Tuesday, April 15, 2025

ብሔርተኝነት የሰው ልጅ የኩፍኝ በሽታ ነው የዘመነ ካሴ ታጣቂ በመምህራንና በፋኖ ታጋዮች ላይ የግድያና የሽብር ድርጊት ሲፈጽሙ የጎጃምና የጎንደር ምሁራን ድጋፍ ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 4/15/25

 

ብሔርተኝነት የሰው ልጅ የኩፍኝ በሽታ ነው

የዘመነ ካሴ ታጣቂ በመምህራንና በፋኖ ታጋዮች ላይ የግድያና የሽብር ድርጊት ሲፈጽሙ የጎጃምና የጎንደር ምሁራን ድጋፍ

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay 4/15/25

በዚህ የታላቁ እስከንድር ንግግር ልጀምር፡

<< የብሄር ስም እና ማንነታችን ያገኘነው የዘር ማጥፋት ሰለባ ከሆኑ ሰዎች ነው። የእኛ ትልቁ ተልዕኮ እና ራዕይ የዘር ማጥፋት መከላከል ነው>> Sep 8, 2023 ከጄፍ ፒርስ ቃለ መጠይቅ።

ፖለቲካና ሥልጣኔ ምንድ ናቸው?

 ፖለቲካ ‘ሰዎች ኑሮአቸውን ለማሻሻል’ የሚጠቀሙበት መወጣጫ መሰላል ነው። ሥልጣኔ ግን የአረመኔነትን ተቃራኒ የሚገልጽ ‘የዓዕምሮ ብስለት’ ነው። ታዲያ በሥልጡን አካሄድና ትእግስት በመራመድ ሚዛን የደፋውን እስክንድር ነጋ ላይ ከአንድ አመት በላይ ያላባራ የስም ማጥፋት ዘመቻና ፋኖ ብሎ ራሱን የሚጠራ ከወረበላው የጎጃም ዘመነ ፋኖ ቡድን የግድያ ዛቻ ሲስተጋባበት ነበር

የሥም ማጥፋት ዘመቻው ተግባራዊ ቢሆንም “ግድያ” ግን በፈጣሪ ተከላካይነት ብተአምር እስካሁን አለ። አሳዛኙ ግን እርሱን መግደል አልመች ሲላቸው በምሪነት ያሉትን የእስክንድር ጓዶች እያደቡ በመግደልና በማፈን ላይ ናቸው።

ይህ አደገኛ የዘመነ ወረበላ ቡድን በግድያና አፈና እንዲሁም በከበባ የሚያሰማራቸው መካከል “ሳሚ” በመባል የሚጠራ እዩኝ እዩኝ ባይ “ሰድ” እና “ናርሲስት “ቀይ ቆብ ለባሽ” ሕዝብን እያስፈራራ በዘመነ አንሰለፍም የሚሉትን “በውግያ ሳይሆን” አድብቶ ከብቦ በማደንና በማስገደል በሽብር ሥራ በመሰማራት ትግሉ በነዚህ “ጮርቃዎች” እጅ ወድቆ ተጠልፎ ተበላሽቷል።

ላታምኑ ትችሉ ይሆናል፤ አምና በወቅቱ አስቀድሜ እነዚህ ጮርቃዎች “ፖለቲካውና ጠመንጃው ከተቆጣጠሩት” በጫካ ሕግና  ባሕሪ እየተመሩ “ሥድ” እንደሚሄዱ ተናግሬ ነበረ። በወቅቱ ጥቂት ጎጃሜዎች ተንጫጩብኝ። አሁን እየሆነ ያለው ያ ሥድነትና አጉራዘለልነት እያደገ መስመሩ ስቷል።  

ይህ ሁሉ ብልሽት እያዩ ዝም የሚሉና የነዚህ የመንደር ‘’አጉራ ዘለሎች” ደጋፊ የሆኑ “ካልቶቻቸው” ሳይሆኑ የጎንደርና የጎጃም ምሁራን ተጠያቂዎች ናቸው።

ጎልተው ወደ መድረክ በመውጣት ታዋቂነትን ያተረፉ የጎጃምና የጎንደር ታዋቂ  ምሁራንን የሚከተሉትን ለናሙና እንመልከት።

 ባለፉት አመታት ወደ መድረክ በመውጣት ታዋቂነትን ያተረፉ የጎጃምና የጎንደር ታዋቂ  ምሁራን መካከል ጥቂቶቹ በኦሮሙማው ሥርዓት ታፍነው የታፈኑበትን መዝጊያን ሰብሮ የሚያስፈታቸው አጥተው በእስር ሲማቅቁ፡

ውጭ አገር በስደት የሚኖሩት የጎጃም መሁራን እንደ ፕሮፌሰር ሃብታሙ ተገኘ የመሳስሉት ደግሞ (ሃበታሙ ተገኘ የልድቱ አያሌውን የቤተሰቦቹ ንብረትና ኑሮ 7 ትውልዱ ወደፊት ንብረታቸው እየተወረሰ አምሐራነታቸው ተነጥቀው እንዲወገዙ የሰበከ። ኮሎኒያሊስቱ ኦሮሙማው አብይ አሕመድም ያንን ምክር ሰምቶ የልደቱን ንብረትና መኖርያ ውርሶታል (ዛሬ ሰሞኑን) ፤

 እንዲሁም እንደ የጎንደሩ የጋይንት ተወላጅ ተክ የሻው የመሳሰሉ ጎንደሬዎችም (ተክሌ የሻው ‘የፋኖ አመራር ለመሆን 7 ትውልዱ ከሌላ ነገድ ያልተቀላቀለ “የጠራ ደም” ያለው  አማራ መሆን አለበት በማለት ‘ናዚያዊ የደም ጥራት’ ወትዋች) ስንመለከት ለጎጃመና ለጎንደር ጮርቃዎቹ ሥድነት አስተዋጻኦ አለበት።

 እነኚህ ብቻ አይደሉም፦

 በታሪክና በበቃ የማሕበራዊ ሙግት ተመራማሪና የተዋጣለት ምክንያታዊ ተሟጋች “የነበረው” ጎጃሜው አቻምየለህ ታምሩ ና የመሳሰሉ የጎጃምና የጎንደር ተወላጅ ምሁራን በስንት ጉትጎታ ወደ ትጥቅ ፍልምያ የገቡት የተለያዩ ፋኖ ድርጅቶች አንድ ያደርጔቸዋል ብለን ተስፋ ስንጥልባችውና በተለይም ዘመነ የተባለው የጎጠኛነት ባሕሪና ፋሺስታዊ የሥልጣን ጉጉት ያደረበትና የግድያ ሱስ ያደረበት ም የጠማው ምክትሉ “አስረስ ማረ” በአምሐራ ነፃ አውጭነት ስም እየተከተሉት ያለው መንገድ በሌላ የፋኖ ድርጅት የተሰማሩትን የፋኖ መሪዎችንና ንጹሃን መምሕራን ጋዜጠኞችን ማፈንና የግድያ ወንጀል ሲፈጽሙ የጎጃም ምሁራን ዝም ማለታቸውና ከዝምታቸውም አልፈው “የዚሀ ወመኔ” ታጣቂ ቡድን ደጋፊዎች ሆነው ማየት እጅግ ተገረምኩ።

ታስታወሱ እንደሆን በበርካታ ትችቶቼ የፋኖ ትግል ተጠልፏል ስል ብዙ ሰው ልብ ያለው አልነበረምና ይኼው ዛሬ ብዙ የግድያ ወንጀልና ሽብር እየተፈጸመ የትግሉ መነሻ ስቶ ይገኛል። ይህ ሁሉ መዘዝ መነሻ የሆነው “ስሜተኛ ብሔረተኛነት” ነው።

ዓለም የሚያውቃቸው ምሁራን ሰለ ስሜተኛ ብሔረተኛነት ሲገልጹ እንዲህ ይላሉ፦ “Nationalism is infantile disease. It is the measles of mankind” (Scientist Albert Einstein) “ብሔርተኝነት የጩጬነት ሕሊና በሽታ ነው። ባጨሩ “ብሔርተኝነት የሰው ልጅ የኩፍኝ በሽታ ነው የላል ሳይንቲስቱ አልበርት አንስታይን

የአልበርት አነስታይን ጥቅስ በመጥቀስ በ12/25/2024 የጻፍኩት ትችት ለተመራማሪ መሁራችን ለድሮ ወዳጄ ለአቻምየለህ ታምሩ ነበር።

በጎጃሜነት ትሥስር የጎጃም ፋኖ ወረበላ ፋሺስቶችን ከሚደግፉ የጎጃም መሁራኖች ውስጥ አንዱ አቻምየለህ ታምሩ ነው።

« አቻም ወገንተኛ ሆኖ ለአውራጃው//ጠ/ግዛት ልጆቹ በመወገን ማስረጃ ማቅረብ በማይችልበት ውንጀላው እስክንድርን ብቻ ለይቶ ጥላሸት ቀብቶት መኖሩን ይታወሳል፡

እንዲህ እያለ፡

ቀደም ብሎ እስክንድር ነጋ ላይ አንድ ነገር ቢሰራ ኖሮ በአርበኛ አሰግድ መኮንን ላይ የደረሰው መከራ ላይደርስ ይችል ነበር” በማለት ምስኪኑን እስክንድርን ይወነጅለዋል፡፡

“አንድ ነገረ ቢሰራ ኖሮ” የሚለው እስክንድርን በሞት” ወይስ  ከትግሉ ማስወገድ? አልገባኝም! በማለት ጠይቄ ነበር።

ያኔ እንዲህ ያልኩበትም “አቻም ወገንተኛ ሆኖ ለአውራጃው/ጠ/ግዛት ልጆቹ በሚያዳላ መልኩ ማስረጃ ማቅረብ በማይችልበት ውንጀላው እስክንድርን ብቻ ለይቶ ጥላሸት ቀብቶታል። ምክንያቴንም ሳቀርብ

ለትውስታችሁ መከራከርያየ እንዲህ የሚል ነበር፡

«የሚገርመው አሰግድ መኮንን እጅ ስጥ ሲባል እንደ የጦር መሪነቱ ራሱን በሳይኖይድ ወይንም ሽጉጡን ጠጥቶ መስዋእት ላለመሆን ፈቅዶ ለአብይ አሕመድ አሽከሮች እጁና መሳሪያውን ያሰረከበን የአሰግድ መኮንን  እጅ መስጠት ምርጫ “እስክንድርን ዋና ተጠያቂ አድረጎ መወንጀልየእናቴ ቀሚስ አደናቀፈኝ ይነቱ የነ አቻመየለህ መሸፈኛ ‘’አርቲ ቡርቲ” የቀረበበት ዋና ምክንያት አቻምየለህና መሰሎቹ እስክድር ላይ የሚዘባበኑበት ምክንያት አላቸው

ይኸውም የአሰግድ መኮንን ሽንፈት መደበቅ ነው አሰቀደሞ ጥንቃቄ ያላደረገ ራስን ለመከላከል ፤ ጠላት እጅ ቢወድቅ ፤ አንድ መሪ ቢያዝ ምስጢር እንዳያወጣ ሽጉጡን መጠጣት ባይችል እንኳ ቅጽበታዊ መስዋእትነት ለመቀበል “በኪሱ” ምን አማራጭ (እንደ የሳዮናይድ ከኒን መርዝ የመሳሰሉ) መያዝ እንዳለበት የመጀመሪያው “ሀ ሁ” የሽምቅ ጦር አዋጊና ሃላፊ’ ትምሕርት የመሰውያ ሕግ ማወቅ/መማር ነበረበት ይህንን “ሀሁ” የማያውቅ የሽምቅ ተዋጊ መሪ የሆነው አሰግድ ልምድና ሥልጠና” ያልነበረው ሰለነበር ሰተት በሎ እጁን ለጠላት ሲያሰረክብ ፤ እነ አቻምየለህ ያቺን ድክመቱን ላለማጋለጥ ፤ ደክመቱና ተጠያቂነቱ ለእስክንድር ጭነውበታል።» ነበር ያልኩት።

አቻምየለህ እስክንድር ላይ ጥላሸት በመቀባቱ ውርጅቢኝ ብቻ ሳይውሰን እስክንድርን ጸረ አማራ አደረጎ በመወንጀል ፤የጀርባ ታሪኩ ጸረ አማራ ነው ሲል ሲከሰው ታያላችሁ፡

አቻምየለህ ታምሩ እስክንድርን እንዲህ ሲል ይወነጅለዋል፡-

 <<የኋላ ታሪኩና በአማራው የኅልውና ተጋድሎ ውስጥ ሊያራምደው በሚሞክረው ጸረ አማራ እሳቤው>>

በማለት ይወነጅለዋል፡፡

የእስክንድር ጸረ አማራ የኅልውና የኋላ ታሪኩ አቻምየለህ ማስረጃ አላቀረበም አቻምየለህ የአማራ ተቆርቋሪ እስክንድር ግን ጸረ አማራ የሚሆበት በታአምርም መባል ያልነበረበት ጮርቃነት ነው

 አቻምየለህ ከትልቁ ኢትዮጵያዊ ማማ ወርዶ ወደ ጠባብ ጎጃምነት ወርዷል።ለእነ ዘመነ አጉራዘለል ባሕሪ ጣራ መንካት የእነ አቻም ድርሻ አለው።<<አማራ አሳቢና እምባ አቅራሪ እሰክንድር ሳይሆን ፤ እኔ ነኝ ፤ የአማራ አሳቢና ተከላካይ እኔና ዘመነ ካሴ ነን >> በሚል ውስጠ ገለጻ እስክንድር የአማራ ሕልውና ለማጥፋት አስቦበት የመጣ በማለት ይወነጅለዋል፡፡

አቻም ከላይ እንደተመለከታችሁት አማራ ማለት እኛ እንጂ እስክንድር የአማራን ሕልውና በመጻረር የሚታወቅ <<የኋላ ታሪኩ>> ሳይመረመር የተቀላቀለን የሚለው የአቻምየለህ ጽሑፍ የሚያሳየን አቻመየለህ ትምክሕተኛ ወደ ሆነው ወደ ማፊያዊና ማፈሪያ ካምፕ ተፈጥፍጦ ሊወድቅ እንጥልጥል ላይ እንደሆነ ነው (if not already) የታዘብኩት። ያሳዝናል

ካልሆነማ የእስክንድር <<የኋላ ታሪኩ>> ምሐራ የዘር ማጥፋት እየተፈጸመበት ነው እያለ በወስጥም ካገር ውጭም በዓለም ሙሉ እየዞረ ለብዙ አመታት ሲታሰር ፤ ሲፈታ ፤ ሲገረፍና ሲታገል፤ “የግራኝ አሕመዱ” አብይ አሕመድ ጉግ ማንጉግ ፖሊሶችና ገራፊ ሰላዮች ፤ እንዲሁም አዲሰ አበባ ውስጥ በጸረ አማራ የተቀረጹ የወሃቢያ ኦሮሚያ እስላማዊ ዱርየዎች ሽጉጥ ይዘው በሞተር ሳይክል ሲፍልጉትና ብዩቱብ ቲቪ እየታዩ ቁምስቅሉን ሲያሳዩት ፤ በወያም አኦሮሙማም ሲታሰር ሲፈታአቻምየለህ ግን እዚህ እኛ ጋር ትምሕርቱን ሲያጎለብት ነበር። የሚገርም ውንጀላ ነው ፤ አይደለም እንዴ?

አቻምየለህ ያ አልበቃ ብሎት “ተፈራ ማሞ” የተባለ “የወያኔ” ጡት እየጠባ ያደገ ሻዕቢያይቱን ሚስቱን እንኴ በቅጡ ተቆጣጥሮ አደብ ሊያስይዛት ያልቻለ ተፈራ ማሞን “የአምሐራ መሪ ይሁን ብሎ ዘመቻ ጀምሯል።

ተፈራ ማሞ ማለት “አምሐራ እየመጣበት ያለው ጉድ የ16ኛው ክ/ዘ ከበባና አደጋ ነው ብሎ ካሕኑም ምሁሩም “ለክቡር መሰዋእትነት” እንዲዘጋጅ ጥሪ ያደረገ የዛሬ ፋኖ ችግኝ የተከለ ጀግናው አሳምነው ጽጌን  “የሕሊና በሽተኛ ፤ ብድ ሰው” በማለት ጀግና አዋራጅ ለሆነው አፍቃሬ ሻዕቢያው ተፈራ ማሞን የአምሐራን ፖለቲካና ወታደራዊ መሪ እንዲሆን ዘመቻ አስፈጻሚ ሆኖ ያየነው ጎጃም ያበቀለቺው ምሁር ነው።

ተፈራ ማለት የወያኔና የሻዕቢያ ታጣቂ ቡችላ የነበረ ከሻዕቢያና ከወያኔ ታጣቂዎች ጋር ሆኖ መንገድ እየመራ “ከወሎ እስከ አዲስ አበባ” ድረስ አገራቸውን ሲከላከሉ የነበሩት መሁራንና አምሐራ ገበሬዎች እያደነ ፤ እንዲሁም የእምየ ኢትዮጵያ ወታደሮችን ሲገድል የነበረ፤ መጨረሻም እነዚያ ብርቅየ ግፉአን ከነ ቤተሰቦቻቸው በረንዳ አደር ሲሆኑ ለባነዳነቱ “የነሱን ቦታ የተሰጠው” “ለባንዳነቱ ያልተጸጸት ባንዳ ነው ተፈራ ማሞ ማለት።

የአቻምየለህ ብርቀየ “መሪ” ተፈራ ማሞ የፀረ አምሐራው የኢሳያስ አፈወርቂ አድናቂና ከማድነቁ የተነሳ ፎቶግራፉን ከቤቱ ድግዳ ትራስ ላይ ተለጥፎ ዩቱ “ቲ ቪ” ላይ እንድናይለት ያደረገ ማፈርያ ነው።

ተፈራ ማለት ወደ ውጭ አገር ለመሸሽ እግሩ ሳይታመም ታመምኩኝ ብሎ የሚወሰልት ሲጨንቀው ወደ ፋኖ የተቀላቀለ፤“ሚስቱን መቆጣጠር የማይችል” “አፍቃሬ ሻቢያነቱ/አፈቃሬ  ኢሳያስነቱን” ለመግለጽ አምሐራ ሕልውናውን ለመጠበቅ ከሻቢያ ጋር ማበር እንዳለበት በተመስገን ደሳለኝ “ፈትሕ” መጽሔት ላይ ሳይደብቅ የነገረን ሰው ነው።

የጎጃምና የጎንደር ምሁራን “አይካን መሪያችን” የሚሉት “የሻቢያው ግርፍ” ዘመነ ካሴ ብቻ አይደለም፤ ተፈራ ማሞ የተባለ ማፈርያም ነው። ተፈራ ማሞን ስታነሱ “ሥርዓቱ የትም እንደማያደርስ ተሎ የነቃው ጀግናው አሳምነውን አስታውሱ።

አብይ አሕመድ የሚያስተላልፋቸውን ጸረ አምሐራ ክንዋኔዎችን ለማስፈጸም አስር ጊዜ  ስብሰባ ሲጠሩትና ሲወተውቱት የነበሩት ከኦሮሙማ ፋሺስቶች ጋር ጠጅ ለማንቃረር ያደሩ ቅጥረኛ ባንዳዊያን ብአዲኖችን ያጋደመ “የወንዶች ልክ” “በአሳምነው ጽ ገናናነትና ምጥቀትነት የሚቀና” ቀናተኛና ሐሜተኛ ሰው ተፈራ ማሞን ለማንገስ እያነፈነፉ ዘመቻ ማቀንቀን የሚገርም መስተንክር ነው።

የጎጃምና የጎንደር መሁራን ለምን እንደዘቀጡ አልገባኝም። አቻምየለህ ታመሩ “አቃጣሪው የወያኔ ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞን እንዲሀ ሲል ያሞካሸዋል፤

«አማራ በዚህ ወቅት የሚያስፈልገው መሪ እንደ ተፈራ ማሞ አይነት በአማራ ላይ የተጋረጠውን የኅልውና አደጋ እንደ እጁ መዳፍ አብጠርጥሮ  የሚያውቅ አራት ዐይና ብቻ ነው።”

በማለት በሚያስቅና በሚያስደነግጥ አባባል አፍቃኴ “ሐምተኛና ስም አጥፊው” ተፈራ ማሞን “የአመሐራ መሪ” አድርጎ “ይምራን” ብሎ “መሪ አድርጎ” ሹሞታል። “ዝገርም እዩ!!” አለ ትግሬ።

ከማንም በፊት አሰቀድሞ በየፋ “አምሐራ ላይ የተጋረጠውን የኅልውና አደጋ እንደ እጁ መዳፍ አብጠርጥሮ ያወቀውን ብ/ጀ አሳምነው ጽጌን “ሲዘልፍ የነበረ “ሐምየተኛና አድር ባይ ፈሪ” ዛሬ ተፈራ ማሞን አቻምየለህ ታመሩ በሚያስቀን አገላለጽና ሹመት “ በአማራ ላይ የተጋረጠውን የኅልውና አደጋ እንደ እጁ መዳፍ አብጠርጥሮ  የሚያውቅ አራት ዐይና” ሲል አሞካሽቶታል።

እነዚህ ምሁራን ምን አዚም ነው የዞረባው ይህንን ሐሜተኛ ሰው እንዲህ  ሊያሞካሹትና መሪያችን ነህ ብለው ሰማየ ሰማያት የሰቀሉት? አልገባ አለኝ።

ጎጃም የበቀለው የዘመነ መንደርተኛ የፋኖ ፋሺስታዊ ቡድን መረን ልቅቆ በጫካ ሕግ በሕገ አራዊት በደመነብስ እየተመራ ንግሥና እና ሥልጣን ስንወለድ “ከ ዲ ኤን ኤ” የተቸረነ ልዩ ፍጡራን ነንበሚል ናዚያዊ ፈለግ እየተከተለ የዘመነ ካሴ ታጣቂ ቡድን በንጹሃን ተማሪዎች ፤መምህራንና በፋኖ ታጋዮች ላይ የግድያና የሽብር ድርጊት ሲፈጽም የጎጃምና የጎንደር ምሁራን በድጋፍ ሰጪነት የቆሙት ሁሉ በታሪክ ተጠያቂዎች ናቸው።

ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay


Monday, April 7, 2025

ትግራይ አምና እና ዘንድሮ (ሀ) የማይረሳው የከሳቴ ብርሃን ት/ቤት ትዝታ --121 ከጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 4/7/25

 

ትግራይ አምና እና ዘንድሮ

() የማይረሳው የከሳቴ ብርሃን /ቤት ትዝታ --121

ከጌታቸው ረዳ  Ethiopian Semay

4/7/25

ክደራሲው ለዛሬ ወልድ ወጣት አንባቢዎች የተሰጠ ምክር!

ዛሬ ሃገራችን የምትለዋት ኢትዮጰያ ከሰማይ ተጋግራ የተሰጠቻችሁ ሃገር ሳትሆን ብዙ ለፍተን ፤ከጠላት ጋር ተታኩሰን፤ ሞተን፤ ተሰድበን፤ ብዙ ድካምና ደም የፈሰሰባት ምድር ያስረከብናችሁ መሆንዋን ዘንግታችሁ በምድሪቱ ሕልውና ላይ ስታላግጡ በማየቴ የተስማኝን ውስጣዊ ሐዘንና ቅሬታየን እየገለጽኩ ታሪክ ወደ ኋላ ላስቃኛችሁና ሐዘን ተሰምቷችሁ ምናልባት ልብ ብትገዙ ስለ ኢትዮጵያ የተከፈለው መስዋዕት እነሆ ከምጽሐፍይ ላስቃኛችሁ።

ቁስለኛና በሽተኛ የሚቀበለው ብቸኛው የከተማዋ ሆስፒታል ከየቀጠናው የመጡ የቆሰሉ ብዙ ሠራዊቶች በብዛት ስለተቀበለ ከአቅሙ በላይ ሆኖበት፤ በሆስፒታሉ የመተላለፊያ በረንዳዎች ላይ ሳይቀር እንዲተኙ በመደረጉ፤ ብቸኛው ሆስፒታል በቁስለኛ ስለተጨናነቀ፤ አማራጭ ሆኖ የተገኘው ከተማዎቹ ወደ እሚገኙ ትምሕርት ቤቶችና ህንጻዎች እንደመታከሚያና ማረፊያ ሆነው እንዲያገለግሉ ቅጽበታዊ ውሳኔ ተደረገ።ከነዚህ ውስጥክሳቴ ብርሃን/ቤት ነበር።፡ ህንጻው ብዙ ክፍሎች ስለነበሩት የቆሰለው ሠራዊት በብዛት በማስገባት በጊዜአዊ አልጋዮች እና ወለል ላይ እንዲተኛ ተደረገ።ከላይ እንደገለጽኩት ወቅቱ ክረምት በመኖሩ፤ የቆሰሉ ሠራዊቶች ወታደራዊ ቦቴ ጫማቸውና ልብሳቸው በጭቃ እና በደም የተለወሰ ሆኖ ለማየት እጅግ የሚያበሳጭ እና የሚያሳዝን ፈታኝ ወቅት ነበር። ሠራዊቶቹ አልጋ ላይም ሆኑ ወለል ላይ የተኙት አጣዳፊ የማጓጓዝ ስራ ሲሰራ በዛው ላይ ብዛት ስለነበራቸው-ጫማቸው፤ የቦምብ ትጥቃቸውና የጠበቀው ቀበቶአቸው ከነትጥቃቸው ተኝተው ይታያሉ።ይህ አሳዛኝ የሆነ የእርስበርስ ጦርነት ላየ ሰው እውነት ከባዕድ ጋር እንጂ  በአንድ አገር ዜጋ ልጆች የተደረገ ጦርነት አይመስልም።እጅግ የሚያሳዝነው ግን ያኔም ሆነ ዛሬ እስካሁና ደቂቃ ድረስ ወያኔዎች በሚያሰራጩዋቸው የፕሮፓጋንዳ መገናኛዎችውጊያው በጣሊያን እና በኢትዮጵያ ዜጎች መካካል እንደተደረገ  አድርገው በማየትወራሪየሚል ቃል በመጠቀም፤ የጦርነቱ ተከታታይነት  ቀዳማይ ወራር፤ ካልኣይ ወራር ሳልሳይ ወራር..” (1 ወረራ፤ 2 ወረራ፤ 3 ወረራ…) በማለት ኤርትራኖች የሚጠቀሙበትንመሬት ለመንጠቅ የመጣ፤ ኮሎኒያሊስት/ ባዕድለማለት የሚጠቀሙበት አገላለጽ ነው የትግሬ ወያኔዎች ሲጠቀሙበት የነበረው። ደርግተገንጣይ ቡድኖችብሎ ሲገልጻቸው፤ ወያኔዎች ደግሞ በሚገርም አሳፋሪ አገላለጽወራሪ ሃይልበማለት ኢትዮጵያዊነታቸው በግልጽ የጣሉበት አጋላለጽ 

ነበር።በወራሪና በባዕድ የተደረገ ጦርነት ብለው ስለሚያምኑም፤ የዓረቦች አሽከርነት ለማሳየትይመስላልከዓረቦች (ባሕሬን) እና ከሰሜን አፍሪካ (ሞሮኮ) አደባባዮች ዛሬም በሕዝብ መሰብሰቢያ አደባባይ ተተክለው የሚታዩት ከነዚህ ዓረብ አገሮች የተቀዳ ዓረባዊየሐውልትቅርጽ ቀድተውመቀሌ ከተማ ውስጥ ለተሰውት ተዋጊ ሃይላቸውሃውልትአቁመዋል።

ወደ ክሳቴ ብርሃን /ቤት ቁስለኛ ማቆያ ህንጻ ልውሰዳችሁ። ከሳቴ ብርሃን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ/ክርስትያን ትምህርት የሚሰጥበት መንፈሳዊ /ቤት ነው። በሰራዊቱ ብዛት እና ድሕረ ውግያ መደረግ የነበረባቸው ጥናት ባለመደረጉ ቁስለኛ የሚመዘግብ፤ የሚያስተናግድ የሰው ሃይል ስላልነበረ አስቀድሜ እንደገለጽኩት ከነ-ቦምባቸው እና የታጠቁት ሽጉጥ ተጋድመው ያቃስታሉ።  በዛው ብርዳማ ወለል ላይ ያለ ብርድ-ልብስ፤ በትራሳቸው ላይ ጉዝጓዝ በሌለው ወለል ላይ በጀርባቸው ተንጋልለው፤ በጥይት እና በቦምብ የተመታው የቆሰለው ገላቸው፤ ስቃዩ አላስችል ብሎአቸው ፊታቸው በላብ ተጠምቆ፤ ገላቸው በትኩሳት ነድዶ፤ የስቃይ ድምፅ በማሰማት ለተጨማሪ ስቃይ ተጋለጡ።

የሰው ልጅ አንጀት ሰርስሮ በሚገባ ሲቃ እያቃሰቱት የነበረው የስቃይ ጽምፅ እንኳን ለሰው ልጅ አንጀት የአራዊት ጀሮ የሚያሰቆም፤ የሚያባባ ፤የሚያስለቅስ ድምጽ ስለነበር፤ በጆሮው የሰማ የመቀሌ ኗሪ ሕዝብ እንዲህ ያለ ስቃይ ለምን እና እንዴት ተከሰተ ለሚለው ምርምር ለምሁራን ትቶ፤ ባደመጠው የስቃይ ድምፅ  ስለባባ የማልረሳው በዓይነቱ ልዩ የሆነ ተስምቶና ታይቶ የማይታወቅ ኢትዮጵያዊ ሰብአዊነት የተመረኮዘ ያየሁትን የማስታውሰውን ለታሪክ ላስመዝግብ። እንደገለጽኩት የሚያርፍበት መጠለያ ስላልተዘጋጀለት ከሠራዊቱ ብዛት አኳያ ለተቀናጀ እንክብካቤ ስላላመቸና በሃላፊነት የወሰደ የሰራዊት አዛዦችም ከነበሩ እየተካሄደ ወደነበረው የውጊያ ቀጠናዎች ቀልባቸው ስለተጠመደ የተመደበው የሰው ሃይልም በቂ ስላልነበረ፡ የአካባቢው ባለሥልጣኖች፤ አጣዳፊ ዝግጅቶች  ካልወሰዱ እርምጃ (ሞት) ለመውሰድ የሚሽቀዳደም እንጂ በጥናት የታቀደ ሃላፊነቱን የማይሸከም ሥርዐትስለነበረ፤ ከሚመጣባቸውዱብ ዕዳ  እርምጃ ለመሸሽ ሲሉ፤ የከተማው የመንግሥት ተጠሪ ቅርንጫፍ መስርያቤት ሃላፊዎች በመሰብሰብ፤ በየሰዓቱ በሄልኮፕተር  ከጦር ሜዳ የሚመጣው ቁስለኛ የት እና እንዴት ያለ እንክብካቤ መደረግ እንዳለበት፤ እንደየ ጉዳቱ አይነት እየለዩ በየክፈሉ ላመስተኛት ተወያይተው የተቻላቸውን ማድረግ ጀመሩ።

በሰራዊቱ ብዛት እና በመንግሥት ጥናት ባለመደረጉ፤

 እየፈሰሰ ያለው የቁስለኞችን ደም ለማስቆም ለመሸፈን የቁስልሻሽ/ጐዝ መድሃኒት መውጊያም፤ የመርፌ መቀቀያዳርፉር ብረት ድሰት የሕክምና ፕላስተር፤ የመሳሰሉ ጥቃቅን ነገሮች ሕዝቡ ከየቤቱ ካለው እንዲለግስ በተጠየቀበት መሰረት ያለውን ቁሳቁስ ሁሉ ከየቀበሌው እያሰባሰበ ወደ መጠለያ አመጣ። የሰራዊቱ ቁስለኛ ብዛት ስለነበረው፤ በዛው መጠን የሕክምና ባለሞያ ያንን የቁስለኛ ብዛት የሚሸፍን የሰው ሃይል ስለታጣ፤ በዚህ የተነሳ ቁስለኛውን የሚያክም ስላልነበረ፤ እንደየ ቁስሉ ስፋት ጥልቀትና ክብደት ጠረኑ እየለወጠ በመምጣቱ፤ ቁስለኛው ለቀናት አንዳንዱም ለሳምንት ሳይታከሙ በመቆየታቸው፤ ቁስሉቂም’ (ኢንፌክሽን) በመያዙ ምክንያት  በትኩሳትነድሮ በደምና በመግል የተጣበቀው ቁስል በማከም ሂደት ውስጥ ወጣቱና ሕዝቡ፤ ጠረኑ አላስጠጋ ያለውን በደምና መግል የተጣበቀው ቁስል፤ በእጁ እያፈረጠ፤ በጨርቅና በጥጥ ውሃ እየነከረ ጠረኑ የለወጠ ቁስል እየሸተተውም ቢሆን በማጽዳት የማይረሳ ኢትዮጵያዊነቱን ያስመሰከረበት ወቅት ነበር።

እዚህ ላይ ልጠቅሰው የምፈልገው፤ የሕክምና ጥጥ እና ጎዝ/ሻሽ እጥረት ስለነበረ፤ የቁስለኛው ቁስል ስያክም ከየ ያመጣው አንሶላም ሆነ ንጹህ ስስ ጨርቅ በቀጭኑ እየቀደደ ነበር ቁስሉን እያጠበ ለቁስል መሸፈኛ የተጠቀመው እንደዚያ ያለው ትውልድ/ ሕዝብ ዛሬ በክረስቶስ ስም ለምነህ ለማስረጃ እንኳን ለሽታ የሚገኝ አይመስለኝም። ባጭሩድንግል ኢትዮጵያዊነበር! ለቁስለኞቹ የተዘጋጀ የሌሊት (ፕሮን) ልብስ/ ፒጃማ/ የመሳሰሉ ስላልነበሩት፤ ቁስለኛው ሰራዊት፤ በውግያው ወቅት በደምና በጭቃ ተለውሶ፤ ወደ ደረቅ አጐዛነት የተለወጠው ወለል ጋር ተጣብቆ ለብሶት የነበረው ወታደራዊ ደምብ ልብስ ሕዝቡ ከየቤቱ የመጣለትን አንሶላና ነጠላ በማልበስ የቆሸሸው ልብስ በየወንዙና እቤቱ ድረስ ወሰዶ በማጠብ፤ በጭቃ፤ በላብና በደም የደረቀ የወታደሩ ልብስ አጥቦ አልብሶአቸዋል።ለቀናት፤ ለሳምንታት መጀመሪያ ሲመጣ ተንጋሎ በተኛበት ሳይላወስ የቆየውን ቁስለኛ ደግፎ በመስነሳት አከላዊ እንቅስቃሴ እንዲያደረግ፤ ወለል ላይ እና አልጋ ላይ በመተኛት የደነዘዘው አካላቱ እንዲፍታታ አድርጎ ትንፋሽ እንዲያገኝ ረድተዋል።

ከጦር ሜዳ ቆስሎ ሲመጣ በጥብቅ ከርሮ ታስሮ የነበረው ወታደራዊ ጫማቸው ለብዙ ቀናት ከእግራቸው ስላልወለቀ አግራቸው በማበጡ፤ ጫማቸውን አውልቀው የረጋወንና ደማቸውና ያበጠው እግራቸው በዘይትና በደረቁ በማሸት አንገቱን ቀና እንዲል ደግፈው፤ ከየቤታቸው ያመጡት ወተትና ምግብ አልከፈት ያለውን የቆሰለው ጉሮራቸው አለሳልሰው በማጉረስ ያደረጉት ሰብአዊ ርሕራሄ እና ዛሬ ያለው የትግራይ ሁኔታ ሳነጻጽር ሁኔታው እንቆቁልሽ ይሆንብኛል እንዲህ ያለ ጥንታዊ ርሕራሔና ሞራላዊ፤ ዜግነታዊ ግዴታወድዶ ያለ ግዴታበመፈጸም፤ መብራት ባልነበረበትና መብራት በሚቋረጥበት ክፍል ውስጥ ተኝቶ የነበረውን ቁስለኛ ሰራዊት፤ ከቤቱ ያመጣውን ሻማ አብርቶ፤ ቁስለኞቹ ከተኙበት አልጋ እና ወለል ደግፈው አንገታቸውን በማቅናት በስቃይ እና በኡኡታ የደረቀ ጉሮራቸውውሃበማጠጣት፤ የደረቀው ከንፈራቸው፤ በጨርቅና በጥጥ እያራሱ፤ በትኩሳትና በጩኸት የተሰነጣጠቀው የደረቀ ከንፈራቸው እንዲርስ  አድርገዋል።

የመቀሌ ሕዝብ እንደዛሬ ሳይሆን፤ ውርቃማ ከሚባሉ የመጽሐፍ ቅዱስና ቁርአን ሕግጋቶች ከሚጠቀሱ ሰብአዊ "ላንተ እንዲደረግልህ የምትፈልገውን ነገር ለሌላው አድርግ" የሚለውን መርሆ ተነስቶየተደናገጠውን ልብ ያረጋጋሕዝብ ነበር። "ነበር" ብየ የምገልጸው በዛሬው ጊዜ እማሃሉ ውስጥ ከሸገር አውራጃ እና ከወስጡ የበቀሉ አክራሪ ፋሺስታዊ ጎሰኛነት የሚያስተምሩ የተለከፉ ግለሰቦች እማሃሉ ውስጥ በካድሬነትና በከፍተኛ የመንግሥት መዋቅርና በየትምህርት ተቋማቱ እና በኪነት ባለሞያዎችና በየቤተጸሎቶች ተሰማርተው የሕዝቡን ስነ ልቦና በጎሰኛነት ስለበከሉት፤ነውከሚለው ቃል ይልቅነበርየሚለው አማራጭ አድርጌ የገለጽኩት።

ይህ በዚህ እንዳለ፤ ሠራዊቱ የከተማው ኗሪ  ሕዝብ ዜጋዊ

እንክብካቤ ካገኘ በኋላ፤ ትንሽ ሕይወት የዘሩ ሰራዊቶች ከየአልጋቸውም ሆነ ከተኙበት ወለል እየተነሱ፤በምርኩዝም ሆነ በጓዶቻቸው ተደግፈው እያነከሱ በየክፍሉ እየዞሩ፤ የሰርዓቱን መሪዎች በማውገዝ፤ ሠራዊቱን በመቀስቀስ የጦር አለቆች እና ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣኖች ከያሉበት ቦታ እንዲጎበኝዋቸው አስቸኳይ የአድማ ጥሪ ቴሌግራም ይደረግ ብለው ስለተስማሙ፤ በጠየቁት መሠረት፤ ከጥቂት ቀናት ቆይታ፤ እንዲመጡላቸው የጠየቁዋቸው የጦር አለቆች ወደ መቀሌ መምጣት ጀመሩ። አለቆችም፤ በእያንዳንዱ ክፍል በመግባትእንደምን አላችሁ?” እያሉ በመጠየቅ ቁስለኞችን መጎብኘት ጀመሩ።  አለቆቹ ወደ ክፍል ሲገቡ፤ ከአልጋቸው መነሳት ያልቻሉ ኩፉኛ የተጎዱ በተለይ እጆቻቸው ወይንም እግሮቻቸው ያጡ ቁስለኞች፤በእጆቻቸው እያወዛወዙ ወደ አልጋቸው ተጠግተው እንዲያነጋግሯቸው ሲጠሩዋቸው፤ የሠራዊቱ አለቆችም ወደ አልጋው ተጠግተውደህና ናችሁ ጓዶች?” ብለው ሲጠጉ፤ ምራቃቸውን ወደ አለቆቻቸው ሲተፉባቸው፤ አለቆቹም ተደናግጠው ከክፍሉ ሲወጡ፤ በምርኩዝ የሚሄዱ እንዳንዶቹ ቁስለኞችም ኋላ ኋላቸው እየተከተሉ ሲሰድቧቸው ሌሎችም ጥግ ጥግ በረንዳው ላይ የቆሙ እና የተኙ ቁስለኞችበፉጨትእያፏጩ ይቀልዱባቸውና ቁጣቸውን ይገልጹ ነበር።

ልዩ ትዕይንት የነበረው ደግሞ፤ ችግራቸው የአገሪቱ የመገናኛ ማዕከሎች/ ራዲዮ/ ጋዜጣ         እንደማይዘግቡላቸው ስለሚያውቁና በቦታውም የተገኙ ጋዜጠኞች ስላልነበሩ፤ በጣም ቀልጣፋ ተነጋሪዎችና በየክፍሉ በተፈጥሮ ስጦታቸው ቀልድ ነጋሪዎች (ኮመዲያን) የነበሩቀልደኞችበስቃይ የሚያቃስቱትን ጓዶቻቸውን ሲያዝናኑ የነበሩ ከየክፍሉ  የተመዘዙ አባሎች፤ በየክፍሉ በመሄድ፤ አንዱ የመድረክ አስተዋዋቂ ዜና ሰብሳቢ፤ አንዱ ዜና አንባቢ፤ ሆነው በመመደብ፤ የጦር አለቆቹ ሲጎበኙዋቸው በዕለቱ የታየው የጉብኝት ትዕይንት  በዜና መልክ እና በቀልድ አጠናቅረውበሚያስደንቅ አነጋገርና አማርኛ፤ ፖለቲካዊ ቅመም ጨምረውበት፤ ስለ ታየው ሩጫ እና አድማ  ያቀረቡት አቀራረብ እጅግ የማልረሳው ታሪክ ነበር። ከተማ ያደጉ ወጣት ወታደሮች ስለነበሩ አማርኛቸው ሲያንበለብሉት፤ አንዳንዱ ባዲስ አበባዎቹ (አራዳ የምትልዋቸው ይመስለኛል) ልሳን  እየተጠቀሙ ዜናውንና ቀልዱንያለምንም ጽሑፍበቃላቸው ሲያንበለብሉት የሰማ ጀሮ መደነቁን ለመግለጽ ቃላት ፈልጎ የሚያገኝ አይመስለኝም። ዜና አንባቢዎቹ እና ቀልድ ነጋሪዎቹ ባሯርዋጧቸው አለቆቻቸው ላይ ያጠናከሩት በያይነቱ ቀልድና ዜና ሲተነትኑት የሰሙ በከባድ ቁስልና ትኩሳት ተይዘው በሲቃ ሲጮኹ የነበሩ፤ ከተራ ወታደር እስከ መስመራዊ መኮንኖች የነበሩበት የቁስለኞች ክፍል ሳያስቡትፈገግእያሉ ጥርሳቸው ብልጭ እያደረጉ የጭንቀት ፈገግታ ሲያሳዩ ማየት በትዝታ ፈለግ አሁን ሲታየኝ ልቤ ኩፉኛ ይሰበራል።

ሠራዊቱን ለማጽናናት ለመደገፍ በፈቃደኝነት ከተገኙ ኗሪዎች አንዱ እኔ ስለነበርኩ፤ ለእናት አገሩ ለኢትዮጵያ ሲል ሠራዊቱ በሲቃ ተይዞ፤ እንደ ጋለ ብረት የሚያቃጥል ገላው እየተለበለበ፤ ትንፋሽ አጥሮት ሲታገል ባስጨናቂ ትኩሳት እና ላብ ተነክሮ የደረቀው ከንፈሩና ጉሮሮው ደርቆ የትንፋሹ ጠረን ቀይሮ፤የውሃ ያለህእማየ ድረሺሲል ገላውና  ከንፈሩ በቀዝቃዛ ውሃ እያራስኩ ሳጽናናው፤ በዛው ስቃይና የሞራል ጥንካሬና መስዋዕት የከፈለው የመሰለ ሠራዊት ተመን የማይገኝለት መስዋዕት መክፈሉን በዓይኔ ስላየሁት፤ ወያኔ ሥልጣን ከያዘ በኋላ እነዚህን የዋሆች ወደ ለማኝነት ህይወት ወደ በረንዳ ሲጥላቸው፤ ከወያኔ ጋር የማይታረቅ ጸብ የፈጠረብኝ፤ አንዱ ምክንያቴ ይኸኛው ነው። አሁንም ሳስታውሰው እንጀቴ ይረበሻል! ወደ ታሪኩ ልመልሳችሁ። በእንደዛው የመሰለ አስጨናቂ  ክስተት እና ከባድ ቁስል እየተሰቃዩ፤ እርስ በርሳቸው በጠንካራ ሞራል ተደጋግፈው ያየ ሰው፤ የኋላ ኋላ የትም ቀርተው፤ በየበረንዳው እና በስደት ዓለም ተበትነው ማየት፤ እውነትም ኢትዮጵያየሞተልሽ ቀርቶ፤ ያልሞተልሽ በላየሚባለው እውነት ነው።  ይህንን ሳስበው አንድ ግጥም ትዝ አለኝ።

የዘመናችንየኪነት ፈላስፋና የድምጸ መረዋው የቅዱስ ያሬድ ፍሬየሆነው አገር ወዳዱ ዝነኛው ሙዚቀኛው ቴዲ አፍሮሊስትሮበሚል ግጥሙ ውስጥ ያለውን ልጥቀስ።  ጫማ በመጥረግ ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደገ አንድ ሊስትሮ፤ ከዚያ ከድህንት ዓለም ወጥቶ አንድ ቀን ጫማ ለማስጠረግ ሊሰትሮ ጋር ሄዶ ከሊሰትሮዋ/ ከሳጥንዋ /ላይ ቆሞ ጫማውን  እያስጠረገ እንዳለ ውለታ ለዋለችለት የሊስትሮ ዕቃው የገጠመላትን ‘’ቴዲ አፍሮበእንዲህ ይገልጸዋል፦

 

በጣሙን አዝናለሁ ውዷ የሊስትሮ ዕቃዬ፤

ምንም እንኳ ብትሆኚ ባለውለታዬ፤

በጫማ ብረግጥሽ አይክፋሽ ግድየለም፤

 ባታውቂው ነው እንጂ ለዋለላት ሁሉ እንዳዛው ነው ዓለም። 

 ከስሜቴ ልውጣ እና እንቀጥል ወደ ታሪኩ ልውሰዳችሁ። ሁኔታው በሰራዊቱ እና በከፍተኛ አዛዦች እንዲሁም አዛዥ አና አዛዥ መካካል በሁኔታው የተነሳ ያለመጣጣም ስለተነሳ፤ ቁስለኛው ኮለኔል ታሪኩ ላይኔ የተባሉ ከፍተኛ የጦር አዛዥ እንጂ ሌላ እንዳይላክላቸው ስለጠየቁ፤ በጠየቁት መሰረት ኮለኔሉ ወደ መቀሌ መጥተው፤ ቁስለኞች ወደ ተኙበት ክሰቴ ብርሃን /ቤት መጡ። ቁስለኛው የቻለና ያልቻለ በምርኩዝ እና በሰው እየተደገፈ በየበረንዳው እና እመሃል መሰብሰብያው ላይ ተጠራርቶ በመሰብሰብ፤ ለኮለኔሉ ጥያቄ አቀረቡ። ተናጋሪዎቹ አስቀድሜ እንደገለጽኩት እሳት የበሉ ተናጋሪዎች ስለነበርዋቸው፤ ቅሬታቸውን አንበለበሉት። ቆም እያሉ ተናጋሪዎቹ  እምባ ሲተናነቃቸውያዩ አዛዡ በትዝታ ተጭነው በሐዘን ተውጠው ያደምጣሉ። አንዳንዶቹ ቁስለኛ ወታደሮች በዛው ጸጥታ በሰፈነበት አየር ንግግር ሲደረግ፤ ከበረንዳው ላይ ተንጋልለውበሰለለ/ የደከመ/ ድምጽ የታጀበ፤ አንጀት የሚፈታተን የስቃይ ድምጽየሰሙ በረንዳው ጥግ ላይ ካጠገቤ ጎን ቆመው የነበሩ ለእርዳታ የመጡ የከተማው ወጣት ሴቶች፤ ዓይናቸው ውሃ ቋጥሮ  በድንገት ሊፈነዳ የተቃረበዕምባይተናነቃቸዋል።

በኮለኔሉ እና በቁስለኛው ሠራዊት መካከል የመደማመጥ መንፈስ ስለነበር፤ አንዱ የሁኔታቸው ነገር አጠቃላይ ንግግር ካስረዳ በኋላ፤ ሌላ ተናጋሪ፤ በመቀጠል፤ ሲጋራ፤ ወርሃዊ ደሞዝ ልብስ….. ወዘተ.. ወዘተ.. የመሳሰሉ ነገሮች ያስፈልጉናል ብለው ብዙ ዝርዝሮች ካቀረበ በኋላአባታችንይህንን እንደምታደርግልን ባለ ሙሉ ተስፋ አለን፡ እናከብርሃለን! ኑርልን! ብሎ ሲጨርስ፡ ኮለኔሉ በሰሜትና በሃዘን ተውጠው ከውስጥ የያዙት ንዴት እንዳለ መገመት በሚያስችል ንግግር ተናግረውየጠየቃችሁትን በሙሉ ባጭር ጊዜ ይመጣል። ካልመጣ ወዲያውኑ መልእክት ላኩልኝ፤ካሉዋቸው በኋላ የጠየቃችኋቸው ወደ ከፍተኛ ሕክምና የመዛወር ጥያቄም አስቸኳይ ጉዳይ በመሆኑ የምችለውን አደርጋለሁ፤ ጥያቄአችሁ ወደ እሚመለከታቸው ክፍሎች ባስቸኳይ አቀርብላችኋለሁ። ተስፋ አትቁረጡ! እናሸንፋለን! ኢትዮጵያ ወይም ሞት! ብለው ተሰናብተዋቸው ሔዱ። ከሰንት ጊዜ ቆይታ አንደሆነ ባለስታውሰውም ከባድ ቁስለኞች ወደ አዲስ አበባ እና የመሳሰሉ የሕክምና ተቋማትበአይሮፕላን እየተጫኑ ለሕክምና ይወሰዱ እንደነበር አስታውሳለሁ። ሆኖም አገሪቱ የነበርዋት የሕክምና ተቋሞች ከየቦታው በመጡ ቁስለኞች ስለተሞሉ፤ ብዙዎቹ እዛው ክሳቴ ብርሃን እና ሌሎች /ቤት ህንጻዎች ውሰጥ ተጠልለው፤ በቂ የሕክምና እና መድሃኒት ባለመኖሩ፤ድሬሰር/አድቫንስ ድሬሰሮችተብለው በሚጠሩ ዝቅተኛ የሕክምና ባለሞያዎች እየታገዙ ከፍተኛ ስቃይ ለነበራቸው፤ ጦር ሜዳ ላይ ያሉ እየመሰላቸው ትኩሳቱ ሲበረታቸው በቅዠትፉከራ እና ኡኡታ ጩኸትየሚያቀልጡ ቁስለኞች ስለነበሩ፤ ከስቃያቸው እና ከቅዠታቸው ለማስታገስ ተብሎ በድሬሰሮች አማካይነት ያለ ምንም የመድሃኒት መጠን አሰጣጥ ቁጥጥርናርኮቲክ” (አስካሪ አደንዛዥ የስቃይ አስታጋሽ መድሃኒቶች) ‘ቡታዘሊዶን፤ ፌኖባርቢቶል፤ ሞርፊን…..እና የመሳሰሉ እንቅልፍ  የሚያስተኙ፤ የሚያሰክሩ፤ መርፌዎች፤ ማታ፤ ማታ እንዲተኙ በሚል በብዛት እየተወጉ፤ ሱስ ውስጥ የገቡ ብዙ ነበሩ።አሳዛኙ ሁኔታ እዛው ላይ አላቆመም። የሕክምና ባለሞያ እና የሚንከባከባቸው ቋሚ ሠራተኛ እጥረት ስለነበረ፤ ቁስለኞቹ ከተኙበት አልጋ ወይንም ወለል የሚያገላብጣቸው የተመደበ ቋሚ ስላልነበረ፤ኒሞኒያእናቤድ ሶር” (ሳይገለበጡ ባንድ ጎን ለብዙ ወር/ሳምንታት በመተኛት የሚፈጠር ጥልቀት ያለው ጎድጓዳ ቁስል) እየተሰቃዩ ብዙ ጊዜ ቆይተዋል። ጦርነቱ ቀጣይ ስለነበረ፤ ተመሳሳይ ውግያ ሲደረግ፤ የዛሬው ትግራይ ሕዝብና ወጣት በወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ከመበከሉ በፊት (እንደዛሬ አያድርገውና) የያኔው የትግራይ ሕዝብ ሠራዊቱ በያለፈበት ገጠርም ሆነ ከተማ ተጎድቶ ሲያልፍ  የማይረሳ ዜጋዊ እንክብካቤ አድርጎለታል።  ይህ ዜጋዊ እና ርህራሄ የተሞላበት እንክንካቤ ወያነ ትግራይ ብዙም ሳይቆይ በሕዝብ ደም ስር ገብቶ ሕሊናው ሳያበላሸውየኢትዮጵያ ሰንደቃለማ እንጂ እንደ ዛሬ ቄሱም መነኩሴውም ሴቱም ፤ ልጁም፤ ምሀሩም ፤ቤተክረሰትያኒቱምየወያኔባለ ኮከቡ የቻይና ኮሚነሰት ባንዴራ ሳያውለበልብ በነበረበት እንዲህ ያለ የዜግነት ሥራ መስራቱን ለመጀመርያ ጊዜ ለታሪክ ተመራማሪዎች የመዘገበ የመጀመሪያ የትግራይ ሰው መሆኔ ኩራትና ደስታ ይሰማኛል

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ (ከየትግራይ ብሔረተኞች በአማራ ላይ ያላቸው ጥላቻ ከምን የመነጨ ነው?) ከሚል ከታተ 2010 . ከገጽ 121 መጽሐፌ የተቀነጨበ) Ethiopian Semay