ብሔርተኝነት የሰው
ልጅ የኩፍኝ በሽታ ነው
የዘመነ ካሴ ታጣቂ በመምህራንና በፋኖ ታጋዮች ላይ የግድያና የሽብር ድርጊት ሲፈጽሙ የጎጃምና የጎንደር ምሁራን ድጋፍ
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay 4/15/25
በዚህ የታላቁ
እስከንድር ንግግር ልጀምር፡
<<
የብሄር ስም እና ማንነታችን ያገኘነው የዘር ማጥፋት ሰለባ ከሆኑ ሰዎች ነው። የእኛ ትልቁ ተልዕኮ እና ራዕይ የዘር ማጥፋት መከላከል
ነው>> Sep 8, 2023 ከጄፍ ፒርስ ቃለ መጠይቅ።
ፖለቲካና
ሥልጣኔ ምንድ ናቸው?
ፖለቲካ ‘ሰዎች ኑሮአቸውን ለማሻሻል’ የሚጠቀሙበት መወጣጫ መሰላል ነው። ሥልጣኔ
ግን የአረመኔነትን ተቃራኒ የሚገልጽ ‘የዓዕምሮ ብስለት’ ነው። ታዲያ በሥልጡን አካሄድና ትእግስት በመራመድ ሚዛን የደፋውን እስክንድር
ነጋ ላይ ከአንድ አመት በላይ ያላባራ የስም ማጥፋት ዘመቻና ፋኖ ብሎ ራሱን የሚጠራ ከወረበላው የጎጃም ዘመነ ፋኖ ቡድን የግድያ
ዛቻ ሲስተጋባበት ነበር።
የሥም ማጥፋት
ዘመቻው ተግባራዊ ቢሆንም “ግድያ” ግን በፈጣሪ ተከላካይነት ብተአምር እስካሁን አለ። አሳዛኙ ግን እርሱን መግደል አልመች ሲላቸው
በምሪነት ያሉትን የእስክንድር ጓዶች እያደቡ በመግደልና በማፈን ላይ ናቸው።
ይህ አደገኛ
የዘመነ ወረበላ ቡድን በግድያና አፈና እንዲሁም በከበባ የሚያሰማራቸው መካከል “ሳሚ” በመባል የሚጠራ እዩኝ እዩኝ ባይ “ሰድ” እና “ናርሲስት” “ቀይ ቆብ ለባሽ” ሕዝብን እያስፈራራ
በዘመነ አንሰለፍም የሚሉትን “በውግያ ሳይሆን” አድብቶ ከብቦ በማደንና በማስገደል በሽብር ሥራ በመሰማራት ትግሉ በነዚህ “ጮርቃዎች”
እጅ ወድቆ ተጠልፎ ተበላሽቷል።
ላታምኑ ትችሉ
ይሆናል፤ አምና በወቅቱ አስቀድሜ እነዚህ ጮርቃዎች “ፖለቲካውና ጠመንጃው ከተቆጣጠሩት”
በጫካ ሕግና ባሕሪ እየተመሩ “ሥድ” እንደሚሄዱ ተናግሬ
ነበረ። በወቅቱ ጥቂት ጎጃሜዎች ተንጫጩብኝ። አሁን እየሆነ ያለው ያ ሥድነትና አጉራዘለልነት እያደገ መስመሩ ስቷል።
ይህ ሁሉ
ብልሽት እያዩ ዝም የሚሉና የነዚህ የመንደር ‘’አጉራ ዘለሎች” ደጋፊ የሆኑ “ካልቶቻቸው” ሳይሆኑ የጎንደርና የጎጃም ምሁራን ተጠያቂዎች
ናቸው።
ጎልተው ወደ መድረክ በመውጣት ታዋቂነትን ያተረፉ የጎጃምና የጎንደር ታዋቂ ምሁራንን የሚከተሉትን ለናሙና እንመልከት።
ባለፉት አመታት ወደ መድረክ በመውጣት ታዋቂነትን ያተረፉ የጎጃምና የጎንደር
ታዋቂ ምሁራን መካከል ጥቂቶቹ በኦሮሙማው ሥርዓት ታፍነው የታፈኑበትን
መዝጊያን ሰብሮ የሚያስፈታቸው አጥተው በእስር ሲማቅቁ፡
ውጭ አገር
በስደት የሚኖሩት የጎጃም መሁራን እንደ ፕሮፌሰር ሃብታሙ ተገኘ የመሳስሉት ደግሞ (ሃበታሙ ተገኘ የልድቱ አያሌውን የቤተሰቦቹ
ንብረትና ኑሮ 7 ትውልዱ ወደፊት ንብረታቸው እየተወረሰ አምሐራነታቸው ተነጥቀው እንዲወገዙ የሰበከ። ኮሎኒያሊስቱ ኦሮሙማው አብይ
አሕመድም ያንን ምክር ሰምቶ የልደቱን ንብረትና መኖርያ ውርሶታል (ዛሬ ሰሞኑን) ፤
እንዲሁም እንደ የጎንደሩ የጋይንት ተወላጅ ተክሌ የሻው የመሳሰሉ
ጎንደሬዎችም (ተክሌ የሻው ‘የፋኖ አመራር ለመሆን 7 ትውልዱ ከሌላ ነገድ ያልተቀላቀለ “የጠራ ደም” ያለው አማራ መሆን አለበት በማለት ‘ናዚያዊ የደም ጥራት’ ወትዋች) ስንመለከት ለጎጃመና
ለጎንደር ጮርቃዎቹ ሥድነት አስተዋጻኦ አለበት።
እነኚህ ብቻ አይደሉም፦
በታሪክና በበቃ የማሕበራዊ ሙግት ተመራማሪና የተዋጣለት ምክንያታዊ ተሟጋች “የነበረው” ጎጃሜው አቻምየለህ ታምሩ እና የመሳሰሉ የጎጃምና የጎንደር ተወላጅ ምሁራን በስንት ጉትጎታ ወደ ትጥቅ ፍልምያ የገቡት የተለያዩ ፋኖ ድርጅቶች አንድ ያደርጔቸዋል ብለን ተስፋ ስንጥልባችውና በተለይም ዘመነ የተባለው የጎጠኛነት ባሕሪና ፋሺስታዊ የሥልጣን ጉጉት ያደረበትና የግድያ ሱስ ያደረበት ደም የጠማው ምክትሉ “አስረስ ማረ” በአምሐራ ነፃ አውጭነት ስም እየተከተሉት ያለው መንገድ በሌላ የፋኖ ድርጅት የተሰማሩትን የፋኖ መሪዎችንና ንጹሃን መምሕራን ጋዜጠኞችን ማፈንና የግድያ ወንጀል ሲፈጽሙ የጎጃም ምሁራን ዝም ማለታቸውና ከዝምታቸውም አልፈው “የዚሀ ወመኔ” ታጣቂ ቡድን ደጋፊዎች ሆነው ማየት እጅግ ተገረምኩ።
ታስታወሱ
እንደሆን በበርካታ ትችቶቼ የፋኖ ትግል ተጠልፏል ስል ብዙ ሰው ልብ ያለው አልነበረምና ይኼው ዛሬ ብዙ የግድያ
ወንጀልና ሽብር እየተፈጸመ የትግሉ መነሻ ስቶ ይገኛል። ይህ ሁሉ መዘዝ መነሻ የሆነው “ስሜተኛ ብሔረተኛነት” ነው።
ዓለም የሚያውቃቸው
ምሁራን ሰለ ስሜተኛ ብሔረተኛነት ሲገልጹ እንዲህ ይላሉ፦ “Nationalism is infantile disease.
It is the measles of mankind” (Scientist Albert Einstein) “ብሔርተኝነት የጩጬነት ሕሊና በሽታ ነው። ባጨሩ “ብሔርተኝነት
የሰው ልጅ የኩፍኝ በሽታ ነው” የላል ሳይንቲስቱ አልበርት አንስታይን።
የአልበርት አነስታይን ጥቅስ በመጥቀስ በ12/25/2024 የጻፍኩት ትችት ለተመራማሪ መሁራችን
ለድሮ ወዳጄ ለአቻምየለህ ታምሩ ነበር።
በጎጃሜነት ትሥስር የጎጃም ፋኖ ወረበላ ፋሺስቶችን ከሚደግፉ የጎጃም መሁራኖች ውስጥ አንዱ
አቻምየለህ ታምሩ ነው።
« አቻም ወገንተኛ ሆኖ ለአውራጃው//ጠ/ግዛት ልጆቹ በመወገን ማስረጃ ማቅረብ በማይችልበት ውንጀላው እስክንድርን ብቻ ለይቶ ጥላሸት ቀብቶት መኖሩን ይታወሳል፡
እንዲህ እያለ፡
“ቀደም
ብሎ እስክንድር ነጋ ላይ አንድ ነገር ቢሰራ ኖሮ በአርበኛ አሰግድ መኮንን ላይ የደረሰው መከራ ላይደርስ ይችል ነበር” በማለት
ምስኪኑን እስክንድርን ይወነጅለዋል፡፡
“አንድ ነገረ ቢሰራ ኖሮ” የሚለው እስክንድርን
“በሞት”
ወይስ ከትግሉ ማስወገድ? አልገባኝም! በማለት ጠይቄ ነበር።
ያኔ እንዲህ ያልኩበትም “አቻም ወገንተኛ ሆኖ ለአውራጃው/ጠ/ግዛት ልጆቹ በሚያዳላ መልኩ ማስረጃ ማቅረብ በማይችልበት ውንጀላው እስክንድርን ብቻ ለይቶ ጥላሸት ቀብቶታል። ምክንያቴንም ሳቀርብ
ለትውስታችሁ መከራከርያየ እንዲህ የሚል ነበር፡
«የሚገርመው አሰግድ
መኮንን እጅ ስጥ ሲባል እንደ የጦር መሪነቱ ራሱን በሳይኖይድ ወይንም ሽጉጡን ጠጥቶ መስዋእት ላለመሆን ፈቅዶ
ለአብይ አሕመድ አሽከሮች እጁና መሳሪያውን ያሰረከበን የአሰግድ መኮንን
እጅ መስጠት ምርጫ “እስክንድርን ዋና ተጠያቂ አድረጎ መወንጀል” የእናቴ ቀሚስ አደናቀፈኝ ዓይነቱ የነ አቻመየለህ መሸፈኛ ‘’አርቲ ቡርቲ” የቀረበበት ዋና ምክንያት አቻምየለህና
መሰሎቹ እስክድር ላይ የሚዘባበኑበት ምክንያት አላቸው።
ይኸውም የአሰግድ መኮንን ሽንፈት መደበቅ ነው። አሰቀደሞ ጥንቃቄ ያላደረገ ራስን ለመከላከል
፤ ጠላት እጅ ቢወድቅ ፤ አንድ መሪ ቢያዝ ምስጢር እንዳያወጣ ሽጉጡን መጠጣት ባይችል እንኳ ቅጽበታዊ መስዋእትነት ለመቀበል “በኪሱ”
ምን አማራጭ (እንደ የሳዮናይድ ከኒን መርዝ የመሳሰሉ) መያዝ እንዳለበት የመጀመሪያው “ሀ ሁ” የሽምቅ ጦር አዋጊና ሃላፊ’ ትምሕርት
የመሰውያ ሕግ ማወቅ/መማር ነበረበት። ይህንን “ሀሁ” የማያውቅ
የሽምቅ ተዋጊ መሪ የሆነው አሰግድ ልምድና ሥልጠና” ያልነበረው ሰለነበር ሰተት በሎ እጁን ለጠላት ሲያሰረክብ ፤ እነ አቻምየለህ
ያቺን ድክመቱን ላለማጋለጥ ፤ ደክመቱና ተጠያቂነቱ ለእስክንድር ጭነውበታል።» ነበር ያልኩት።
አቻምየለህ
እስክንድር ላይ ጥላሸት በመቀባቱ ውርጅቢኝ ብቻ ሳይውሰን “እስክንድርን ጸረ አማራ አደረጎ በመወንጀል” ፤የጀርባ ታሪኩ ጸረ
አማራ ነው ሲል ሲከሰው ታያላችሁ፡
አቻምየለህ ታምሩ እስክንድርን እንዲህ ሲል ይወነጅለዋል፡-
<<የኋላ ታሪኩና በአማራው የኅልውና ተጋድሎ ውስጥ ሊያራምደው በሚሞክረው ጸረ አማራ እሳቤው>>
በማለት ይወነጅለዋል፡፡
የእስክንድር ጸረ አማራ የኅልውና የኋላ ታሪኩ
አቻምየለህ ማስረጃ አላቀረበም። አቻምየለህ የአማራ ተቆርቋሪ እስክንድር
ግን ጸረ አማራ
የሚሆንበት በታአምርም መባል ያልነበረበት ጮርቃነት ነው።
አቻምየለህ ከትልቁ ኢትዮጵያዊ ማማ ወርዶ ወደ ጠባብ ጎጃምነት ወርዷል።ለእነ ዘመነ አጉራዘለል ባሕሪ ጣራ መንካት የእነ አቻም ድርሻ አለው።<<ለአማራ አሳቢና እምባ አቅራሪ እሰክንድር ሳይሆን ፤ እኔ ነኝ ፤ የአማራ አሳቢና ተከላካይ እኔና ዘመነ ካሴ ነን >> በሚል ውስጠ ገለጻ
እስክንድር የአማራ ሕልውናን ለማጥፋት አስቦበት የመጣ በማለት
ይወነጅለዋል፡፡
አቻም ከላይ እንደተመለከታችሁት አማራ ማለት እኛ እንጂ
እስክንድር የአማራን ሕልውና በመጻረር የሚታወቅ <<የኋላ ታሪኩ>> ሳይመረመር የተቀላቀለን
የሚለው የአቻምየለህ ጽሑፍ የሚያሳየን አቻመየለህ ትምክሕተኛ ወደ ሆነው ወደ
ማፊያዊና ማፈሪያ ካምፕ ተፈጥፍጦ ሊወድቅ
እንጥልጥል ላይ እንደሆነ ነው (if not
already) የታዘብኩት። ያሳዝናል።
ካልሆነማ የእስክንድር <<የኋላ ታሪኩ>>
“አምሐራ
የዘር ማጥፋት እየተፈጸመበት ነው” እያለ በወስጥም ካገር ውጭም በዓለም ሙሉ እየዞረ ለብዙ አመታት ሲታሰር ፤ ሲፈታ ፤ ሲገረፍና ሲታገል፤ “የግራኝ አሕመዱ” የአብይ አሕመድ ጉግ ማንጉግ ፖሊሶችና ገራፊ ሰላዮች ፤ እንዲሁም አዲሰ አበባ ውስጥ በጸረ
አማራ የተቀረጹ የወሃቢያ ኦሮሚያ እስላማዊ ዱርየዎች ሽጉጥ ይዘው በሞተር ሳይክል ሲፍልጉትና ብዩቱብ ቲቪ እየታዩ ቁምስቅሉን ሲያሳዩት ፤ በወያኔም አኦሮሙማም
ሲታሰር ሲፈታ ፤ አቻምየለህ ግን እዚህ እኛ ጋር ትምሕርቱን ሲያጎለብት ነበር። የሚገርም ውንጀላ ነው ፤ አይደለም እንዴ?
አቻምየለህ ያ አልበቃ
ብሎት “ተፈራ ማሞ” የተባለ “የወያኔ” ጡት እየጠባ ያደገ ሻዕቢያይቱን ሚስቱን እንኴ
በቅጡ ተቆጣጥሮ አደብ ሊያስይዛት ያልቻለ ተፈራ ማሞን “የአምሐራ መሪ ይሁን ብሎ ዘመቻ ጀምሯል።
ተፈራ ማሞ
ማለት “አምሐራ እየመጣበት ያለው ጉድ የ16ኛው ክ/ዘ ከበባና አደጋ ነው” ብሎ ካሕኑም ምሁሩም
“ለክቡር መሰዋእትነት” እንዲዘጋጅ ጥሪ ያደረገ የዛሬ ፋኖ ችግኝ የተከለ ጀግናው አሳምነው ጽጌን “የሕሊና በሽተኛ ፤ ዕብድ ሰው” በማለት ጀግና አዋራጅ ለሆነው አፍቃሬ ሻዕቢያው
ተፈራ ማሞን የአምሐራን ፖለቲካና ወታደራዊ መሪ እንዲሆን ዘመቻ አስፈጻሚ ሆኖ ያየነው ጎጃም ያበቀለቺው ምሁር ነው።
ተፈራ ማለት
የወያኔና የሻዕቢያ ታጣቂ ቡችላ የነበረ ከሻዕቢያና ከወያኔ ታጣቂዎች ጋር ሆኖ መንገድ እየመራ “ከወሎ እስከ አዲስ አበባ” ድረስ
አገራቸውን ሲከላከሉ የነበሩት መሁራንና አምሐራ ገበሬዎች እያደነ ፤ እንዲሁም የእምየ ኢትዮጵያ ወታደሮችን ሲገድል የነበረ፤ መጨረሻም
እነዚያ ብርቅየ ግፉአን ከነ ቤተሰቦቻቸው በረንዳ አደር ሲሆኑ ለባነዳነቱ “የነሱን ቦታ የተሰጠው” “ለባንዳነቱ ያልተጸጸት ባንዳ
ነው ተፈራ ማሞ ማለት።
የአቻምየለህ
ብርቀየ “መሪ” ተፈራ ማሞ የፀረ አምሐራው የኢሳያስ አፈወርቂ አድናቂና ከማድነቁ የተነሳ ፎቶግራፉን ከቤቱ ግድግዳ ትራስ ላይ
ተለጥፎ ዩቱብ “ቲ ቪ” ላይ እንድናይለት ያደረገ ማፈርያ ነው።
ተፈራ ማለት
ወደ ውጭ አገር ለመሸሽ እግሩ ሳይታመም ታመምኩኝ ብሎ የሚወሰልት ሲጨንቀው ወደ ፋኖ የተቀላቀለ፤“ሚስቱን መቆጣጠር የማይችል” “አፍቃሬ
ሻቢያነቱ/አፈቃሬ ኢሳያስነቱን” ለመግለጽ አምሐራ ሕልውናውን
ለመጠበቅ ከሻቢያ ጋር ማበር እንዳለበት በተመስገን ደሳለኝ “ፈትሕ” መጽሔት
ላይ ሳይደብቅ የነገረን ሰው ነው።
የጎጃምና
የጎንደር ምሁራን “አይካን መሪያችን” የሚሉት “የሻቢያው ግርፍ” ዘመነ ካሴ ብቻ አይደለም፤ ተፈራ ማሞ የተባለ
ማፈርያም ነው። ተፈራ ማሞን ስታነሱ “ሥርዓቱ የትም እንደማያደርስ ተሎ የነቃው ጀግናው አሳምነውን አስታውሱ።
አብይ አሕመድ
የሚያስተላልፋቸውን ጸረ አምሐራ ክንዋኔዎችን
ለማስፈጸም አስር ጊዜ ስብሰባ ሲጠሩትና ሲወተውቱት
የነበሩት ከኦሮሙማ ፋሺስቶች ጋር ጠጅ ለማንቃረር ያደሩ ቅጥረኛ ባንዳዊያን ብአዲኖችን ያጋደመ “የወንዶች ልክ” “በአሳምነው ጽጌ ገናናነትና ምጥቀትነት የሚቀና”
ቀናተኛና ሐሜተኛ ሰው ተፈራ ማሞን ለማንገስ እያነፈነፉ ዘመቻ ማቀንቀን የሚገርም መስተንክር ነው።
የጎጃምና
የጎንደር መሁራን ለምን እንደዘቀጡ አልገባኝም። አቻምየለህ ታመሩ “አቃጣሪው የወያኔ ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞን እንዲሀ ሲል ያሞካሸዋል፤
«አማራ በዚህ
ወቅት የሚያስፈልገው መሪ እንደ ተፈራ ማሞ አይነት በአማራ ላይ የተጋረጠውን የኅልውና አደጋ እንደ እጁ መዳፍ አብጠርጥሮ የሚያውቅ አራት ዐይና ብቻ ነው።”
በማለት በሚያስቅና
በሚያስደነግጥ አባባል አፍቃኴ “ሐምተኛና ስም አጥፊው” ተፈራ ማሞን “የአመሐራ መሪ” አድርጎ “ይምራን” ብሎ “መሪ አድርጎ” ሹሞታል።
“ዝገርም እዩ!!” አለ ትግሬ።
ከማንም በፊት አሰቀድሞ በየፋ “አምሐራ ላይ የተጋረጠውን የኅልውና አደጋ እንደ እጁ መዳፍ አብጠርጥሮ ያወቀውን ብ/ጀ አሳምነው ጽጌን “ሲዘልፍ
የነበረ “ሐምየተኛና አድር ባይ ፈሪ” ዛሬ ተፈራ ማሞን አቻምየለህ ታመሩ በሚያስቀን አገላለጽና ሹመት “ በአማራ ላይ
የተጋረጠውን የኅልውና አደጋ እንደ እጁ መዳፍ አብጠርጥሮ
የሚያውቅ አራት ዐይና” ሲል አሞካሽቶታል።
እነዚህ ምሁራን
ምን አዚም ነው የዞረባቸው ይህንን ሐሜተኛ ሰው እንዲህ ሊያሞካሹትና
መሪያችን ነህ ብለው ሰማየ ሰማያት የሰቀሉት? አልገባ አለኝ።
ጎጃም የበቀለው
የዘመነ መንደርተኛ የፋኖ ፋሺስታዊ ቡድን መረን ልቅቆ በጫካ ሕግ በሕገ አራዊት በደመነብስ እየተመራ ንግሥና እና ሥልጣን ስንወለድ “ከ ዲ
ኤን ኤ” የተቸረነ ልዩ ፍጡራን ነን ፤ በሚል ናዚያዊ ፈለግ
እየተከተለ የዘመነ ካሴ ታጣቂ ቡድን በንጹሃን ተማሪዎች ፤መምህራንና በፋኖ ታጋዮች ላይ የግድያና የሽብር ድርጊት ሲፈጽም የጎጃምና
የጎንደር ምሁራን በድጋፍ ሰጪነት የቆሙት ሁሉ በታሪክ ተጠያቂዎች ናቸው።
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian
Semay