የሚኖር ነገር መቼም የለም ወገኖቼ፡፡ እያየነው!! ስለዚህ ለራሳችን እንዘን፤ ለራሳችን እናልቅስ፡፡ ጊዜው ከፍቷል፡፡

አማራ “ለቤት ቀጋ ለውጭ አልጋ” ነው ከሚባለው ብሂል ራሱን አውጥቶ ለማይቀረው የኅልውና ዘመቻ ራሱን ያዘጋጅ፡፡ ብዙ ሆኖ ሳለ ለዚህ መከራ የተዳረገው ርስ በርስ መናበብ ባለመቻሉና ሁነኛ አመራር ባለማግኘቱ ነውና ከሰሞኑ የኦሮሙማ ዕኩይ ድርጊቶች በመማር ኅልውናውን ለማስጠበቅ ጥረት ያድርግ፤ አለበለዚያ “አማራ የሚባል ዘር በዚህች ኦሮምያ ግዛት ውስጥ ይኖር ነበር” ተብሎ በታሪክ ሊጻፍ የሚችልበት አጋጣሚ ከፊት ለፊታችን በአማራጭነት ተገትሮ በግልጽ እየታዬ ነው፡፡ “በጊዜ የጮኸ ጅብ አያሳድረኝም” ይባላልና ኦሮሙማ አማራን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ቀላል ትግል አይደለም የተያያዘው - የኅሊና ጸሎትን ከመከልከል ቀላል ነገር ጀምሮ በሁሉም አቅጣጫ ነው አማራን የወጠረው፡፡ አማራ በሰማይም እንዳይጸድቅ እኮ መሆኑ ነው! ምን የመሰለ ጅልነት ነው ግን ወንድሞቼ፡፡ ሰው አእምሮውን ሲስት ለካንስ እንዲህና እስከዚህም ይጃጃላል፡፡ በስማም!! “መጥኔ ለወለደሽ ያገባስ ይፈታሻል” አሉ እመት ዘለቃሽ፡፡ እውነታቸውን ነው፡፡ በሉ እየተገረማችሁ ሰንብቱልኝማ፡፡


Tuesday, June 21, 2022

አቢይና ሽመልስ ኦሮሞን በቁም እየገደሉት ናቸው!! ይነጋል በላቸው ETHIOPIAN SEMAY 6/21/22

 

አቢይና ሽመልስ ኦሮሞን በቁም እየገደሉት ናቸው!!

ይነጋል በላቸው

ETHIOPIAN SEMAY

6/21/22


የወጣትነት ዕድሜውን በማገባደድ ላይ የሚገኝ አንድ ተንከራታች ዜጋ ኑሮ ቢጠምበት፣ መልካም ዕድል ፊቷን ብታዞርበት ጊዜ ወደ አንድ ጠንቋይ ቤት ይሄዳል፡፡ እንደሄደም ወረፋውን ጠብቆ ተራው ሲደርስ እጠንቋዩ ፊት ይቆማል፡፡

ከዚያም ጠንቋዩ፤ “እህ፣ ምን ሆነህ መጣህ?” በማለት ይጠይቀዋል፡፡

እሱም፤ “ጌታየ! በርስዎ መጀን፤ ኑሮ ቢመረኝ፣ ቢያንገፈግፈኝ፣ ጓደኞቼ ደልቷቸው እኔ ብደኸይ አንዳች መላ ቢሹልኝ ብዬ ወደርስዎ መጣሁ፡፡” ብሎ ይመልስለታል፡፡

አያ ጠንቋዩም ቀጠለ፤ “ለመሆኑ ዕድሜህ ስንት ነው?”

አስጠንቋይ፤ “በመጪው ትሳስ 28 ዓመት ይሞላኛል፡፡”

ጠንቋይ፤ “አሃ! ጥሩ ነው፡፡ እንግዲያውስ ችግርህ 30 ዓመት እስኪሞላህ ነው፡፡ አይዞህ ወዳጃችን፡፡”

የቸገረው ሰው በተስፋ ሆዱን ለመቀብተት የሚቀድመው የለምና የጠንቋዩን ምላሽ ለማዳመጥ   ጆሮዎቹን በጉጉት ቀስሮ፤ “ከዚያስ በኋላ ጌታየ?” በማለት ይጠይቃል፡፡

“ከዚያ በኋላማ ትለምደዋለህ፡፡”

አዎ፣ የአማራና በአማራ ላይ የታወጀው የዘር ፍጂት ነገርም ልክ እንደዚሁ ነው፡፡ በዚያች ጠማማ ዓመት፣ በ1968 ትግራይ ውስጥ ደደቢት ላይ የተጻፈች “አማራንና ኦርቶዶክስን ከኢትዮጵያ ማጥፋት፤ አማራን በተለይ ማኅበራዊ ዕረፍት መንሳት” የምትል ወያኔያዊ ሰነድ ከተቀረጸችና ወደተግባር ከተለወጠች ወዲህ ይሄውና አማራ እስከዛሬዋ መዓልትና እስካሁኒቷ ቅጽበት ድረስ ቁም ስቅሉን እያዬ ነው፡፡ አማራም ከአንድነቱ መለያየቱ፣ ከመግባባቱ መነቋቆሩ፣ ከመተዛዘኑና መተሳሰቡ መነካከሱና መቆራቆሱ የተስማማው ይመስላል በምልዓት ከማንም ሳያንስ ለጠላቶቹ ዒላማነት ምቹ ሆኖ በማለቅ ላይ ይገኛል፡፡ እናም ላለፉት 31 ዓመታት በተለይ ደግሞ ካለፉት 4 የጥልቅ መከራ ኦሮሙማዊ አገዛዝ ወዲህ እየደረሰበት የሚገኘውን የስቃይ ዶፍ ለምዶት እንደቤቶች ድራማ ገጸ ባሕርይ እንደሙሽራው እከ ለሽ ብሎ ተኝቷል፡፡

ከአርባ ጉጉ እስከ ጉራ ፈርዳ፣ ከአሰቦት እስከ በደኖ፣ ከገለምሶ እስከ ሻሸመኔ፣ ከደምቢ ዶሎ እስከ አጣዬ፣ ከከሚሴ እስከ ጊምቢ፣ ከአሶሳ እስከ ጋምቤላ …. በመላዋ ኢትዮጵያ በየቀኑ ስለሚገደለው አማራና ሌላው ኢትዮጵያዊ ለመናገር አይደለም አነሳሴ፡፡ አንድ ችግር ተደጋግሞ ሲነገርና ሲጻፍ እውነትም ይለመዳል፡፡ የሚለመድ ነገር ደግሞ ደስታም ሆነ ሀዘን ተራ ነገር ይሆንና ማስደሰቱም ማስደንገጡና ማሳዘኑም የማይሰማን ስሜት አልባ ድንዙዛን እንሆናለን፡፡ ወደስሜት አልባነት ደረጃ የተለወጠ ግለሰብም ሆነ ማኅበረሰብ ለአደጋ የተጋለጠ ነው፡፡ ለምሣሌ በሌፕረሲ የተጠቃ ሰው በሽታው የነርቭ ሕዋሳቱን ስለሚያደነዝዛቸው ሰውዬው እሳት ቢፈጀው ወይንም ቢላዎ ቢቆርጠው ህመም አይሰማውም፡፡ በዚያም ምክንያት ሳይታወቀው ሁሉ ለከፋ አደጋ ይጋለጥና የሰውነት ክፍሉን ሊያጣ ይችላል፡፡

በነገርም ይሁን በመጠጥ የሰከረ ሰውም እንዲሁ በሌሎችም ሆነ በራሱ ላይ አደጋ የሚያስከትለውና የደረሰውንም አደጋ የማያስተውለው በዚህ ሳቢያ ነው፡፡ አማራም ወደዚህ ደረጃ የቀረበ ይመስለኛል፡፡ የኋላ ኋላ ከንቅልፉ መንቃቱና ለመብቱ መነሳቱ ታሪካዊ እውነታ ቢሆንም አሁን ያለበትን ተጨባጭ ሁኔታ በዚህ መልክ መግለጹ ነውር አይደለም፡፡

እናም አማራው ጥልቅ እንቅልፍ ላይ ይገኛል፡፡ ሰሞኑን - ሰኔ 11/2014 - በአቢይ አህመድና በሽመልስ አብዲሣ በሚመራው ኦነግ-ሸኔ የተባለ የነዚህ ልጆች ፍጡር ከሁለት ሽህ በላይ አማራ ወለጋ ውስጥ ባልተወለደ አንጀት ሲረፈረፍ አንድም ቦታ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ አልተደረገም፡፡ ይህ የሚያሳየን ከችግር ጋር መኖርን እንዴቱን ያህል እንደተላመድነው ነው፡፡ የሚገርም ድንዛዜ ነው፡፡

በአንድ የዘር ፍጂት ይህን ያህል ሕዝብ ከአንድ ነገድ ሲታጨድ ሁሉም ዝም ጭጭ ማለቱ በርግጥም በእጅጉ ያስደነግጣል፡፡ “አማራ ሰው አይደለም እንዴ?” የሚል ትልቅ ጥያቄም ያጭራል፡፡ ይሄኔ ከሌላ ነገድ አሥር ሰው ተገድሎ ቢሆን ለሦስት ቀናት ባንዲራ ዝቅ ተደርጎ ይውለበለብ፣ አቢይም በፓርላማና በኢቲቪ ወጥቶ ይቅለበለብ፣ ሚዲያዎችም ሁሉ አለልክ ይቅመደመዱ ነበር፡፡ አማራ ሲሞት ግን በተለይ አቢይና ጓደኞቹ ቤት ዘግተው ፌሽታ ሳያደርጉ አይቀሩም፡፡

 ይህ ዓይነቱ ደዌ የለከፈው ሰው ሀገርን እንዲያስተዳድር ዕድል ሲገጥመው ማየት ያሳዝናል፡፡ የአማራ ተወካይ ነኝ ባዩ ብአዴንም የሎሌነት ሚናውን በሚገባ እየተወጣ ነው፡፡ ለአማራ ደግሞ ዋናው ጠላት ኦነግ/ኦህዲድ ሳይሆን በስሙ የተመሠረተው ብአዴን ነው፡፡

አቢይና ሽመልስ የመጡበትን ዓላማ በፍጹም አይዘነጉም፡፡ እባብ የወጣበትን ጉድጓ እንደማይስት ሁሉ እነዚህ ብላቴናዎችም ያደጉበትንና የተመረዙበትን አማራን የማጥፋት ሤራ ለሰከንድም አይዘነጉም - እንጀራቸውም ነው - ነፍሳቸውን ረክዘው ከዐወሬው ጋር የተፈራረሙበት የሕይወታው ትልቁ የስኬት አጀንዳ ነው፡፡ ዓላማቸውን አለመርሳት ደግሞ የተልእኳቸው ዓይነተኛ ግብኣት ነው፡፡ ያም ዓላማ አሁን ብዙው ሰው እንደተረዳው አማራንና የሰሜኑን ሕዝብ በጥቅሉ ከምድረ ገጽ በማጥፋት ታላቋ ኦሮምያን መመሥረት ነው፡፡

ነገር ግን የተከበረው የኦሮሞ ሕዝብ በነዚህ የታሪክ ውርጃዎች ማፈርና ኦሮሞን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከእስካሁኑ በባሰ የጠቆረ ገጽ ሳያሰጡት በተቻለ ፍጥነት ማስወገድ እንደሚገባው መጠቆም እወዳለሁ፡፡ አቢይና ሽመልስ ያልታጠቁ አማሮችን፣ ሴቶችንና ገና ሦስት ቀንም ያልሆናቸው ሕጻናትን በጥይትና በሜንጫ ስለረፈረፉ ፍላጎቱ ምንም ይሁን ምን የኦሮሞ ፍላጎት አይሳካም፡፡ በአርባና በሃምሳ ሚሊዮን የሚገመተው የአማራ ሕዝብ ከምድረ ገጽ ጠፍቶ ኦሮሞ የሚያገኘው ነገር ምንም ይሁን ምን ሰፊውን የኦሮሞ ሕዝብ ሊያስደስተውና የኅሊና ሰላም ሊሰጠው አይችልም፡፡

 ኦሮሞ በአሜሪካና በአፍሪካ ሄዶ ሀብት ንብረት እያፈራና ባልተወለደበት የባዕድ ሀገር ለመንግሥት ሥልጣንም እየተወዳደረ ባለበት የ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አብሮ የኖረና የተዋለደ ሕዝብ ወዶና ፈቅዶ ባልተወለደበት የዘር ሐረግ ወይም ነገድ ምክንያት አንድን ሕዝብ በገዛ ሀገሩ መጨፍጨፍ የጤና አለመሆኑን በተለይ ኦሮሞው ተረድቶ ልጆቹን ሃይ ቢል የመጀመሪያው ተጠቃሚ ሌላ ሳይሆን ራሱ ነው፡፡ አዎ፣ በአማራ ዕልቂት ኦሮሞም ሆነ ሌላ ማንም ወገን አይጠቀምም ብቻ ሳይሆን የዞረ ድምር ሊኖረው እንደሚችል መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ እያስፈራራሁ አይደለም፡፡ ነገር እያባባሰኩም አይደለም፡፡ ግን ግን ፈጣሪ ሁል ጊዜ ከግፈኞች ጋር ሳይሆን ከተበዳዮች ጋር መሆኑን ከመገንዘብ አንጻር ስለነገው የሚታየኝን የነገሮች የመጨረሻ ዕጣ ፋንታ መጠቆሜ ነው፡፡

አክራሪ ኦሮሞዎችን አንድ ነገር ላስታውሳቸው እወዳለሁ፡፡ አሁን የምትጨፈጭፏቸው አማሮች ሰዎች እንጂ ጉንዳኖች ወይንም ዐይጦች አይደሉም፡፡ ሰዎች እንደመሆናቸው የሚፈሰው የእያንዳንዱ ንጹሕ ዜጋ ደም ወደፈጣሪ ይጮሃል፡፡ የውሻን ደም መና የማያስቀረው ፈጣሪ ደግሞ በደልን መካስን፣ ጥጋበኛን ማስታገስን አሳምሮ ያውቅበታል፡፡ ለዚህ ደግሞ የቅርቡን ሕወሓትን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡ የነሥዩም መስፍንን፣ የነአባይ ወልዱን፣ የነአባይ ፀሐይን፣ የነስብሃት ነጋን ዕብሪትና ጥጋብ በምን መልክ እንዳስተነፈሰ ከአቢይና ሽመልስ ወዲያ የሚያውቅ ላሣር ነው  - ከቡችላነታቸው ጀምሮ እዚያው ነበሩና፡፡

ስለሆነም ያዋጣናል ካላችሁ በመለሳዊ አገላለጽ መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ፡፡እናም በዘረኝነት ፕሮፓጋንዳ ያሰከራችኋቸውን ቄሮዎች አማራን እንዲያጠፉ በደምብ ንገሯቸው፤ ግድያውን አጧጡፉት፡፡ ቶሎ ቶሎ በሉና ታለቋን ኦሮምያ መሥርቱ፡፡ ሁሉንም አማራ በተቻለ መጠን በጥቂት ወራት ውስጥ ለመጨረስ በርቱ፡፡ ደም እንደጎርፍ ይሂድ፡፡ ካዋጣችሁ እንግዲህ በዚሁ ግፉበት፡፡

የአፄዎቹን ግፍ፣ የደርግን ሞገደኛነት፣ የወያኔን በደልና የመጨረሻ ፍርድ እንደታዘበ አንድ አንጋፋ ዜጋ የአቢይንና የሽመልስን ጥጋብ መጨረሻ መተንበይ ትልቅ ዕውቀትን አይጠይቅም፡፡ የዱባ ጥጋብ ጥቂት ሰዎችን ብቻ ቢጎዳ እሰዬው ነው፤ ነገር ግን የወያኔ ዕብሪትና ጥጋብ አንድ ክፍለ ሀገርን ያህል ነገር ለምናውቀው ጉዳት እንደዳረገ ለምንገነዘብ ወገኖች የኦህዲድ ድንቁርና ምን ሊያስከትል እንደሚችል በጣም ግልጽ ነውና የኦሮሞ ማኅበረሰብ ቆም ብሎ የሚያስብበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ በኋላ “አይቡን ሳያዩት አጓቱን ጨለጡት” እንዳይሆን ነገራችን ሁላ፡፡

በመጨረሻም አማራም ሆነ ትግሬ ወደወለጋና ሌሎች የኢትዮጵያ ግዛቶች የሄዱት ወደው ሳይሆን የደርግ መንግሥት በሠፈራ ፕሮግራም በግድ ወስዷቸው ነው፡፡ የያኔው መንግሥት ኢትዮጵያዊ ነበር፡፡ እንዲህ ያለ ኢትዮጵያን ባወጣች ሸጦ የሚበላ ጭራቅ መንግሥት እንደሚመጣ ያኔ ማንም ባለማወቁ ሠፈራውን በጥልቀት አልተቃወመም፡፡ ባዶና ጠፍ መሬት እየተፈለገ በድርቅ ከተጎዱ አካባቢዎች ሰዎችን በግድ በማፍለስ ወደነዚያ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ ተደረገ፡፡ ስለሆነም እዚያ ሥፍራ መገኘታው የነሱ ጥፋት አይደለም - ጥፋትም ከሆነ፡፡ የራሱን መጨረሻ ለማበላሸት ቆርጦ የተነሳው ኦሮሙማ መፃዒ ዕድሉን ለዘብ ለማድረግ ቢፈልግ ኖሮ ሰዎቹን መግደልና ንብረታቸውን መዝረፍ ወይም ማውደም ሳይሆን በሰላም እንዲለቁ በሩን ከፍቶና ቀነ ገደብ ወስኖ ማሰናበት ነበረበት፡፡ ይህ ዓይነቱ ከሰው ቀርቶ ከለዬለት ዐውሬም የማይጠበቅ ጭካኔና ዐረመኔነት ግን የሰውን ልጅ ተፈጥሮ ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው፡፡

 መሣሪያ ያልያዘን ሰው፣ ስለነገዳዊ ምንነቱ እንኳ የማያውቅን ሰው፣ በራሱ ላብና ወዝ ለፍቶ መሬት በምትሰጠው ፀጋ የሚኖርን ሰው፣ ከአካባቢው ባህልና ወግ ጋር ተላምዶ በመከባበርና እርስ በርስ በመዋለድ የሚኖርን ሰው፣ በሃይማኖትና በባህል ከቀደም ነዋሪዎች ጋር እምብዝም የማይለያይን ሰው፣ በመልክ በቁመት ወዘተ.  አንድ የሆን ሰው…. ያላንዳች ጥፋቱ አንገቱን መቅላት ከሰው ሳይሆን ከለየለት ሰይጣንም አይጠበቅምና ለጤናማ ኦሮሞ ወንድምና እህቶቼ ይህ መልእክቴ ይድረስልኝ፡፡ ከዘረኝነት አባዜ ወጥተንና ከስሜት አምባላይ ፈረስ ወርደን ይህን ነገር በጥሞና እናስተውለው፡፡ ማንም ቢሆን በነገዱና በጎሣው አይሰቃይ፡፡ ፈሪሃ እግዚአብሔርም ይኑረን፡፡ እርግጥ ነው - የሚገድል ሁሉ ማንም ይሁን ማን የእግዚአብሔር ወገን አይደለምና ለራሲ ሲል ይጠንቀቅ፤ ከሰፊው የሚያማልል መንገድም በአፋጣኝ ይውጣ፡፡

ETHIOPIAN SEMAY

Sunday, June 19, 2022

የኢትዮጵያ ወይንስ የኦሮምያ ንግድ ባንክ? የኦሮምያ ወይንስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ?... ዳግማዊ ጉዱ ካሣ ይድረስ ለ“ኢትዮጵያ” ንግድ ባንክ! Ethiopian Semay 6/19/22

 

የኢትዮጵያ ወይንስ የኦሮምያ ንግድ ባንክ?

የኦሮምያ ወይንስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ?...

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ይድረስ ለ“ኢትዮጵያ” ንግድ ባንክ!

Ethiopian Semay

6/19/22



የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፖለቲካ ሊገናኝ የማይገባው፣ ከዘረኝነትም ሊቆራኝ የማይጠበቅበት የሀገር የወል ሀብት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በወያኔ ዘመን እንኳን ይህ ሀገራዊ ይዘቱና አገልግሎቱ እምብዝም ሳይነካ ሊቀ ሣጥናኤል ጠቅልሎ ቤተ መንግሥታችንን እስከተቆጣጠረበት እስከ 2010ዓ.ም ድረስ ቆይቷል፡፡ ባንክ ሙያተኞችን እንጂ ዘረኛና ጎጠኛ የአእምሮ ድኩማንን አይፈልግም፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በነገድና በጎሣ ሊቀፈደድ የማይገባው ቢቻል እንዲያውም ዓለም አቀፍ ይዘት እንዲኖረው ቢደረግ የማይበዛበት ትልቅ ተቋም ነው፡፡

ኢትዮጵያም ሆነች ንብረቷ የ86 ነገዶች የጋራ ሀገርና ንብረት እንጂ የኦሮሞ ወይንም የሌላ ነገድ ብቸኛ አንጡራ ሀብት አይደለችም፡፡ ይህ ዓይነቱ የተሳሳት ሃሳብ ከወያኔ ጀምሮ አሁንም ድረስ በባሰ ሁኔታ የቀጠለ፣ ነገና ከነገ ወዲያ ግን በታሪክ አሳፋሪ የሆነና በዚህ ድራማ ውስጥ የገቡ ሁሉ አንገታቸውን የሚደፉበት ትውልድን አሸማቃቂ ድርጊት ነው፡፡ በአእምሮ ሳይሆን በተለጣጭ ላስቲክ ሆድ የሚነዱ ዜጎች ነገ መግቢያ ቀዳዳ ሲጠፋቸው መፈጠራቸውን እንደሚራገሙ ማወቅ አለባቸው፡፡ ከቻሉ  ዛሬና አሁን ብዙም ሳይረፍድባቸው ከስህተታቸው ይመለሱ፡፡ ካለፈ ታሪክም ይማሩ፡፡ ማንም እንደገነነ አይቆይምና፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በአሁኑ ወቅት ምንም ዕውቀትና ችሎታ ሳይኖራቸው በኦሮሙማ መልማይነት ከየገጠሩ የሚሰባሰቡ ያልሰለጠኑና ከኅብረተሰቡ ጋርም በቋንቋም ሆነ በማኅበራዊ ተግባቦት ድሃ የሆኑ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ሙሉ በሙሉ ሊባል ጥቂት በሚቀረው ደረጃ ተቆጣጥረውታል፡፡ በመሠረቱና እንደእውነቱም ከሆነ የባንክ አገልግሎት የገንዘብና ገንዘብ ነክ ዕውቀትን እንጂ ነገዳዊ ማንነትን አይሻም፡፡ የባንክ ሥራ ሙያዊ ብቃትን እንጂ በአንድ ቋንቋ ተናጋሪነት የሚሰባሰቡ ማይማን ሰገጤዎችን አይፈልግም፡፡ ከሞራልም ከሃይማኖታዊና ባህላዊ ዕሤትም ያፈነገጡ ቁጡ ኦሮሞዎች የወረሩት የገንዘብ ተቋም ኪሣራ እንጂ ትርፍ እንደማይጠበቅበት ደግሞ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ዘረኝነት የተጣባው እልህ የትም አያደርስም፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚታየው እውነት ይሄው ነው፡፡

ከዚህ በተያያዘ አንድ ሰሞነኛ መረጃ ልንገራችሁ፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው ሰሞን የውስጥ ዕድገት ማስታወቂያ ያወጣል፡፡ ሠራተኞችም ማስታወቂያውን አንብበው ይመዘገባሉ፡፡ ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ግን አዲስ መመርያ ይወጣና የተመዘገቡት ሁሉ ብሔራቸውን እንዲሞሉ ይነገራቸዋል፡፡ የዚህ መመርያ ዓላማ በጣም ግልጽ ነው፡፡ እንዲህ ያለ መመርያ ደግሞ በየትም ሀገር አይወጣም፤ ቢወጣ ደግሞ ዓላማው ልክ እንደኛው ሀገር ነው፡፡ ሠራተኞችን በትምህርት ደረጃቸውና በሥራ ልምዳቸው አወዳድሮ እንደማሳደግ ብሔር የተጠየቀበት ምክንያት ለሌላ ሣይሆን ኦሮሞ ኦሮሞውን መርጠው ለማሳደግ ነው፡፡ ይህን አሠራር ደግሞ በሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ፈጥጦ እያየነው ነው፡፡ ከቀበሌ እስከወረዳና ከፍተኛ፣ ከከፍተኛ እስከሚኒስቴር መ/ቤቶችና መከላከያ አዛዥ ናዛዦቹ ሁሉም ኦሮሞ ናቸው፡፡ ወያኔን አስከንድተው እነሱ በአሁኑ ወቅት የእግዚአብሔርንም ቦታ ለመቆጣጠር ሳይከጅሉ አልቀሩም፡፡ እኛም በዚህ ከእንስሳም በወረደ ድርጊታቸው ፈዘንና ደንግዘን ፍርዱንም ለላይኛው ሰጥተን ተቀምጠናል፡፡

ከወያኔ የበለጠ ይሉኝታና ሀፍረት የሌለው የለም ስል እንደነበር አስታውሳለሁና የወያኔ ጌታ ሚስተር ሉሲፈር ይቅር ይበለኝ፤ እነሱን ዕጥፍ ድርብ የሚያስከነዱ ደናቁርት ኦሮሙማዎች ሀገሪቱን እንደመዥገርና እንደተምች ተጣብቀው እየቦጠቦጡ ናቸው፡፡ ሁሉም አክራሪ ኦሮሞ በ“አካም ነጉማ፣ በፈያዳ ፈዩማ” እየተሰባሰበ ኢትዮጵያን ከዳር እዳር እየዋጣት ነው - ሌላው አዘጥዛጭና አሽቃባጭም አላቸው - ሊያውም ከፕሮፌሰር እስከ ዲፕሎማ፤ ከትምህርት ሚኒስቴር እስከእርሻ ሚኒስቴር፤ ከቤተ መንግሥት እስከ ፓትርያርክ ጽ/ቤት፡፡ የሚገርመው ለመሰልቀጥ ዕቅድና ፕሮግራም የተያዘላቸው “”ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች”ም ሁሉ ተስማምተው በየተራ ለመበላት ወረፋ ይዘዋል፤ ከዚያም ባለፈ እርስ በርስ እየተጨፋጨፉ የኦሮሙማን ድካም በእጅጉ እየቀነሱለት ነው፡፡

ወይ ኢትዮጵያ! እንዲህ ያለ አዘቅት ውስጥ ትግባ? ፋኖዎች ቶሎ ቶሎ በሉ እንጂ፡፡ የምን ማፈር መተፋፈር ነው፡፡ ትግሉን እዚያው ጀምሩና ብዙ ሰው ወደሚጠብቃችሁ ወደ መሀል ሸዋ ብቅ በሉ፤ በቅድሚያ ግን ሆዳምና ተላላኪ አማራን ከሥሩ የሚያጸዳ ልዩ ኃይል ይቋቋም፡፡ ….

በኦሮሞ ብቻ ከተወረሩ መሥሪያ ቤቶች አንደኛው የኦሮምያ ማነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው፡፡ በዚህ ተቋም ከዘበኛ እስከ ሥራ አስኪያጅ ኦሮሞ ነው፡፡ ሁሉም ሠራተኛ ኦሮሞ መሆኑ ብቻውንና በራሱ ለኔ ችግር አይደለም፡፡ ሁሉን የሥራ ቦታ ኦሮሞ ቢይዘው ደንታየ አይደለም፡፡ ችግሩ ዓላማውና የሥራ ችሎታ ሳይኖር በዘረኝነት ትብታብ ተጠልፎ ሀገርን ለማውደም የሚሠራው ግፍና በደል ነው፡፡ እንጂ ለምሣሌ ሥራውን ችለውት፣ ቅንና ጨዋ ሆነው በትህትና ማስተናገዱን ቢያውቁበት እኔ ግድ የለኝም፡፡

ሰሞኑን ሆነ ብዬ በተወሰኑ ሆስፒታሎች ዞርኩ፡፡ ተገረምኩ፤ አዘንኩም፡፡ የኢትዮጵያ ትንሣኤም በእግረ መንገድ ቁልጭ ብሎ ታየኝ፡፡ የጅብ ችኩል ቀንድ የመንከሱ ምሥጢርም ተከሰተልኝ፡፡ ኦሮሙማዎች ይደንቃሉ፡፡ ጠንጋራም ሆነ ወልጋዳ ለአንድ ዓላማ ከልብ ከሠሩ አይቀር እንደኦሮሙማዎች ነው፡፡ ከዚህ ብዙ መማር አለብን፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ ነጻነት ተዋጊዎች ከነዚህ ጅሎች ትምህርት ቅሰሙ፤ ግን ጽናታቸውን ብቻ እንጂ ጭካኔያቸንና ጅብነታቸውን አይሁን፡፡ መጨከን ሲያስፈልግ መጨከንም ለድል ያበቃልና ጨክኑ፡፡

ወያኔ ብልጥ ነበረች፡፡ በይሉኝታቢስነትና በሀፍረተቢስነት በዓለም አንደኛ እንደሆነች ቅንጣት ሳላፍር እናገርላት የነበረችው ወያኔ አሁን ዞሬ ንግግሬን ሳጤነው ትልቅ ስህተት እንደነበር ተረዳሁ - ማንን ይቅርታ እንደምጠይቅ አላውቅም እንጂ በድጋሚ ትልቅ ይቅርታ፡፡ በሀፍረት የለሽነትና በይሉኝታቢስነት ኦሮሙማዎችን የሚስተካከል እንደሌለ ዛሬ ላይ ሆኜ በሚገባ ተገንዝቤያለሁ፡፡ ወያኔ ከአሥር ነገሮች አንድ ወይ ሁለቱን ምናልባትም ሦስቱን ለሌላ ጎሣና ነገድ ለይስሙላም ቢሆን ታካፍል ነበር፡፡ የአሁኖቹ ግን ድብን ያሉ ገገማዎች ናቸው፡፡

 ከ100 ነገሮች ውስጥ አንድ መቶ አንዱን ለነሱ ይወስዱታል፡፡ ሌላው አጨብጭቦ ሲቀር እነሱ ይምነሸነሹበታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ ስትጠግብ በሚተርፋት ገንዘብ አንዳንድ ሀገራዊም ይሁን ግለሰባዊ ቁም ነገር ትሠራ ነበር፡፡ እነዚህ ገሪባዎች ግን ዕውቀትና ፍላጎት፣ ትምህርትና ልምድ፣ ጥበብና ችሎታም ስለሌላቸው ዳንኪራ ሲረግጡና ካገኟት ሴት ጋር አንሶላ ሲጋፈፉ አድረው ቀኑን ሲያፋሽጉ ይውላሉ እንጂ በቁም ነገር ቦታ አታገኟቸውም፡፡ ትልቅ አለመታደል ነው፡፡ ስሙን አስተካክለው የማይጠሩትን መኪና ይገዙና ከየግድግዳና ፖሉ እያጋጩ በሀገር ሀብት ይጫወታሉ፡፡ አምናና ታቻምና መኪና አጣቢና ተላላኪ ሆኖ የምታውቀው ኦሮሞ ዛሬ ባመቱና በሦስት ወሩ መሬት እየቸበቸበና ከፍተኛ ጉቦ እየተቀበለ ሚሊየኔር ነው፤ ወይ ኦነግና ኦህዲዶች!!

ዕድሜያቸው አጭር ነው የምንለው ለዚህ ነው፡፡ እነዚያ ብልጦች ስለነበሩ 27 ዓመታትን እንደምንም ቆዩ፡፡ እነዚህ ግን የለየላቸው ደናቁርት ስለሆኑ አምስት ዓመት መድፈናቸውንም እጠራጠራለሁ፡፡ አያያዛቸው ያስታውቃልና ዕድሜያቸው የወራት እንጂ የዓመታት አይደለም፡፡ ቱ! ምን አለ እንትና በለኝ ጥቂት ሣምንታት ቢቀራቸው ነው፡፡ እንደጉድ እኮ ነው የወበሩት!!

 

 

Saturday, June 18, 2022

ሊቀ ሣጥናኤል በቤተ መንግሥት ዳግማዊ ጉዱ ካሣ Ethiopian Semay 6/18/22

 

ሊቀ ሣጥናኤል በቤተ መንግሥት

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Ethiopian Semay

6/18/22



ሰሚ ኖረም አልኖረም ሊቀ ሣጥናኤል አቢይ አህመድ የተሠራው ከውሸት መሆኑን ደጋግመን ጽፈናል፤ ተናግረናል፡፡ በሰሞኑ የፓርላማ ስብሰባ ደግሞ ይህንኑ በሚገባ አረጋግጦልናል፡፡ እኔ እዚያ ፓርላማ ተብዬ ውስጥ እንደአንድ አባል ተቀምጬ ብሆን ኖሮ እንደወጣሁ ወደሚቀርበኝ ዛፍ ሄጄ እንጠለጠል ነበር፡፡ በዚያ ዓይነት ሰው መመራት እጅግ እጅግ አሳፋሪና ስብዕናን የሚነካ ነው፡፡

የውሸቱ ለከት ማጣት ሰው ለሆነ ሰው ክፉኛ ያስደነግጣል፡፡ ለሌሎች የማይታይን ዕድገትና ብልጽግና ሲናገር “ለእናንተ አይደለም ለኔ ነው የሚታየው” በማለት እርሱ የተለዬ የማየት ችሎታ እንዳለው በተካነበት ሥራየ-ቤታዊ የሽሙጥ አነጋገር ሲገልጽ ዞምቤ ሮቦቶቹ ከማጨብጨብ ባለፈ አልገረማቸውም፤ አልደነቃቸውም፡፡ ምክንያቱም እነዚህ የንክር ቤት አባላት በመጽሐፉ “ዐይን አላቸው አያዩም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸቱበትም፤ አፍም አላቸው አይናገሩበትም” ተብሎ እንደተነገራለቸው የጣዖት አማልክት ናቸውና ከድጋፍ ጭብጨባ ባለፈ ምንም ነገር አያውቁም፡፡ ሲናገሩ እንደምንሰማቸው የተጻፈላቸውን እንኳን ለማንበብ የሚንተባተቡና የሚቸገሩ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በነዚህ ሲወከል ይታያችሁ፡፡ ደግነቱ እኛን ከቁም ነገር ቆጥሮ የሚያይ የለም እንጂ ቀሪው ዓለም በነዚህ ተወካዮቻችን ጥርሱን በዘነዘና ተወቅሮ በሣቀብን ነበር፡፡ ከቃላት ጦርነት ባለፈ አሽትሬ እየተወራወሩ የሚጨቃጨቁና የሚከራከሩ የፓርላማ አባላት ባሉባት ዓለማችን እነዚህን ጉዶች ማየትና በነዚህም እንደምንወከል ሲነገር መስማት በአቢይ አገላለጽ ያስደነግጣል፡፡

 አቢይ ለኢትዮጵያና ሕዝቧ ያለውን ንቀት በነዚህ ሰዎች - ሰዎች ማለት ከተቻለ - አዎ፣ በነዚህ ሰዎች መረዳት ይቻላል፡፡ በዐይን ጥቅሻ ብቻ ለርሱ ታዛዥ የሆኑ ወጣት ሴቶችንና ከደብተር ያልተላቀቁ ታዳጊ ወጣት ወንዶች ፓርላማ ተብዬው የሕዝብ አዳራሽ ውስጥ እያከማቸ ሀገሪቱን ይጫወትባታል፡፡ ተጽፎ የተሰጠውን ማንበብ የማይችል ሰው እንዴት አንድ መቶ ሽህ ሕዝብ እንደወከለ ይነገራል? ሰው ጠፍቶ ደግሞ እንዳይመስላችሁ፡፡ የሚፈለገው ማይምና ከዕውቀትና ከችሎታ የጸዳ በመሆኑ ነው፡፡

ከ500 በላይ የሚቆጠር በግ በአንድ አዳራሽ ሰብስቦ ይሄ አቢይ የሚባል ሊቀ ሣጥናኤል እንጨት እንጨት የሚል የቁጭ በሉ ድራማ ይተውንብናል፡፡ ለነገሩ በራሱ ላይ ነው ትያትሩን የሚጫወተው፡፡ ሒሣቡን የሚወራርደው ራሱ ነውና፡፡ የዚህን ሰውዬ መጨረሻ ሂትለርና ሣዳም ሁሴን ይቀኑበታል፡፡

በነገራችን ላይ የአቢይን ተፈጥሯዊ ጠባይ የሚገልጡ ሁለት አጫጭር ታሪኮችን ልናገር፡፡ ባትስቁም ፈገግ በሉ፡፡

አንዱ ዐይኖቹን ታሞ ከቅምብቢት ወደ አዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ይመጣል፡፡ ዱሮ ነው ታዲያ፡፡ የህክምና ዶክተሩ የልጁን ዐይኖች ሲመረምር ወጥተው መታጠብና መጽዳት እንደሚኖርባቸው ይረዳል፡፡ ወዲያውኑም ውልቅ ያደርጋቸውና አጣጥቦ መልሶ ሊከታቸው ሲል ጓደኛው ለሻይ ይጠራዋል፡፡ ከሻይ ሲመለስ ግን የልጁን ዐይኖች ካስቀመጠበት ያጣቸዋል፡፡ ያኔ ዘወር ሲል አንድ የሆስፒታሉን ድመት ይመለከታል፤ ያም ድመት ኖሯል እነዚያን ዐይኖች ቀርጥፎ የበላቸው፡፡ ይሄኔ ዶክተሩ ምኑ ሞኝ ያንን ድመት ይይዝና ዐይኖቹን በህክምና ዘዴ ጎልጉሎ አውጥቶ በጠፉት ምትክ በታማሚው የዐይኖች ጉድጓድ ይሰካቸዋል፡፡ ከዚያም ከ15 ቀናት በኋላ ለቼካፕ እንዲመለስ ነግሮ ልጁን ወደቅምብቢቱ ይሸኘዋል፡፡

 

ዐይኖቹን ታክሞ አገር ቤት የሄደው ልጅ ዘመድ አዝማድና ጎረቤት ተሰብስቦ ጠበቀው፡፡ በልጃቸው መምጣት የተደሰቱት የአካባቢው ማኅረሰብ አባላት ልጁን ጥያቄ በጥያቄ ወጠሩት፡፡ “እንዴት ነው በደምብ ይታይሃል?” “አዎ፣ በደምብ ይታየኛል”፤ “አሁን በዙሪያ ምን ይታይሃል?” “አሁን በዙሪያየ ብዙ ዐይጥ ይታየኛል፡፡” ልጁ ልክ ነው - “ዶሮ ብታልም ጥሬዋን” እኮ ነው ነገሩ፡፡ የማያውቁት አገርስ ይናፍቃል?

እውነት ነው፣ የድመት ዐይን ከዐይጥ ሌላ አይታየውም፡፡ የአቢይም አንደበት ከውሸትና ከእብለት ሌላ ሊናገር ፈጽሞውን አይችልም፡፡ ችግሩ ያለው ከርሱ ሳይሆን ከኛው ከሀገሪቷ ሕዝብ ነው፡፡ ይህን የመሰለ እንኳንስ ሀገር ለመምራት ራሱንም መምራት የሚያስቸግር ዕብድና ወፈፌ ዜጋ ቁንጮ ላይ ማስቀመጥ ወይም እንዲቀመጥ መፍቀድ ነው ትልቁ ችግር፡፡ ኢዲያሚን ዳዳም፣ አፄ ቦካሣም እንደኛው ልጅ ዕብድ ነበሩ፡፡

ሁለተኛዋ ትንሽ ታስከፋለችና ብተዋት ደስ ባለኝ፡፡ ግን አልተዋትም፡፡ አንዱ ዲያቆን ሚስት ሊያገባ ነው፡፡ ግን ልጃገረድ እገስሳለሁ ብሎ በራሱ አይተማመንም ነበር፡፡ በራስ ላይ እምነት ሲጠፋ ደግሞ አእምሮ አስቀድሞ ተቀይዷልና ችግር መፈጠሩ አይቀርም፤ በራስ መተማመን ጥሩ ነው፡፡ አለመተማን ግን ብዙ ጣጣ አለው፡፡ ይህም ልጅ ታዲያ ሠርጉ ደርሶ የሙሽራ ወጉን በማድረግ የደም ሸማው ሲጠበቅ እርሱ ግን ስላቃተው በፊቱን አዘጋጅቶት በነበረ ከእንጨት የተሠራ አርቲፊሻል የወንድ ብልት ልጅቷን አበላሻት፡፡ ያንን የልጁን ነውረኛ ድርጊት የተረዳችው ሙሽራ በደረቅ ሌሊት ከጫጉላ ቤቱ አምልጣ ጠፋች፡፡ እውነተኛ ታሪክ ነው - የፈጠራ አይደለም፡፡ አያድርስ በሉ፡፡ አንድ ማኅበረሰብ በብዙ አፈንጋጮች የተሞላ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

ሊቀ ሣጥናኤል አቢይ አህመድም ሀገራችንን ልክ እንደዚያ በራሱ የማይተማመን ሙሽራ እያደረጋት ነው፡፡ አቢይ ከልጁ የሚለየው የሰይጣናዊ ተልእኮው ክብደት ነው፡፡ ማን ምን እንዳዞረብን ደግሞ አላውቅም፡፡

አሁን ሁሉም ሰው ስለዚህ የመርገምት ፍሬ ብዙ ነገር ያውቃል፡፡ ሀገር ለማፍረስ መምጣቱን እናውቃለን፤ ከኛ መራብና መጠማት ይልቅ ለወንበሩ እንደሚሳሳ እናውቃለን፡፡ ከኛ መፋጀት ይልቅ የርሱ ዝናና ክብር እንደሚበልጥበትና ለዚያም ተግቶ እንደሚሠራ እንገነዘባለን፡፡ እርሱ እያለ ኢትዮጵያ ለይቶላት ከዓለም ካርታ እንደምትፋቅ እናውቃለን፡፡ ችግሮቻችንን ብቻም ሳይሆን መፍትሔዎቻቸውንም እናውቃለን፡፡ ግን እንዴት እንተግብረው ነው ትልቁ ጥያቄ፡፡ አሁን ነው የዐይጦችን ጉባኤ ማስታወስ፡፡

አንድ ድመት ዐይጦችን እየበላ አስቸገረ፡፡ ዐይጦች ጉባኤ ጠሩና ስለመፍትሔው የጦፈ ውይይት ያዙ፡፡ ብዙ የመፍትሔ ሃሳቦች ላይም ተወያዩ፡፡ አንደኛው የመፍትሔ ሃሳብ ብቻ አሸነፈና የሁሉንም ቀልብና ድጋፍ አገኘ፡፡ እርሱም “በድመቱ አንገት ላይ ቃጭል እናድርግና ሲመጣ ሰምተን እንሽሽ” የሚለው ነው፡፡ ስብሰባው በጭብጨባ ሊበተን ሲል ግን አንድ ብልኅ ሽማግሌ ዐይጥ “ሃሳቡ ጥሩ ነው፡፡ ግን ቃጭሉን ወደ ድመቱ አንገት ወስዶ የሚያስረው ማን ነው?” የሚል ጥያቄ ደቀነባቸውና የጉባኤውን ልፋት ሁሉ መና አስቀረው፡፡

ይህ የአጋንንት ውላጅ፣ ይህ አስተዳደግ የበደለው ክፉና በሰዎች ስቃይ የሚደሰት ሀዘን አምላኪ፣ ይህ አማራንና ኦሮሞን እያፋጀ ያለ የሣጥናኤል የበኩር ልጅ፣ ይህ በክፋት ሥራ መላ ሰውነቱ የተበከለ የሰንበት ጽንስ እንዴት ከአራት ኪሎ ይውጣ ነው ጥያቄው፡፡ ይወጣል አይቀርም፡፡ እስኪወጣ ግን ጣጣው ብዙ ነው፡፡

 

…. ያቺ ጥቁር ክላሽ ግን አስቂኝ ናት፡፡ የመጣችው ከጦርነቱ በኋላ፡፡ ፋኖ የቆሰሉ አማሮችንና ኦሮሞዎችን እንዲሁም ወላይታዎችን የገደለውና ጥቁሪቷን ክላሽ ከቁስለኞች ማርኮ የታጠቀው ደግሞ ከጦርነቱ በፊት፡፡ ምን ዓይነት ውሸት ነው? ይሄ ሰውዬ የመዋሸት አማካሪም የለውም እንዴ? ደግሞስ ሰውን ከእስር ሲፈታ ደንግጦ፣ ሰውን ሲገድል ደንግጦ፣ ሰውን ሲያስር ደንግጦ፣ ሲሰድቡት ደንግጦ … እንዴት ይዘልቀዋል? ከኢዜማም ከቁዘማም ይህን ሰውዬ የከበባችሁ ሰዎች እባካችሁን አለቃችሁ እንዲህ ዓይነት ቅሌት ውስጥ እንዳይገባባችሁ የሚናገረው ውሸት ከቦታ ከጊዜና ከሁኔታ ጋር በመጠኑም ቢሆን እንዲመጣጠን እርዱት፡፡ ውሸት እኮ ልክና መጠን አለው፤ በትክክለኛው መንገድ ቢዋሽ ለሰሚም ግራ አይሆንም፡፡ መጥኔ ለሚስቶቹ ማለቴ ለሚስቱ፡፡ የቱቦ እንጂ የሰውነት ባሕርይ የሌለው የመጀመሪያው ፍጡር ይህ ሰውዬ ይመስለኛል፡፡ ወደፊት ሰዎች ስለውሸታም ሰው ሲናገሩ “እንደ እንደአቢይ ይቀረደዳል” ማለታቸው አይቀርም፡፡

ከርሱ አንደበት እንደተሰማው ከኢትዮጵያ መሪዎች እንደሱ የተሰደበ የለም፡፡ እኔም እላለሁ ከኢትዮጵያ መሪዎች እንደሱ ኢትዮጵያን መቀመቅ የከተተ የለም፤ ወደፊትም አይኖርም፡፡ እናም ስድቡ መለማመጃ እንጂ ገና ብዙ ነገር ይጠብቀዋል፡፡ በእልህ ሥጋውን በልተው የማይረኩ እጅግ የተናደዱና የተከፉ ወጣቶች እንደሮማንያው ቻውቼስኮ ከሄሊኮፕተር አውርደው የመጨረሻውን ዋጋ ይከፍሉታል፡፡ ጠብቁ፤ እንጠብቅ፡፡

 

 


Monday, June 13, 2022

“የሕዝብ ሰው /Public Figure/ መሆን አንዳንዴ ሳያሰክር ይቀራል? ብሥራት ደረሰ ETHIOPIAN SEMAY 6/13/22

 

“የሕዝብ ሰው /Public Figure/ መሆን አንዳንዴ ሳያሰክር ይቀራል?

ብሥራት ደረሰ

ETHIOPIAN SEMAY

6/13/22


በስንቱ ተናድጄ እንደምዘልቀው አላውቅም፡፡ ዛሬ ሌሊት ነው፡፡ እንደልማዴ የዩቲዩብ ቻናሎችን ስዳስስ አንዱ ቀበጥ አርቲስት ሚስት ሊያገባ ከአርባ በላይ ሽማግሌዎችን ወደእጮኛው ቤት መላኩን በኩራት የሚገልጽ አንድ የዩቲብ ገጽ ላይ ዐይኔ ዐረፈ፤ ቀልቤንም ሳበውና እከታተለው ጀመር፡፡ ግን አልጨረስኩትም፡፡

 የሰዎችን ሥራ ፈትነት ከተገነዘብኩበት በቂ ነው ብዬ ወደ ሌላ አንገብጋቢ ዝግጅት አመራሁ፡፡ የሀገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት መቼም የሚያስቀና ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ይህ አብሻቂ ክስተትም የሚያሳየን ይህንኑ ነው፡፡

በርግጥም ይሄ በሰዎች ዘንድ የመታወቅ ጣጣ ሳያጃጅልና ሳያሰክር አልቀረም፡፡ አሁን ማን ይሙት አንድ ታዋቂም ሆነ አል-ታዋቂ ሰው ሚስት አገባ አላገባ ምን ያህል ሀገራዊና ሕዝባዊ ቁም ነገር ኖሮት ነው እንዲህ ያለ መጃጃል ውስጥ የተገባው? በውነት በዝግጅቱና በአርቲስቱ አፍሬያለሁ፡፡ ነገሩ ባጭሩ “ሳይቸግር ጤፍ ብድር” እንዲሉ ነው፡፡ በሽምግልናው የተካተቱ ሰዎችም ሥራ ፈትነታቸው አሳዝኖኛል፡፡ የቀረ እኮ የለም! ከጳጳስ እስከ ዲያቆን፣ ከሰባኪ እስከ ዘማሪ፣ ከሴት አርቲስት እስከወንድ የቦተሊካ አናሊስት … ምን አለፋችሁ በሽምግልናው ያልታደመና ያልተካተተ አንድም የበቃና የነቃ ብፁዕ ዜጋ የለም - ከፓትርያርኩና ከጠ/ሚው እንዲሁም እስልምናንና ካቶሊክን ከመሰሉ አንዳንድ የሃይማኖት መሪዎች በስተቀር ሁሉም ተካቷል ማለት ይቻላል - ሲያሳዝኑ!! መጋቢ ሀዲስ እሸቱ ራሳቸው አሉበት፡፡ ያልገባኝ ግን ዓላማው ነው፡፡ በዛሬ ጊዜ ባል ተገኝቶ እምቢ ሊባሉ ኖሯል? ሥራ ያጣች መነኩሴ አሉ …

ሀገራችን ጭንቅ ላይ ናት፡፡ ጦርነቱ፣ ርሀቡ፣ ስደትና መፈናቀሉ፤ ዘረኝነቱ፣ የኑሮ ውድነቱ፣ እስር እንግልቱ፣ አፈናውና እገታው …. ይህና ሌላው ችግር ወጥሮን ቀኑ በመከራ ነግቶ በመከራ እየመሸ እንዲህ ዓይነት ቅብጠትና የአርቲስቶች መሞላቀቅ በፍጹም ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ለካንስ ዜጎች በተለያዬ ምህዋር ውስጥ ነው የምንገኘው!! ለካንስ ተለያይተናል፡፡

 ደግሞም አንድኛህ አንባቢ ወይ አድማጭ  “ቀንተህ ነው” በለኝና አስቀኝ አሉ፡፡ ምኑ ነው የሚስያቀናው? የአርቲስቱ ዘግይቶም ቢሆን ማግባት? ለአንዲት “ኮረዳ” ከአርባ በላይ ዕውቅ ዜጎችን ለሽምግልና ልኮ ሥራ ማስፈታት? ይህ ድርጊት ያሳፍራል እንጂ በጭራሽ አያስቀናም፡፡ አእምሮን በትክክል ያለመጠቀም ውጤት ሊያስቀና አይችልም፡፡

ሽምግልና ምን ማለት ነው? እኔ እንደሚገባኝ ሽምግልና ማለት ዓይነቱ ብዙ ቢሆንም ሠርግና ጋብቻን በተመለከተ ግን ወንዱ ለሴቷ ቤተሰቦች ሦስት ሽማግሌዎችን ልኮ “ልጃችሁን ለልጃችን” በሚል ባህላዊ ሥርዓት የቤተሰብን ፈቃድ የሚጠይቅበት ወግ ልማድ ነው፡፡ ሦስት ሰዎች መሆናቸውም ሥላሤዎችን እንደሚወክል ስለሦስት ቁጥር ታሪክ ከተጻፉ መልእክቶች መረዳት አይከብድም፡፡ ገና ለገና ታዋቂ ነኝ ተብሎ፣ ገና ለገና “አገር ምድሩ ስለሚያውቀኝ ታዋቂ ሰዎችን በብዛት ልኬ ታሪክ እሠራለሁ” ከሚል የሞኝ አስተሳሰብ ተነስቶ እስከዚህ መውረድ የጤንነት አይደለም፡፡

ለዚህ ለዚህማ አገር በመከራ ዶፍ እየተመታች በአሁኑ ሰዓት በሌለን ገንዘብ በ50 ቢሊዮን ብር ቤተ መንግሥት ሊሠራ የሚጃጃለው ጠ/ሚኒስትራችን ምን አጠፋ!! በሀገራችን የጋብቻ ታሪክም አርባና ሃምሳ ሽማግሌዎችን ልኮ ቤተሰብን ያስፈቀደ አልሰማሁም፤ የዚህ ችግር ምንጭ የመታወቅና ያለመታወቅ ብቻ ሳይሆን ባህሉን በውል ያለመረዳትም ጭምር ይመስለኛል፡፡ እንጂ እኮ መቶ ሽማግሌም መላክ የሚችሉ ከዚህ አርቲስት የበለጡ ሀብታሞችና ዝነኞች አሉ፡፡“ኧረ ይሄ ነገር ያስቅብናል፤ ‹አወቅሽ፣አወቅሽ› ቢሏት ‹የባሏን መጽሐፍ አጠበች› ተብሎም ይተረትብናልና ግዴለህም በቅጡ እናድርገው!” የሚል አማካሪስ እንዴት ይጠፋል? እንዴት ሁሉም ተያይዞ የሕጻናት ዕቃቃ ጨዋታ ውስጥ ይገባል? የደላው ሙቅ ያኝካል ነው የሆነብኝ፡፡

ሌላው የገረመኝ ደግሞ ለሽምግልና የተመረጠው ታዳሚ ሁሉ ወግና ልማዱን ዘንግቶ ተግተልትሎ መሄዱ፡፡ አርቲሰቱን ማፍቀር ሌላ፣ ከባህልና ከወግ መጣረስ ሌላ፡፡ ምን ፈረደብን ጎበዝ፡፡ አንድ ሰው እንኳን “ኧረ ይሄ ነገር ከባህላችንና ከትውፊታችን ውጪ ነው” ብሎ እንዴት አልተቃወመም? “እኔ እንዲህ ነኝ፤ ዕወቁኝ” ለማለት ካልሆነ በስተቀር በዚህ የሽምግልና ሂደት አንዳችም ትምህርት አልተላለፈም - ከጉራ በስተቀር፤ “ጉራ ብቻ” አለ ቴዲ አፍሮ - እውነቱን ነው፡፡ ከዚህ ዓይነት ጅልነት ለወደፊቱ ታዋቂ ሰዎቻችን ቢጠነቀቁ ከትዝብት ይድናሉና ይህችን ማስታወሻ ሳያገባኝ እንዲሁ ከተብኩ፡፡ ታዋቂነት ከብልኅነት ጋር ይደመር፤ አለዚያ ትርፉ ኪሣራ ነው፡፡ “በማን ላይ ቆመሽ” እንዲሉ ነውና ሕዝባችሁን አስቡት፡፡ እንደዚህ ዓይነቱ እዩኝ እዩኝ በተለይ በዚህን የመከራ ወቅት ተገቢነት የለውም፡፡

ከታዋቂ ሰዎች አንዱ እንግዲህ ወፈፌው ጠ/ሚኒስትራችን መሆኑም አይደል? አዎ፣ ሀገር በችጋርና በችግር እየተጠበሰች የደላው አቢይ የግድግዳ ቀለም በማስቀየር ላይ ነው፡፡ የዕብድ ገላጋዩም በዛና አዲስ አበባ ውስጣዊ ክርፋቷን በግድግዳ ቀለም የደበቁ የሚመስላቸው ኦሮሙማዎች ሌት ተቀን ግድግዳ እየፋቁ ግራጫ ቀለም በመቀባት ላይ ናቸው፡፡ ማወቅ ያለባቸው ግን በውጫዊ የቀለም ለውጥ የውስጥ ግማትንና ቁናስን መከላከል የማይቻል መሆኑን ነው፡፡ ይቺ ሌላ ያቺ ሌላ ብለዋል አለቃ ገ/ሃና፡፡ ወይ ዘመን ሲያረጅ!! የዘመን ጅጅትና አይግጠማችሁ፡፡ ይሄ ዘመንማ አለቅጥ ጃጀ፡፡ እጅግ አስጠሊታም ሆነ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያልን እንግዲህ 2015 ዓ.ምን ልንቀበል የዛሬዋን ሰኔ ስድስትን ጨምሮ ልክ ሦስት ወራት ብቻ ቀሩን፡፡ ያኔ ከፍ ሲል ከጠቃቀስኳቸው የግልና የቡድን ጅልነቶችና ማኅበረሰብኣዊ ስካር ዕብደቶች ተገላግለን በጤናማ ሁኔታ እንደምንገናኝ ተስፋ አለኝ፡፡ ያኔ ብዙዎቻችን ወደ አቅላችን ተመልሰን እንደሰው ማሰብ እንደምንጀምር ትልቅ ተስፋ አለኝ፡፡ ያኔ ቁጥራችን ከአሁኑ ሲነጻጸር ዝቅተኛ መሆኑ ቢገመትም ለዚያ ዘመን የምንበቃ ዜጎች እርስ በርስ እየተያየን አንዳችን ለአንዳችን መተሳሰብና መተዛዘን የምንጀምርበት ወቅት እንደሚብት እገምታለሁ፡፡ ያኔ አሁን መቀመቅ የከተተን ዘረኝነትና ጎጠኝነት ተወግዶ በሀገራዊ የጋራ ስሜት እንደምንተሳሰር ተስፋ አለኝ፡፡ ያኔ አሁን የሚያመነቃቅሩን የዲያቢሎስ ልጆች ጥጋቸውን ይዘው በዕውቀትና በጥበብ በሚመሩ መልካም እረኞችና ለነፍሳቸው በሚያድሩ ደጋግ አባቶች እጅ እንደምንገባ አምናለሁ፡፡ ለአርቲስቶቻችንም ልቦና ይስጥልን፤ ከሚያጥበረብርና ልብን ከሚያሳባጥ ዕብሪትም ይሠውርልን፡፡ ፈጣሪ ሀገራችንን በቶሎ ይጎብኝ፡፡ ….

ETHIOPIAN SEMAY


Thursday, June 9, 2022

አማራዊነት ያሸንፋል፤ ኢትዮጵያም በልጆቿ ትነሣለች! ዳግማዊ ጉዱ ካሣ Ethiopian Semay 6/9/2022

 

አማራዊነት ያሸንፋል፤ ኢትዮጵያም በልጆቿ ትነሣለች!

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Ethiopian Semay

6/9/2022


እንግዲህ “ሽልም ከሆነ ይገፋል፤ ቂጣም ከሆነ ይጠፋል” እንዲሉ ሆነና ሽሉም ገፍቶ ቂጣውም ጠፍቶ የምናይበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ ጊዜ መስታዎት ነው፡፡ ሁሉን ያሳያል፡፡ የነበረ እንዳልነበረ፣ ያልነበረም እንደነበረ የሚሆኑባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው፡፡ በአንድ ጉባኤ አርባ ጊዜ “ኢትዮጵያ ፣ ኢትዮጵያ” እያለ የኢትዮጵያ ስም በመሪዎቿ አንደበት መጠራት የብርቅ ያህል ይናፍቀው ለነበረ ሕዝብ የዓዞ ዕንባውን ይረጭ የነበረው ይሁዳም እውነተኛ ይሁዳዊ ማንነቱን አሳይቶ ኢትዮጵያን በመሳም ለጠላቶቿ አሳልፎ ሸጧታል፡፡

 ባህር ዳር ላይ ሄደው “ኢትዮጵያ ሱሴ”ን የዘመሩ ሁሉ ዝማሬያቸው ለተወሰነ ጊዜ ብዙ ፍሬ ቢያስገኝላቸውም የመጨረሻ ዓላማቸው በመገለጡ ግን አሁን ተነቅቶባቸዋል፡፡ የኦሮሙማው ኢምፓየር አጋፋሪ አቢይ አህመድ፣ ሆዳምና ነፈዝ አማሮችን በገንዘብና በማይሠሩበት ሽርፍራፊ ሥልጣን እየደለለ አጃቢዎቹ አድርጎ ላለፉት አራት ዓመታት ኢትዮጵያን ለመበታተን ሌት ከቀን ተግቶ ሠርቷል፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የት እንዳለ እንኳን በውል የማያውቅን ገዱ አንዳርጋቸው “የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር” አድርጎ እንደመሾም ያለ ዐይን አውጣነትና አስመሳይነት በዓለማችን ታይቶ አያውቅም - እኔማ የዚህ ሰውዬ ምትሃታዊ ተግባራት ከማስገረም አልፈው ያስቁኛል፤ የሚያምነው ሰው ደግሞ መሙላቱ፡፡ ከርሱ ጋር እንደሰው መቆጠሬ ራሱ ያበሳጨኛል፡፡ ይህ ልጅ በርግጥም ከታችኛው ዓለም ስለመላኩ መጠራጠር አይገባም፡፡ ለዚሁ እርኩስ ዓላማው ስኬት ሲል ቤተሰቡን እስከመበተን በደረሰ ጭካኔና ኢሞራላዊነት የ120 ሚሊዮን ሕዝብ የጋራ እናት የሆነችን ሀገር በጣጥሶ ለመጣል የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡ ግን አይሳካለትም፡፡ ኢትዮጵያ የተለዬች ሀገር ናት፡፡ ታሪክን ጎብኙ፡፡ እንጎብኝ፡፡

አሁን ኢትዮጵያ የመዳን ዕድሏ - እውነቱን ለመናገር - በአማራው እጅ ውስጥ ይገኛል፡፡ ሰፊው የአማራ ሕዝብ በተሠራበት ደባ ምክንያት እስካሁን ድረስ አፉንም ክንዱንም ፀጥ ረጭ አድርጎ እየሆነ ያለውንና ሲሠራበት የነበረውን ግፍና በደል ሁሉ በዝምታ ሲመለከት ቆይቷል፡፡ ይህን ዝምታውን እንደፍርሀት የቆጠሩት ወገኖች በደስታ እየፈነጠዙ አማራውን አደጁ ድረስ ሄደው አንገቱን እየቀሉት ነው፤ ንብረቱን እያወደሙና ዘሩንም እያመከኑት ነው፡፡ ግፍ ሲበዛ ከተኙበት መባነን ያለና የነበረ ነውና አሁን አማራው ለማንም ወደማይመለስበት ደረጃ እየተቃረበ ነው፡፡ ግን አሁንም ቢሆን ገና ነው፡፡ ብዙ ሥራ መሠራት አለበት፡፡ ይህ ሥራ ደግሞ በአማራው በራሱ ብቻ ሳይሆን ይበልጡን በጠላቶቹ እየተሠራ ነውና አማራው መንቃትና ማምረርም ጀምሯል - ቢዘገይም ጥሩ ነው፡፡ ለወትሮው “በጊዜ የጮኸ ጅብ አያሳድረኝም” የሚል ብሂል የነበረው አማራ የነካው ሳይታወቅ ለበርካታ አሠርት ዓመታት የጠላቶቹ ሰለባ ሆኖ ከርሟል፡፡ በዚያም ምክንያት ከስድስት ሚሊዮን ሕዝብ የወጡ ወሮበሎች የመንግሥትን ሥልጣን ይዘው በአርባና ሃምሳ ሚሊዮኑ አማራ ሲዘባነኑበትና መከራ ፍዳውን ሲያሳዩት ታዝበናል፡፡ ይህ ትግስትም ፍራቻም ሊባል የሚከብድ ታራካዊ አጋጣሚ እንዴት እንደተከሰተ ታሪክ ራሱ ይድረስበት፡፡ ግን ግን እውነት ነው - “የናቁት ያደርጋል ራቁት!”

የአሁኑ ይባስ ደግሞ በርግጥም የአሁኑ ይባስ ሆኗል፡፡ ኦሮሙማዎች እጅጉን ታውረዋል - “ኦሮሞዎች” አላልኩም!! ማንም ጠግቦ በማያውቀው ደረጃም ጠግበዋል፡፡ በዚያም ምክንያት አይነጋ መስሏት ወፍጮዋን እንዳበላሸችው ሴት ሆነዋል፡፡ ይህ ለወደፊቱ የአብሮነት ሕይወት አሳዛኝ ጠባሳ መፍጠሩ አይቀርም፡፡ ጥጋብን መቆጣጠር የአንድ ሰውም ይሁን የአንድ ድርጅትና ቡድን የመጀመሪያ ኃላፊነት መሆን ሲገባው ኦሮሙማዎች ግን ለታዛቢ እስከሚያስደነግጥ ድረስ ጥጋባቸውና ዕብሪታቸው ለከት አጥቶ ይሠሩትን ቀርቶ ይናገሩትን አሳጥቷቸዋል፡፡ አንዳንዴ ለነሱም አዝናለሁ፡፡ “ከተራበ ለጠገበ አዝናለሁ” መባሉም እኮ ለዚህ ነው፡፡

ለዚህ ጥጋባቸው ግን ተጠያቂው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፡፡ እዚህ ላይ አማራ ትግሬ ኦሮሞ ማለት አያስፈልግም፡፡ በዘር የማያምን፣ በጎሣዊ በነገድ ልክፍት ያልተጠቃ፣ በሃይማኖትና በመሳሰለው ልዩነት ያልተመረዘና ራሱን ከፍ ሲል እንደሰው - ዝቅ ሲልም እንደኢትዮጵያዊ የሚቆጥር ማንኛውም የዚህች አገር ዜጋ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ከዚህ በመለስ በቋንቋውና በነገዱ የሚኮፈስ ቢኖር ከሰው ተራም የሚገባ አይደለምና መጥፋት ያለበት አራሙቻ ነው፡፡ አማራን እስካሁን አቆርቁዞ ያቆየው እንግዲህ እንደሌሎች ወርዶ በአማራነቱ አለመደራጀቱ ነው፡፡ ይህም ለበጎ ነው፤ እንደዚያ ቢሆን ኖሮ አማራም እንዳንዳንድ ነገዶች  ኢትዮጵያዊነቱ ያከትምና ወይም በእጅጉ ይቀዘቅዝና ሀገራችን ወደማትወጣው ችግር ትገባ ነበር፡፡ ትልቅ መሆን በትንሾች ያስጠቃል፡፡ ትልቅ ሆነህ ትንሽ ልሁን ብትል ትኅትናህን እንደፍርሀት ይቆጥሩና ይበልጥ ያላግጡብሃል፡፡ ለአብነት የአርባ ዓመት ጎልማሳን የአምስት ዓመት ታዳጊ ጮርቃ በሣማ ቢገርፈው ትልቁ ይሸሻል እንጂ አይገጥመውም፤ ለተመልካች ፍርድም ያስቸግራልና እንዲህ ያለ ነገር አያድርስ ነው፡፡ እንጂ የአራትና አምስት ክፍለ ሀገር ሕዝብ - መለያየቱና ከዘረኝነት መጽዳቱ ለጠላቶቹ የጥቃት ዒላማነት እንዳመቻቸው በታሳቢነት ተይዞ - አስተባባሪና ጥሩ አመራር ቢኖረው ኖሮ ወያኔም ሆነ ኦነግ/ኦህዲድ ባልተጫወቱበት፣ ሀገሩንም ለጊዜውም ቢሆን ባልበታተኑበት ነበር፡፡ ግዴለም፡፡ ይሁን፡፡ መሆን ያለበት ይሆናልና ላለፈው አንቆጭ፡፡ ስላለንበትና ስላለፍነው ጨለማ ሳይሆን ስለወደፊቱ ብርሃን እናስብ፡፡ ኢትዮጵያ ወደነበረው ክብሯ ትመለሳለች፡፡  

ወንድሞችና እህቶች ሆይ! የወደፊቱ አያሳስባችሁ፡፡ ጠላቶቻችን ከደገሱልን የዕልቂት ብፌ ይልቅ ፈጣሪያችን ያዘጋጀልን የነፃነት ወርቃማ የብርሃን ቀንዲል ይበልጣል፡፡ ነገ ነገር ሁሉ በጎ ይሆናል፡፡ ነገ መልካም የሚሆነው ግን ስለተመኘን ብቻ አይደለም፡፡ የክፉዎች መጨረሻ በምድርም ሆነ በሰማይ ስለማያምር እንጂ የታሰርንበት የእሳት ሰንሰለት በራሱ ለቆን ስለሚጠፋ አይደደለም፡፡

አሁን ሁሉም ነገር ፍንትው ብሎ የሚታይበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ብያለሁ፡፡ ይህ ሁኔታ ግን ገና ለ30 እና 40 በመቶ ለምንሆነው ዜጎች ነው፡፡ ቀሪው አሁንም ገና ዳፍንት ውስጥ ነው፡፡ ሆኖም በአሁኑ የጠላቶቻችን ፍጥነት በእያንዳንዱ ዜጋ ላይ ችግሩ ሲከሰት ሁሉም ይባንናል፡፡ በናቡከደነፆር አቢይ አህመድ ግራኝና በሂትለር ሽመልስ አብዲሣ ተመልምሎ በመቶ ሽዎች የሰለጠነው ኦነግ-ሸኔ አዲስ አበባ ገብቶ በየበርሽ በጥይት ሲቆላሽ ያኔ እያንዳንድሽ የዛሬ ጩኸታችን ይገባሻል፡፡ ያኔ ነው ጉዱ፡፡ አሁንም ግን አዳሜ ለሽ ብለሽ ተኚ፡፡ “የሚፈለገው ፋኖ እንጂ እኔን ማን ይፈልገኛል” እያልክ እንደከብት ያገኘኸውን እያመነዠክህ የምትተኛ ሁሉ የምትተርፍ መስሎህ ተደበቅ፡፡ ለማንኛውም እነአቢይ መግቢያ ቀዳዳ የሚያጡት በዚያን ወቅት ነው - ሁሉም ነቅቶ ወደአልሞትባይ ተጋዳይነት ሲለወጥና ላለመሞት መላው ዜጋ ነብር ሲሆን ነው የመለያ ምቱ ፊሽካ የሚነፋው፤ አሁንማ የኦነግ/ኦህዲድ ዓላማና ፍላጎት ብዙ ሰው የገባው አይመስልም፡፡ ኦነግ/ኦህዲዶችም ዛሬና አሁን ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ የሆነላቸው መስሏቸዋል፡፡ በዚያም ምክንያት አማራ የተባለን ሁሉ እያፈኑ ወደማይታወቁ ሥፍራዎች ወስደው እያጎሩ ነው፡፡ የአማራ ክልል ኦሮሚያ እስኪመስል ድረስ የኦሮሞ ልዩ ኃይሎችን እያሰማሩ አማራ የተባለን ሕዝብ እያሰቃዩ ነው፡፡ ጥሩ፡፡ በዚሁ ይቀጥሉ፡፡ ብአዴንም ትብብሩን ይቀጥል፡፡

ወገኖቼ የናቁት ወንድ ያስረግዛል፤ ይህንን እውነት ይበልጥ እንገነዘብ ዘንድ በሀገራችን ብዙ ሆነ፡፡

በኢትዮጵያ ምድር መናናቅ ትልቁ ባህል ነው፤ አስጠሊታ ባህል፡፡ የመናናቅ ውጤት ግን እንዳየነው ሀገርን እስከማፍረስ ይደርሳል፡፡ ጉንዳን እንኳን ሱሪ ታስወልቃለች፡፡ ዓለም የናቃት ጽዮናዊቷ  እስራኤል በጥቅሉና በዓለም ዙሪያ ጭምር 18 ሚሊዮን አካባቢ የሚገመት ሕዝብ ይዛ ዓለምን በቁጥጥሯ ሥር እንዳደረገች ለምንረዳ የተናቀ ማስረገዙን በቀላሉ እናስተውላለን 

ሰባት ሰባራ ክላሽ ይዘው የተነሱ ወያኔዎች “ምንም አያመጡም” እየተባሉ ሲናቁ ከርመው ታላቁን የምሥራቅ አፍሪቃ መንግሥት ገለበጡ፡፡ እነዚያ ጥቂት ወያኔዎች ብዙውን አማራና ኦሮሞ እንዲሁም ሌላ ነገድ ለ27 ዓመታት እንደሰም አቅልጠው እንደብረት ቀጥቅጠው ገዙ፡፡ አዎ፣ “የጠሉት ይወርሳል፤ የፈሩት ይደርሳል” ነውና ምድርና ሰማይ የማይችሉትን ወንጀልና የክፋት ሥራ በተለይ በአማራው ላይ አድርሰው እነሱም በተራቸው ሒሣባቸውን አገኙ፡፡ ገናም ያገኛሉ፡፡ የሙሽቱን ቀምሰዋል፤ ዋናው ይቀራቸዋል፡፡

ከነሱም በፊት እዚህ ግባ የማይባል መንግሥቱ ኃ/ማርያም የተባለ የመስመር መኮንን በመፈንቅለ መንግሥት ወደሥልጣን ወጥቶ ሀገራችንን ለ17 ዓመታት በዕውር ድምብር ሲገዛ ቆዬ - ልክ እንደአቢይ አህመድ ሁሉ ሥልጣኔን ይቀናቀናሉ ብሎ የሚጠራጠራቸውን የተማሩና የበቁ ዜጎችን ሁሉ በጥይት እያጨደ፡፡ ጓደኞቹ ከአካባቢያችን ይራቅ ብለው በኮሚቴነት መርጠው የላኩት ያ ሰው ድንገት ሳይታሰብ ላይ ወጣና ሀገርን መቀመቅ ከተተ፡፡ ቁጭ ብለን የምንሰቅለው ሁሉ ቆመን ማውረድ እያቃተን ብዙ ጊዜ ጉድ ተሠራን፡፡ ያ ሰው ልክ እንደኔ አሁን ድረስ ለጉድ ጎልቶት እዚህ ግባ የማይባል መሽረፊት(ማራገቢያ) ሻጭ ሀገርን እንደከብት እየገረፈ ሲነዳ ለማየት በቃ፡፡ በመሠረቱ መሽረፊት መሸጥ ነውር ሆኖ ሳይሆን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ቤተሰባዊ አስተዳደግም ትልቅ ስንሆን በሚኖረን የስብዕና ይዘትና ጥራት ወሳኝ መሆኑን ለመጠቆም ነው፡፡ “ከሰው መርጦ ለሹመት፣ ከእንጨት መርጦ ለታቦት” መባሉም ለዚህ ነው፡፡ ለሀገር አመራር አስተዳደግና ሃይማኖታዊ የሞራል ዕሤቶች ዳራ ወሳኝ መሆናቸውን መዘንጋት የለብንም፡፡ የዐይኑን ቀለም የሚጠላውን ዜጋ ሁሉ ባልተወለደ አንጀት በጥይት የሚቆላ ዐረመኔ መሪ፣ መሪ ሊሆን አይገባም፡፡

ኢትዮጵያ ሀብታም ሀገር ናት፡፡ ሰው አላጣችም፡፡ ግን ሾተላይ አለባት፡፡ ሊጠቅሟት የሚችሉ ልጆቿን ቅርጥፍ አድርጋ እየበላች ከይሲዎቹን ወደላይ ታወጣለች፡፡ ያኔ ሀገር ትጫጫለች፤ ሕዝብም ይጎሳቆላል፡፡ ያደላቸው ሀገራት ሕዝባቸውን በቀን አምስትና ስድስቴ ከመመገብ አልፈው ተረፈ ምርታቸውን ለባህር ዓሣዎች ይደፋሉ፤ ለድሃ ሀገራትም ይልካሉ፡፡ የኛዎቹ እርጉማኖች ግን በቀን አንዴም መመገብን ይከለክሉንና ከሰው በታች ያደርጉናል - እነሱ እየጠገቡ፡፡ ይህን መሳይ ድሃ ሕዝብ መምራት እንዴት እንደሚያረካቸው ባላውቅም እነዚህ ሰዎች የሌሎች ሀገራትን የሕዝብ አስተዳደር ጥበብና ችሎታ መረዳትና ራሳቸውን ከዓለም ጋር ማስተካከል የማይፈልጉ በመሆናቸው ሥነ ተፈጥሯቸውን ለማወቅ በጣም እጓጓለሁ፡፡ መቼም ቢሆን እነዚህ ሰዎች - ሰዎች ማለት ከተቻለ ነው ለዚያውም - ጤነኛ ናቸው ማለት አንችልም፡፡ የተራበንና የተጎሳቆለን ሕዝብ መምራት እንዴት ሊያኮራ ይችላል?

ለማንኛውም መጪውን ዘመን መልካም የነጻነት ዘመን ያደርግልን፡፡ አማራው በርታ፡፡ የኢትዮጵያ ፋኖ በርታ፡፡ በነገራችን ላይ ከጨለማው የአቢይ አህመድ ትብታባም የዲያቢሎስ መንግሥት የሚወጡ ዜጎችን አናሸማቃቸው፤ በፍቅር እንቀበላቸው፡፡ ከጥፋት ወደ ልማት ለመመለስ የጊዜ ገደብ የለውም፡፡ ዋናው ክልብ ተፀጽቶ መመለሱ ነው፡፡ ስለሆነም ከክፋትና ከድግምታዊ አንደርብ  በየትኛውም ጊዜ ቢሆን ነጻ መውጣት ይቻላልና እነሱን ማሳቀቅ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል፡፡ እርግጥ ነው - ከአቢይ ጎራ የሚኮበልሉ ወገኖችን የሚነቅፉ ሰዎች በጠላት ወገን የሚላኩ ተከፋዮች ሊሆኑ እንደሚችሉ መጠራጠር አይከፋም፡፡ በትግል ወቅት አጋዥ አይጠላም፡፡ እውነት መሆኑን ግን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ ለአፍራሽ ተልእኮ ከመጡ ችግር ነው፡፡ ውስጥን ማጥራት እንዳለ ሆኖ አዳዲስ መጪዎችን ጤናማነታቸውን ማጣራት መጥፎ አይደለም፡፡ በተረፈ በኔ ይሁንባችሁ ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!! በቅርብም ነጻ እንወጣለን፡፡ የኢትዮጵያ አምላክ እንኳን ከፎከረ ከወረወረም ያድናልና በዚህ አንጠራጠር፡፡ ይሁንና - ልድገመው - ይሁንና በከተሞች በስፋት የሚታየው ሶዶም ወገሞራዊ አስረሽ ምቺው እንዲቀር፣ ከቤተ መንግሥትና ከቤተ አምልኮቶች ጀምሮ ከላይ እስከታች በምዕራባውያን የተዘረጋው የሴቴኒዝም እምነት እንዲጋለጥና ሕዝባችን ከጥፋትና ከሙስና እንዲታቀብ አጥብቀን እንጸልይ፡፡ ሀገራችን የቀራት ብቸኛ የነጻነት መንገድ ፈጣሪ ነውና ሁላችንም ከየገባንበት የክፋት አዘቅት ወጥተን ወደላይ እንጩህ፡፡ ይህን የምለው በነፃነታችን መምጣት ተጠራጥሬ ሳይሆን የመከሰቻው ጊዜ እንዲያጥርና በቶሎም እንዲመጣልን ከማሰብ አንጻር ነው፡፡ እንጂማ ዐውሬው አንገቱ ሊያዝ የቀረው ጊዜ በጣም ትንሽ  ነው ፡፡ ምኞት አይደለም፤ እውነት ነው፡፡ በጣም የተንቀዠቀዠውም ዘመኑ አጭር መሆኑን ስለተረዳ ነው፡፡….

Ethiopian Semay