Sunday, May 26, 2019

ነጭ ባንዲራ አውለብላቢዎች ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ)


ነጭ ባንዲራ አውለብላቢዎች

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ)
ራሱን በማቃጠል መስዋዕት በመሆን የቱኒዚያን አብዮት ያቀጣጠለው ቦአዚዝ
የኔ ሰው ገብሬ ራሱን በማቃጠል መስዋዕት በመሆን የኢትዮጵያን አብዮት ለማቀጣጠል መስዋዕት ቢሆንም ተቃወሚዎች የከዱት መስዋዕት ሆኖ ቀርቷል። ዛሬ የሚዘክረውም የለም።
የጣሊያኖችን ዘመን ትተን እኛ በነበርንበት ዘመን በእኛ አቆጣጠር በ60ዎቹ ከተማሪዎች አብዮት ዘመን ጀምሮ ኢትዮጵያችን በሶቭየት ሕብረት ኮሚኒስት፤በምዕራባውያን እና በዓረቦች ዓይን ውስጥ ከገባችበት ወቅት ጀምሮ እስካሁን ድረስ እየታየ ያለ ጥቃት የነዚህ አገሮች ምስጢራዊ እና የግሃድ የጥቃት ዘመቻ ዛሬም አላባራም

 ጃስሚን አብዮት Jasmine Revolution (የኑሮ ምስቅልቅል ያስከተለ ተከታታይ ሕዝባዊ አመጽ) ተብሎ የሚታወቀው “አገልግሎቱ የጨረሰ” ተብሎ በአሜሪካኖቹ የተወገደው አገልጋያቸው የነበረው የቱኒዚያ መሪው ቤን አሊን ያስወገደው አብዮትም ሆነ ብዙዎቹ ታዋቂ ዓረብ አገሮችን ፈራረሱ አገሮች” ያደረገው “አረብ ስፕሪንግ” በመባል የሚታወቀው ሱናሚው አብዮት የተቀነባበረው በአሜሪካውያኖች መሆኑን ታስታውሳላችሁ። ይህ ዘመቻ ግምባር ቀደም የተጫወተው ልክ እንደ አብይ አሕመድ ስልጣን በያዘ በጥቂት ወራት “የኖቬል የሰላም ሽላማት ተሸላሚ” ሆኖ የሰላም ሰው ለማስመሰል በሴራ እንዲሸለም የተደረገው  ወያኔዎችን “በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት” በማለት ሲያሞካሻቸው የነበረው በዓለም ውስጥ ሥርዓተ አልበኛነትና ስደተኛን በዕቅድ እንደ 'ሰደድ-እሳት' ያስፋፋ አደገኛው የዓለማችን ሰው “ባራክ ኦባማ” ነው።

በራሱ የአስተዳዳር መሪነት የተመሰረተው PSD-11 የተባለው የምስጢር ዘመቻ በተጠቀሱት አረባዊ እና እስላመዊ/አፍሪካዊ አገሮች ላይ ያጠነጠነ አገርን የማፍረስና መሪዎችን የመተካት ምስጢራዊ ዘመቻ መከናወኑ በተመራማሪዎች የተገኘ ሰነድ MANIFEST DESTINY - DEMOCRACY AS COGNITIVE DISSONANCE(F. WILLIAM ENGDAHL) ወዳጄ ዶ/ር አሰፋ ነጋሽ እንዳነብበው ከሰጠኝ መጽሐፍ ውስጥ ለማየት ችያለሁ 

ዘራፊዎቹ እና አገር አጥፊ ኮሎኒያሊስቶቹ የወያኔ መሪዎች ያገራችንን ነባራዊ እሴት ባሕል “ፍርስርሷን አውጥተው” ለዓለም ዘራፊዎች ሁሉ አጋልጠዋት የዘረፉት ገንዘብ ሁሉ ለማሸሽ እንዲመቻቸው ፊታቸው ወደ ቻይና ማዞር ከጀመሩበት ወቅት ጀምሮ ወደ ልጣን ያወጡዋቸውና በገንዘብ ሲደጉሙዋቸው የነበሩት አሜሪካኖች ነገረ ስራቸው ስላልተመቻቻው በምትካቸው ሌላ “አስበዝባዥ እና ታዛዥ” ቡድን መተካት ስለነበረባቸው የጃስሚን አብዮት Jasmine Revolution መሳይ ቀስ እያለ በኢትዮጵያ ሲቀጣጠል ቆይቶ እንደምታውቁት ያንን ‘ሕዝባዊ አመጽ’ በመጠቀም ሴረኛው እና ተንኮለኛው አብይ አሕመድ የተባለ “የኦሮሚያ እና የአፍሪካ ፕሮጀክት ንድፍ አቀንቃኝ ለበርካታ ወቅቶች” ውስጥ ለውስጥ ስልቱን በተጠና ዘዴ እየተሰራበት ቈይቶ በሚገርም ስልት ወደ ሥልጣን እንዲወጣ ተደርጓል።

ያማሞቶ የተባለው መሰሪ ጃፓናዊ አሜሪካዊ ዲፕሎማት “ፐራያ ስቴት” (ባይተዋርዋ አገር) ተብላ ለ27 አመት ተገልላ ሕዝብዋ ስታሰቃይ የኖረቺው የስቃይና የእሪታ ምድር ወደ ሆነቺው ወደ ኤርትራ በመጓዝ ኢትዮጵያ ውስጥ አብይ አሕመድ የተባለ ወታደራዊ ኮሎኔል ወደ አገር መሪነት እንደሚመጣ መወሰኑን የ ‘ሲ አይ ኤ’ ወዳጅ ለሆነው ለኢሳያስ አፈወርቂ አብስሮት ለሁለቱም ሕዝብ “ደንገተኛ” የሆነ የድምበር መከፈት እንደተከሰተ ሕዝብን 'በአፍዝዝ ወ አደንዝዝ' በስሜት አስክረው እምባ አራጭተው በማስጨፈር እንደገና በሕዝቡ ሕሊና በመጫወት ድምበሩን ላሁኑ እንዲዘጋ ተደርጓል።ኢትዮጵያ ወደቦቿን በባንዳ ልጆቿ ተባባሪነት የተፈጸመባት ሴራ ማጋገም አቅቷት ይኼው እስከዛሬ ድረስ አገራዊ መሪ እንዳይኖራት የመደረጉ ዋናው ሴራ እና ምልክቱ እንዲህ ያለ ቲያትር ማየት አንጀት ያሳምማል።

ይህ ምስጢራዊው PSD-11 ዘመቻ የሚካሄደው በብዙ ቅርንጫፍ ቢሆንም ዘመቻው ሲመራው የነበረው በኦባማ የአገራዊ ደህንነት ባልደረቦች እና በእነ ‘Dennis Ross, Samantha Power, Gayle Smith, Ben Rhodes, and Michael McFaul.” የተባሉ በበላይነት መዋቅሩን ይሚመራ ምስጢራዊ የዘመቻው መሪዎች ናቸው  እንደምታውቋት Gayle Smith ማለትGuerilla Mistress” በመባል የምትታወቅ  (“Guerilla Mistress To Obama Confidant; The Life And Crimes Of Gayle Smith (By Thomas C Mountain 01 December, 2010 Countercurrents.org የሚለው ጽሑፍ አንብቡ) በዚያ “Guerilla Mistress”  እየተባለች የምትታወቅዋ ይህች ሴት የወያኔው “ተወልደ ጃማይካ”  ውሽማ የነበረች ( በ1980 ዎቹ (በፈረንጅ ዘመን) በ ሲ አይ እና በመለስ ዜናዊ መካካል ምስጢራዊ ተልዕኮዎችን እንደ ድልድይ ሆና የሰራች እና ዛሬም አገራችን ውስጥ ሆና “ዩ ኤስ ኤይድ” በመባል የሚታወቀው በአሜሪካን ኤምባሲዎች ስር የተዋቀረ “የ ሲ አይ ኤ  “ሰብኣዊ ተራድኦ ድርጅት” (ለስለላ ስራ በሽፋን የተዋቀረ ድርጅት) በበላይነት ተጠሪ ሆና እየሰራች ያለች ከዚህ በታች ፎቶግራፍዋ የምታይዋት ሴት ነች።

 እንግዲህ እነዚህ ናቸው የአገራችንም ሆነ የዓረቡ ዓለም መፍረስ አቅደውታል የሚባሉት ሰዎች።

እነዚህ ሰዎች በሚመሩት ምስጢራዊ ዘመቻ ሩስያንም ሆነ ሌሎች አገሮችን ለማፍረስ በዋናነት የሚጠቀሙበት ስልት ኢላማ በሆኑት የአገር መሪዎች ላይ የመሪ ለውጥ ለማድረግ ሲፈልጉ በእዛው አገር ውስጥ “ሁማን ራይት፤ ዩ ኤስ ኤይድ…..መንግስታዊ ያልሆኑ በጎ አድራጊ ድርጅቶች፤ አይ ኤም ኤፍ (የገንዘብ አበዳሪ ድርጅቶች)…” የመሳሰሉትን በአገሪቱ ውስጥ እግር እንዲተክሉ ካደረጉ በላ የሚከሰቱ የሕዝቡ ተከታታይ ቅሬታዎች እንዲባባሱ በማድረግ ሚና ይሰጣቸዋል።  

ወደ ኋላ ስንመለስ ለምሳሌ የእንቅስቃሴው ተዋናይ የሆነ ‘በአረቡ አለም’ “እስላሚክ ብራዘር ሁድ” (ኣኽዋን) የተባለ “አይሁዶችን ለመምታት” ከናዚ ጋር ሲሰራ የነበረው፤ በኋላ ግብጽ ላይ እንደ አዲስ የተዋቀረው አኽዋን በዓረብ አገሮች እና እስላማዊ አገሮች ብጥብጥ ለማስነሳት ያለው ሚና አሜሪካኖች እንዴት እንደሚጠቀሙበት ከላይ የጠቀስኩት መጽሐፍ ማንበብ ይጠቅማል። የአኽዋን የሽብር ድርጅት መሪዎች ከዚህ ከተጠቀሰው የአሜሪካኖች የዘመቻ ዕቅድ በምስጢር በመገናኘት ከአሜሪካኖችየመሳሪያ እና ገንዘብ ዕርዳታ በማግኘት” በሕዝብ የሚሰሙ ስሞታዎች እና የሚታዩት ተቃውሞዎችን እንዲባባሱ በማድረግ እሳት ይለኩሳሉ። በአፍጋኒስታን፤ በኢራቅ፤ በቱኒዚያ፤ ግብጽ፤ሊቢያ፤በሶሪያ፤ሶማሊያ…በመሳሰሉ አገሮች “ኣኽዋን” አሜሪካኖች ከሚለግሱዋቸው ምስጢራዊ ድጋፍና ማበረታታት ተደግፎ አገር እንዲፈርስ መሪ እንዲለወጥ ያደርጋሉ።

ኢትዮጵያም ውስጥ የተደረገው ይህንኑ ነበር። ለበርካታ አመታት በባሌ፤በወሎ’ ባዲስ አበባ ፤በጅማ በበርካታ ኦሮሞ እና ምስራቃዊ ኢትዮጵያ “አኽዋኖች” ተስፋፍተው በርካታ ጥፋት አድርገዋል። ዛሬም ዘመናዊ ትምሕርት የቀሰሙ ወጣት “አኽዋኖቹ ለጊዜው አንገታቸውን አቀርቅረው ቢታዩም ቡዙዎቹ በተገንጣዮች በተለያዩ ድርጅታዊ መዋቅሮች እና ብዙዎቹም በፖለቲካ ተሰግስገው በምስጢራዊ ሽፋን “ፖለቲካል እስላም” በማካሄድ ላይ ናቸው።

ለምሳሌ ጃዋር የተባለ የሚናገውን ንግግር ሳያሸማቅቀው በግልጽ ማንነቱን ሳይደብቅ “የኦረሞ ፖለቲካ” ከፖለቲካል እስላም ጋር መያያዝ  እንዳለበት የሚሰብክ የቄሮ ኦሮሞ ዋና ተዋናይ “በሚደርሰበት አቤቱታም ሆነ ፔቲሽን/ ክስ” አሜሪካኖች ከአሜሪካን ያስወጡት ነበር። ሆኖም ያ ተቃውሞ ከአሜሪካኖች ፍላጎት ጋር ስለማይጣጣም ጉዳያቸው አይደለም። ብርሃኑ ነጋ አሜሪካዊ ዜጋ ሳይሆን መንግሥት በብረት ትጥቅ አስወግዳለሁ ብሎ አሜሪካ ውስጥ የሚዲያ ተቁዋም (ኢሳት)
መስርቶ እራሱም በፈለገበት ወቅት ያለ ምንም ስጋት የኤርትራን ፓስፖርት እና የአሜሪካ ፓስፖርት የመሳሰሉ እየተጠቀመ ሲዞር ምንም አልተነካም። ብርሃኑ ነጋና ብርቱካን ”የያስፖራ ማሕበረሰብ አንድነትን” ለማፍረስ ወደ አሜሪካ እንዲመጡ አሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ሲፈቅድላቸው ‘ሃይሉ ሻውል’ ወደ ካናዳም ሆነ በላም ወደ አሜሪካ እንዳይሄዱ ተከልክለው እንደነበር የሚታወስ ነው።

ለምን ቢባል እነዚህ ሁለቱ ሰዎች በአገራችን ላይ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አሜሪካኖች ያውቃሉ። በስልጣን ያስወጥዋቸው ስርዓቶች በማንኛውም ወቅት ከተሰጣቸው የታዛዥ አገልጋይነት ፈቀቅ ካሉ ፤ እነዚህን ግለሰበች በመጠቀም ተከታዮቻቸውን አመጽ እንዲያስነሱ በመገፋፋት ስርዓቱ እንዲለወጥ መሳሪያ አያደርጉዋቸውም ማለት አይቻልም።

ሁለት ክስተቶችን ልጥቀስ፤ ቱኒዚያ እና ኢትዮጵያ። ቦአዚዝ የተባለው ቱኒዚያዊ የሱቅ በደረቴ የቀን ሰርቶ አደር የሥራ ፈቃድ ማስረጃ ከሌለህ ጉቦ ስጠኝ ብላው ገንዘብ እንደሌለው ሲነግራት “ለመሸጥ ይዞት የነበረው ፍራፍሬ አትክልት በመድፋት ''ነገዱን እና የቤተሰቡ ማንነት አንስታ” መጥፎ ስም በመስደብ በጥፊ ስለመታቺውየደረሰበት ጥቃት አቤት ለማለት ወደ ባለስልጣኖች ቢሄድም እዛውም በባሰ መልኩ ስላመናጨቁት “ሕግ ባለመኖሩ በዚህ ብስጭትና ውርደት ከመኖር አገሬው አብዮት እንዲያስነሳ ማስታወሻ ጽፎ በመተው ቤንዚን እራሱ ላይ አርከፍክፎ ራሱን አቃጥሎ ገድሏል።” በዚህ የተነሳ ሲቀጣጠል የነበረው ተከታታይ የቱኒዚያ የሕዝብ ብሶት ለማቀጣጠያ መነሻ ሆኖ በመላ አገሪቱ አብየት ተነስቶ መሪው “ቤን አሊን” ተወገደ።

የቱኒዚያ አብዮት እንዲቀጣጠል ትልቅ ሃይል የሆነው የቦአዚዝ” ምክንያት ይሁን እንጂ ከበስተጀርባው ክርቢቱን ያቀጣጠለው በአሜሪካኖች (ናሺናል ኤንዳውመንት ፎር ዲሞክራሲ/National Endowment for Democracy) ተብሎ የሚጠራ የስለላ መዋቅር ድርጅት ‘የቱኒዚያ ወጣቶች ዲሞክራሲን ላማጎልበት’ በሚል ስም $131,000 ለዚህ Al-Jahedh Forum for Free Thought (AJFFT) የተባለ ‘አኽዋን’ ወጣቶች (አክራሪ ለሆነው ሙስሊም ብራዘር ሁድ) በመለገስ ነበር አመጹ ተቀጣጥሎ ቤኒ አሊ ከሥልጣን እንዲወገድ የተደረገው። ኔድ/ NED/ የተባለ ይህ የስለላ ድርጅት ለነሱ ብቻ ሳይሆን የጎዳና ነውጡን ለማፋፋም በእዛው በ2009 (በፈረንጅ ዘመን) (APES)፣ (CEMAREF)….” ለተባሉ ማሕበራትምህራን እና ለወጣቶች በሥልጣና ሽፋን ገንዘብ አፍስሷል። በዛውም ተሳክቶለታል።

በተመሳሳይ በደቡብ የአገራችን ክፍል አዋሮ በተባለ አውራጃ ዋካ በተባለ አካባቢ “የኔ ሰው ገብሬ” የተባለ መምህር “ፍትሕ እና አስተዳዳር” በኢትዮጵያ መበላሸቱን ያሰተዋለ ይህ አርበኛ ሕዝብን ያስነሳ ይሆናል በሚል እምነት ሕዳር 1/2004 ዓ.ም (በኛ ዘመን አቆጣጥር) እራሱን ቤንዚን አርከፍክፎ በማቃጠል እራሱን የሳዋ ይህ አርበኛ ሲሞት፡ ለሞቱ ሰበብ የሆነውን የዱርየዎቹ የወያኔ ስርዓት ለምን በጉዳዩ ማጣራት አላደረገም ብለው ፓርቲዎች መንግሥት እንዲያጣራ መግለጫ ከማውጣት ያለፈ ያሳዩት ሕዝባዊ ተቃውሞ አልነበረም። ሕዝቡም ከቤተሰቡም ሆነ ከሚያውቁት ባልደረቦቹ ጤነኛ እንደነበር እና በስርዓቱ እንዳልተደሰተ ሁሌም ይናገር እንደነበር በቂ መረጃ ቢዘረጋም ሕዝቡ እንደ ቱኒዚያው ቦኣዚዝ ሆ ብሎ የወያኔዎቹን ስርዓት ለመገርሰስ “አልተነሳም”። ምክንያቱም መለስ ዜናዊ የለየለት የአሜሪካ  ቅጥረኛ እና አገልጋያቸው ስለነበር ምስጢራዊው PSD-11 ዘመቻ መሪዎች ልክ ቱኒዚያ ውስጥ የተጠቀሙት የቡአዚዝ አይነት የጎዳና ነውጥ አቀጣጣዮች ኢትዮጵያ ውስጥም በገፍ ቢኖሩም በወቅቱ  ሊጠቀሙባቸው አልፈለጉም እና የየኔ ሰው ገብሬ’ ን መስዋእት ከንቱ ሆኖ እንዲቀር ሆኗል።

መለስ ዜናዊ ከሞተ በላ ግን በሚፈልጉት መንገድ እንደመለስ ዜናዊ  ዓይነት አፈ ጮሌ በየአፍሪካም ሆነ በየአለማቱ እየዞረ የሚያያጃጅል ምላጭ አፉ’ አገልጋይ ስላጡ፤ መለስ ዜናዊ ትቷቸው የሄደው የትግሬ “ጀዝባ” ጎሬላ መሪዎቹ ለዚያ ወንበር ስለማይመጥኑ ከመለስ ዜናዊ እጅግ የተለ የፖለቲከኞች እና የጤነኛ ምሁራን ሕሊናን የሚያደነዝዝ ‘በአፍዝዝ ወ አደንዝዝ’ ስልት የተካነ አብይ አሕመድ የተባለ አደገኛ የሕሊና ጠላፊ ወታደራዊ ኮለኔል እና የዶክተሬት ትምሕርት ያለው የስርዓቱ ኣባል የነበረ በነገዱ “ኦሮሞ” የሆነ አገልጋይ ስላገኙ ምርጭያቸው አደረጉት። ስለተሳካላቸውም ብዙ ሰው ያከበራቸው ዩኒቨረሲቲ ታዋቂ ምሁራን “እንደ አብይ የመሰለ ደፋር መሪ አላየሁም” እያሉ መሳቂያ ምሁራን ሆነው ሕሊናቸው ተጠልፎ ለማየት በቅተናል።

መለስ ዜናዊን የሚተካ ሰው በመገኘቱ ልክ እንደቱኒዚያው ጃስሚን አብዮት Jasmine Revolution (የኑሮ ምስቅልቅል እና ሰብአዊ ጥሰት ያስከተለ ተከታታይ ሕዝባዊ አመጽ) ስልት በመላ ኢትዮጵያ በመቀጣጠሉ የኦሮሞ እስላማዊ ሃይሎች፤ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች እና ኦሮሞ ቄሮዎች ለዚህ ምቹ መሰሪያዎች ነበሩና አመጹ እንዲቀጣጠል እውን ተደረገ። ከመቀጣጠሉ በፊት በርካታ የተቃዋሚ መሪ ተብየዎች እና ጠባቡ እና አደገኛው ጸረ ኢትዮጵያ መረራ ጉዲና ለበርካታ ጊዜ በመመላለስ ስልጠና እንዲቀስም ተደርጓል። በእግረ መንገዱም ሚኔሶታ ድረስ እየሄደ ኦሮሞ ወጣቶች እና ተዋቂ ኦሮሞችን አንድነት አንዲፈጥሩ በማበረታታት “አገራችሁ ውስጥ ሪፑበሊክ ማቋቋም ባትችሉም ሙኔሶታ ውስጥ ‘ሪፑብሊክ’ መስርታችል…..” በማለት የወደፊቷን ኦሮሚያ ለሪፑብሊክ ምስረታ እንደምትሄድ ሲያስተምራቸው እንደነበረ ካንደበቱ የተናገረው ሰነድ አንድ ወዳጁ አስደምጦኛል።አብይ አሕመድ እና ጃዋር መሓመድም ምስጢራዊ በሆነ የኢመይል ግንኙነት ይጻጻፉ እንደነበር ጃዋር እራሱ ተናግሯል።

የእነ ቄሮ እና የነ ጃዋር እንቅስቃሴ ልክ እንደ ቱኒዚያው ሳይሆን በከፋ መልኩ “መረራ ጉዲና፤በቀለ ገርባ፤ዳውድ ኢብሳ፤ነጋሶ..” የመሳሰሉ የነገድ ፌደራሊዝም አስታክኮ ‘ኦረሚያ ሪፑብሊክን’ ሲሰብኩ ያንን ለማጠናከር “ዶ/ር እዝቄል ጋቢሳ የተባለ የፕሮተስታንት ፓስተር” የነበረ (ልጆቼን አማርኛ ባለማስተማሬ ኩራት ይሰማኛል ብሎ ያለ) ደግሞ በልዩ የስራ ምደባ ተሰማርቶ ከሜኔሶታ ወደ ኢትዮጵያ ሄዶ “የተወሰኑ የደቡብ” ነገዶችን በመሰብሰብ “እኛ ኦሮሞዎች እና እናንተ ‘ኩሽ’ የምንባል ዘሮች ነን። እኛ ኩሾች “ሰሜቲክ” ልሳን ከሚናገሩ ቋንቋ ተናጋሪዎች የተለየን ዝርያዎች ስለሆንን ልዩ ማሕበረሰብ መን ዓለም ስትፈጠር ወደ ነበርንበት ልዩ ዝርያነታችን ይዘን እንገንጠል እያለ በመቃዠት ሕዝብን እና ቤተሰብን የሚነጣጥል አደገኛ የዘር ፖለቲካ እንዲቀሰቅስ በቅጥረኛው አብይ አሕመድ ተፈቅዶለት የተጠቀሰው ሚስጢራዊው አገር የማፍረስ ዘመቻ አገራችን ውስጥ እየተጧጧፈ መሆኑ ለመረዳት አያዳግትም። በዚህ ዘመቻ መሳሪያ ሆነው የታጩ እና አገልጋዮች የሆኑ ነጭ ባንዴራ አውለብልበው እጃቸውን ለአገር አፍራሹ ቡድን አብይ አሕመድ በመስጠት አገር ውስጥ እንዲገቡ ተፈቅዶላቸው በተምበርካኪነት የዘመቻው አካል የሆኑት ነጭ ባንዴራ አብለውላቢዎቹም በማፍረስ ሂደት ላይ የሚኖራቸው ሚና በሚከተለው…. ክፍል ሁለት እንመለከታለን።….. ይቀጥላል………
ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ)


Sunday, May 19, 2019

የእነ በርሃኑ ነጋ ኢዜማ ፕሮግራም ስለ መገንጠል ያለው አቋም ከጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ አዘጋጅ Ethio semay)


በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤትነት የተመዘገበችው ኢትዮጲስ ጋዜጣ ዋና ዘጋቢ ጋዜጠኛ ምስጋን ጌታቸዉ በፖሊስ ተደቦድቦ ታሰረ
May 22, 2019


የኢትዮጲስ ጋዜጣ ዘጋቢ በፖሊስ ተደቦድቦ ታሰረ፡፡ ዛሬ ጠዋት 4ኪሎ አካባቢ ቤታቸዉ ሲፈርስባቸዉ የነበሩትን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ቅሬታ ሊዘግብ በሄደበት ወቅት ከቢሮ እንደወጣ በመንገድ ላይ ፖሊሶች ጠብቀዉ በመደብደብና በእጁ የነበረዉን ካሜራና ሌሎች እቃዎች ቀምተዉ ወደ ጣቢያ ወስደዉታል፡፡ጋዜጠኛ ምስጋን በአሁኑ ሰዐት አራዳ ፖሊስ ማዠዣ ጣቢያ ታስሮ የሚገኝ ሲሆን በድብደባ ጉዳት ያደረሰበትን ፖሊስ ለመክሰስ ምስክር ቢጠራም አይሆንም ተብሎ ሲደበድቡት ያዩ የአይን እማኞች ከግቢ እንዲወጡ ፖሊስ አድርጓል ሲል ስንታየሁ ቸኮል ያደረሰን ዘገባ አመልክቷል።

የእነ በርሃኑ ነጋ ኢዜማ ፕሮግራም ስለ መገንጠል ያለው አቋም
ከጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ አዘጋጅ Ethio semay)

ሰሞኑን እንደሰማችሁት ከተለያዩ የከሰሙ (?) የፖለቲካ ድርጅቶች/ፓርቲዎች/ ተወጣጥተው የመሰረቱት ኢዜማ የሚባል አዲስ ፓርቲ መመስረቱን ሰምታችሁ ይሆናል። ይህ ድርጅት የመሰረቱት ያው የሚታወቀው ባለፈው ሰሞን ትችቴ የተቸሁት ብርሃኑ ነጋ እና እንዲሁም ዛሬ ይህንን ዕድል ተጠቅሜ በትንሹ የማሳያችሁ የድሮ በወያኔ ፓርላማ/ምክር ቤት ተመራጭ የነበረው “መለስ ዜናዊ ሞቷል፤ የሞተን ሰው የሰራውን ሓጢያት እያነሳን ማውራት እናቁም” እያለ ሲቦተልክ የነበረ እና በቅርቡም የእስክንድር ነጋን ሕዝባዊ ጥያቄየማየው በጎሪጥ ነው” ብሎ ያለን እና እንዲሁም ትግሬዎች የበላይነት ከተንጸባረቀበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 12 አብራሪዎች እና 4 ቴክኒሻኖች (ብዙዎቹ አማራዎች) ሲባረሩ ወጣት ግርማ ሰይፉ በሚያስደነግጥ አነጋገር “ካፕቴን አበርሃም ጥበቡ” የተባለ በነገዴ/በዘሬ ምክንያት ብዙ ግፍ ደርሶብኛል ብሎ “ፓይለት ሆኖ ባርያ ከመሆን አርሶ አደር ሆኖ በነፃነት መኖር”  መሆን ይሻልል ብሎ አብራሪነቱን ትቶ ወደ አራሽ ገበሬነት የተለወጠው ግፍ የደረሰበት ዜጋችንን
“በማንነቴ ከሥራ ተባረርኩ ለሚል ዛሬ ጆሮ የለንም፣ ለምን ያኔ አላልክም? ብለን እንጠይቃለን። ፈርቼ፣ የት፣ ምናም ከሆነ መልሱ ፈሪ ከዚህም በላይ ይጠብቀዋል (የታረመ ፊደል)። ለፓይለትነት ከመውረድ በላይ የት እንዳያውርዱት ነው የሚፈራው። የት ሆኖ ልጅ ለማሳደግ ብለዋል ዶር ሀይሉ አርሃያ። ጎበዝ በብሄር ማንነት ተባረርኩ የፓይለቱን ከተቀበልኩ፣ የልደቱንም መቀበል ግድ ይለኛል። መውረድ አቃተኝ አልሞክረውም። "በመንጋ መንጫጫት እውነት አይፈጥርም። ፓይለቱ ወንድማችን በግብርናው ዘርፍ ምን አሰመዘገበ? ለአካባቢው አርሶ አደሮች ሞዴል ነበር? ወይስ ያው እንደ አነርሱ አራሽ ሆነ?" (አቶ ግርማ ሰይፉ ማሩ)

 በማለት ግፍ በደረሰበት ወገናችን ሲያሾፍ የነበረ እና የመሳሰሉ ሰዎች የመሰረቱት አዲስ ፓርቲ ነው “ኢዜማ” ማለት። ይህ ሰው የፓርላማ ተመራጭ ሆኖ የወያኔ አስተዳዳር በዘር የተዋቀረ ግፍ እንደሚፈጽም እያወቀ ግፍ በተፈጸመባቸው ዜጎች እንዲህ ያለ ጸያፍ ምላስ መሰንዘር ዛሬ በዚህ ፓርቲ ምን ብለው ሊሰብኩን እንደመጡ ግራ ገብቶኛል።

“ኢዜማ’ ብሎ የተጠራው ይህ ድርጅት ከትናንት በስቲያ በድርገጾች በለጠፈው ክፍል አንድ ባወጣው ፕሮግራሙ መፈታት ያለባቸው ባገራችን ውስጥ የተጫነብንን የጠላት ሴራ “በትምህርት ተቋማት፤ በዳንስ ቤቶች፤ እስከ ሚኒስቴር እና የሃይማኖት መሪዎች ድረስ እንደ እሳት ሰደድ የደረሰው የግብረ ሰዶም ወረርሺኝ እና ስለ ባሕር ወደቦቻችንም ሆነ ስለ ኤርትራን ጉዳይ አስመልክቶ” ምንም የተነፈሰው ነገር የለም”። ሌለው ሁላችንም የሚያሳስበንን ጣሊያኖች እና ኢትዮጵያውያን ግራ ክንፍ ፋሺስታዊ ማርክሲስቶች (በትግሬ ወያኔ በመለስ ዜናዊ እና በኦሮሞው ኦነግ መሪነት) የቀረጹልንን አገርን የማፍረስ ተልዕኮ ማለትም ‘ስለመገንጠል መብት መገደብ ወይንም መፍቀድ’ ያነሳው ነገር ምንም የለም። በሚገርም “የሕዝብ ውሳኔ” በሚል ኮድድ በሆነ “ምስጢራዊ አባባል” ግን ሕዝብ ከፈለገ በድምጽ መገንጠል ይችላል በሚል መልኩ አስቀምጦታል።

ትንሿ ትግራይን  ሲም-ካርድ’ (Sim Card ) ሰይሞ፤ ታላቋ ኢትዮጵያንግዑዝየቴሌፎን ቀፎ” አድርጎ የሳላትን የትግሬዎች ትምክሕት በሕግ የተደነገጉ 44 የጎሳ ባንዴራዎች አዘጋጅቶ፤ ለሚገነጠሉ ጎሳዎች አንቀጽ አዘጋጅቶ አገሪቱን ለማፍረስ እንደሰራ ይታወቃል። ኢዜማ በአገር ሰንደቃላማ ላይ ያለው አቋም ግልጽ ሲያደርግ “ስለ የጎሳ ባንዴራዎችም ሆነ ስለ መገንጠል” ምንም ያለው ነገር የለም። ኢዜማን እየመራ ያለው ብርሃኑ ነጋም ካሁን በፊት በግልጽ እንዳስቀመጠው “አንድ ጎሳ/ቤተሰብ… እገነጠላለሁ ካለ በጠምንጃ አንይዘውም በደምጽ መገንጠል ይችላል ብሏል” አሁን ያንን በውስጠ ሴራ ‘ኢዜማ’ ከዚህ በታች እንደሚከተለው አስቀምጦታል።

“1.1.3. ማንኛውም የፖለቲካ ጥያቄዎች በውይይት እና በዴሞክራሲያዊ ስርኣት እንዲፈቱ ይደረጋል፡፡ እንደ አስፈላጊነቱ ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮች ወደ ህዝብ ውሣኔ እንዲሄዱ ስርዓት በማበጀት የህዝብን ውሣኔ ተግባራዊ ይደረጋል።” ይላል።

ይህ አባባል ወደ ጎረቤት አገሮች እንቀላቀላለን፤ወይንም እራሳችን አገር እንሆናለን (እንገነጠላለን) የሚሉ ነገዶች /አካባቢዎች/ወረዳዎች /አውራጃዎች/ ቤተሰቦች… ካሉ ”ወደ ህዝብ ውሣኔ እንዲሄዱ ስርዓት በማበጀት የህዝብን ውሣኔ ተግባራዊ ይደረጋል” ማለት ነው። የፍሬ ነገሩ ዋና ማጠንጠኛው እዚህ ላይ ያለቀ የደቀቀ ያደርገዋል። እነዚህ የበሰበሱ ደካማ ፖለቲከኞች በመሰረቱት አዲስ ፓርቲ ውስጥም የወያኔ ቀጥተኛ ቅጂ “ሕዝበ ውሳኔ” በሚል ሊሂቃን የሚፈበርኩትና የሚያቀጣጥሉት የተቆነጃጃ ማጃጃያ ቃላት ተጠቅመው አገር ለማፍረስ ወደ ላ እንደማይሉ የተረዳንበት አንቀጽ ነው። እንግዲህ ሕዝበ ውሳኔ የሚባለው ወሳኙ ብዙ ሳይሆን አንድ ሰው ነው

ለመሳሌ ሁለቱ ተቀናቃኝ ክፍሎች 50% ሌላኛው ደግሞ 50% ድምጽ ካገኙ ለመገንጠል የሚፈልገው ክፍል ማግኘት ያለበት ደምፅ 50%+1 ከሆነ በአንድ ሰው የካርድ ምርጫ ምክንያት አገር ይፈርሳል ማለት ነው። በቃ! ይህ ነው ሕዘበ ውሳኔ ማለት “ሕጋዊ አምባገነንነት” ማለት ነው። በሕዝብ ድምጽ ተንተርሰው የአንድ ሰው ካርድ “ወሳኝ ደምፅ” ሆኖ እንዲህ ያለ አገር በማፍረስ አሰራር ውስጥ ኢዜማም ገብቶበታል። ጠየተቀሩት ፌደራል ምናምን ምናም የሚሉ የተቀባዠሩ “ዲሞክራት ተቃዋሚ ፓርቲዎችም” ከዚህ ወረርሺኝ አልተላቀቁም።
ስለ ሰንደቃላማ ያወጣውን እንመለክት።
“2.6. የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ይሆናል፡፡ የመንግሥት ዓርማ የሚያስፈልገው ከሆነ በሕዝብ ይሁንታ የሚወሰን ይሆናል፡፡” ይላል።  (ይህም 50%+1 ማግኘት ማለት ነው)። እኔ ግራ የገባኝ “ለምንድነው የመንግሥት ዓርማ የሚያስፈልገው?” የኢትዮጵያ ሰንደቃላማ የመንግሥት ነው፡ አይደለም እንዴ? የኢትዮጵያ ሰንደቃላማ “አረንጓዴ፤ቢጫ እና ቀይ” ከሆነ  ሌላ የመንግሥት ዓርማ ለምን ያስፈልጋል? ሌላ  ዓርማ ማውለብለብ ምን ማለት ነው። ሌላ  ዓርማ እንዲያውለበልብ አይፈቀድለትም ብሎ እቅጩን ማሳወቅ ምንድ ነው ችግሩ?

“1.1.4. የኢ-ዜማ የፖለቲካ ፕሮግራም በማንኛውም ሁኔታ የዜጎችን የኤኮኖሚ ነፃነት፣ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሁም የመኖሪያ ምድራችንን ከባቢ ሊጎዳ በሚችል መልኩ አይገረጽም።” ይላል

የመኖርያ ምድራችንን አካባቢ በሚጎዳ መልኩ እንዲቀረጽ እንፈልጋለን ብሎ አንዱ ክፍል ቢነሳ መፍትሔው ያው “የሕዝብ ውሳኔ” ሊሆን አይደለም ወይ? የሕዝብ ውሳኔ ገደቡ የት ነው? መንግሥት የሚባል ፈርጠም ብሎ መወሰን መብት የለውም? መገንጠል ትችላለህ ተብሎ ሁሉም በሕዘብ ውሳኔ የሚወሰን ከሆነ አካባቢየ በሚጎዳ መልኩ በፈለግኩት ልቅረጽ ቢል የሚያቆመው አካል ማን ነው?

“1.1.5. ዜጎች ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎችንም መብቶቻቸውንና ጥቅሞቻቸውን ለማስከበር በጋራ የመደራጀት፣ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብታቸው ይከበራል።” ይላል።

ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት አከብራለሁ ካለ የሸሪዓ/የካሊፋ/ መንግሥት(እስላማዊ መንግሥት) ይመስረት ብለው አንገታቸውን ለጊዜው አቀርቅረው ውስጥ ለውስጥ በፖለቲካ ድርጅቶች ተሸሽገው ያሉት ነግር ግን በፓልቶክ እና በየ ዩቱብ ላይ በወጣቶች በተለይም በወጣት እስላም ሴቶች እህቶቻችን ሕሊና ውስጥ መርዝ የሚረጩት “የኢትዮጵያ ሙስሊም ብራዘር ሁድ” ዜጎች ስለሆንን “ተደራጅተን ሃሳባችንን እናሰራጭ” ቢሉ ኢዘማ በዚህ መልኩ በነፃነት መብት ሰበብ “የመደራጀት፤የመሰብሰብ፤የመስበክ እና የማወጅ ነፃነት መብታቸውን ሊያከብር ይሆን”? 

“1.1.6. የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ሊገሰስ የማይችልና የማይገሰስ መሆኑን፤ በኢትዮጵያ ሉአላዊ ግዛት ውስጥ የሚገኝ ማናቸውም የተፈጥሮ ሃብት የሃገሪቱ ዜጎች ሁሉ የጋራ ሃብት መሆኑን ኢ-ዜማ ያምናል።” ይልል።

በሕገ ወጥ የተነጠቅነውን ሉአላዊ ኤርትራ ውስጥ የሚገኝ ሃብቶቻችን ፤ገዳሞቻችን ወደቦቻችንን እና ሳይወዱ በግድ ለሁት የተከፈሉት ነገዶች እና ቤተሰቦች “ሉአላዊ ግዛትነት” ኢዜማ ምን አቋም አለው? ምንም! አስመራ ውስጥ ከኢሳያስ ጋር ሲሞዳሞድ የነበረው ከብርሃኑ ነጋ ይህንን የሚታሰብ አይደለም።ያኔ ስለ ባሕር ወደብ ያለውን አቋም ተጠይቆ እኛ ንቅናቄዎች ነን እለ ወደብ እና ኤርትራ ጉዳይ ለመወሰንም ሆነ አቋም ለማስያዝ መብት የለንም ሲል አሁንም አገራዊ ፓርቲ ብሎ አዲስና ‘ሕጋዊ ፓርቲ’ ሲመሰርትም ያንኑ አቋሙ እንደጠበቀ ነው!

“1.2.3. የየራሳቸው ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ ይኖራቸዋል፡፡ የአካባቢ መስተዳድሮች የራሳቸው የወንጀል መቆጣጠሪያ የፖሊስ ተቋም ይኖራቸዋል።” ይላል።

ሁለት ነገሮችን ላንሳ። የአካባቢ ፖሊሶች ሲባል ምን ማለት ነው? የነገድ ፖሊሶች ናቸው? (ምክንያቱም በፕሮግራሙ ላይ ‘አንዳንድ ቦታ ውስጥ ቋንቋን ያማከለ መስተዳድር/አከላላል ይከተላል ይላል) እንዚህስ በምን ስም ነው የሚጠሩት (በቋንቃቸው ‘ኦሮሚያ ወዘተ ያ ወዘተ ያ… ወይስ ሌላ መጠሪያ ሊሰጣቸው ነው?)። ለምንድነው ካሁኑኑ የሚዋቀሩት አስተዳደራዊ አካባቢዎች ማን ከማን እንደሚዋሃድ ወይንም ብቻውን (ቋንቋ መሰረት አደርጎ) የሚተዳዳር/የሚቀረጽ አካባቢ/ነገድ/ በፕሮግራማቸው ግልጽ አድርገው ሊነግሩን ያልፈለጉት? ይህንን በተመለከተ በፕሮግራሙን ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ አላገኙትም? ካልሆነ ፕሮግራማቸው ይህ ብቻ ከሆነ ይፕሮግራሙ ግልጽነት ጥያቄ ጭሮብኛል። 

ከምድሪቱ እትብት ተለይተው ብቻቸውን ርቀው የተጓዙት አራዊቶቹ የወያኔ መሪዎች በቅኝ ግዛት ያልተገዛው ይህ ኩሩን ሕዝብ የሚቀጠቅጡት የወታደሮቹ ማዕረግ ስም፣ ንግድ ቤቶቹ፣ ትምህርት ተቋማቱ፣ /ሀገሮቹ (ዞን) ጎዳናዎቹ በባዕድ ቋንቋ ተሰይመዋል። የወታደሮቻቸው “መታወቂያ” ባጅ/በደረታቸው የሚታይ ስማቸው/ የሚጻፈው በእንግሊዝኛ ነው፡ ማዕረጋቸውም ኮማንደር፣ ኮንስታብል፣ ኢንስፔክተር፣ ሱፐር ኢንስፔክተር፣ ሱፐር ኢንቴንዳንትነው።ሻምበል፣ ሻለቃ፣ መቶ አለቃ፣ ሃምሳ አለቃ፣ አሥር አለቃ…. የሚሉ አገር በቀል ወታደራዊ መጠሪያዎች የአማራዎች ነውና “በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት እንደተገዙት  የኬኒያ እና የናይጄሪያ ፖሊሶች” ስያሜ ወስደን በላቲን ማዕረግ ሰይመናቸዋል ብለውናል። አማራና አማርኛን ለማጥፋት የተነሳንበት ዓላማ ነውና ስትፈልጉ አልቅሱ ይሉናል። በዚህ መልክ እያለቀስን 28 አመት ይኼየው ዛሬም ቀጥሏል።የቆየውን ይህ የቅኝ ገዢነት ወደ አገራዊ ስያሜ (ወደ ነበረበት) ለመመለስ ኢዜማም ሆነ ሌሎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዚህ ላይ ምን ሃሳብ አላቸው? መልሱን እጠብቃለሁ።

መዝናኛ ስፍራዎች ንግድ ፤ትምሕርት ቤቶች የተሰየሙበት ላቲናዊ፤ዓረባዊ፤ጣሊያናዊ፤ቻይናዊ ስያሜ ያላቸው መጠሪያዎቻቸው “አገርኛ” በሆነ “የስም መጠሪያ” እንዲሆን በሕግ እንዲጸድቅ ኢዜማ ይሰራል ወይስ እንደ ድሮው ተቃዋሚዎቹ ተበባሪነታቸው/ቸልተኛነታቸውን ይቀጥሉበታል? 
አመሰግናለሁ - ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)


Thursday, May 16, 2019

የብርሃኑ እና የብርቱካን መዲቅሳ አዲሱ ሴራ በልደቱ አያሌው ፓርቲ ላይ! ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)


አሁን የደረሰኝ ትኩስ ዜና

ትናንት ሓሙስ (5/16/2019) ባሕር ዳር ከተማ ውስጥ ከሌሊቱ 5 ሰዓት ያልታወቁ ሰዎች በየመንደሩ እየዞሩ በተለይ ቀበሌ 5 እና 6 የሰው መኖርያ  ቤቶችን  ማቃጠል እና ጥይት መተኮስ እንዲሁም የመንግስት ህንጻዎች እና የሆቴሎች መስተዋቶችን ሲሰባብሩ አድረዋል። የሚቆጣጠራቸው የመንግሥት ወታደር ወይንም አካል እንደሌለ ከስፍራው ያገኘሁት ቀጥተኛ መልእክት ያመለክታል። ትንሽ ቆይቶ ነገሩ ቢሰክንም ሕዝቡ ግን ሽብር ገብቶበት ማደሩን ካገኘሁት ቀጥተኛ መልእክት ለማወቅ ችያለሁ። ለዝርዝሩ ሰፊውን ዜና እስካቀርብላችሁ ድረስ ተከታተሉኝ። ሥርዓተ አልባው መንግሥት ተብየው የዜጎችን ህይወት ሽብር ውስጥ አንዳይገባ ሽብርተኞችን  ስርዓት ማስያዝ እንዳልቻለ ይህ ማስረጃ ነው። (ዜና ምንጭ Ethiopian semay)

የብርሃኑ እና የብርቱካን መዲቅሳ አዲሱ ሴራ በልደቱ አያሌው ፓርቲ ላይ!   
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)

ልደቱ አያሌው ሲናገራቸው እና ሲቀሰቅስባቸው በነበሩት አንዳንድ ፖለቲካዊ ሁኔታዎቹ እንደብዙዎቻችሁ ቅሬታ እንዳለኝ እና ስተቸው እንደነበረ ታውቃላችሁ ብየ እገምታለሁ። ልደቱ ስሕተቶቹን ተረድቶ እራሱን ‘ትንሽ’ ሞርዶ ለፖለቲካው እራሱን እንደገና ካዘጋጀ ማንኛቸውን ፖለቲከኛ ማስገንደስ የሚችል በርቱ ጭንቅላት ያለው ወጣት ነው የሚል እምነት አለኝ። በዚህ እንተማመን እና ያ እንዳለ ሆኖ የኢሳት ባለቤት የነበረው ግንቦት 7 የተባለ በሰብኣዊ ጥሰት ወንጀል ክስ ሊከሰስ የሚገባው ድርጅት እና ድርጅቱም በበላይነት ሲመራ የነበረው ሴረኛው ብርሃኑ ነጋ አሁን ባለው ‘የአናርኮ የፋሺሰቶቹ’ ስርዐት ምሕረት ተድርጎለት ከአስመራ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ከገባ ጀምሮ ብዙ ክስተቶች አይተንበታል።

ለሥልጣን ከፍተኛ ጉጉት ያለው፤ በቂም እና በሴራ የተካነው ይህ ሰው የመጀመሪያ ሴራውን ማጠንጠን የጀመረው አዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቶ ‘በተከታዮቹ በኩል’ በአደባባይ ኢትዮጵያ ሕዝብ እየተመለከተ እና እየሰማ በተቀናቃኙ በልደቱ  አያሌው ስብእና ላይ ነበር መዝመት የጀመረው። ‘ስሙን በማጉደፍ እና ፎቶግራፉም ተዘቅዝቆ’ ለሕዝብ እንዲታይ ከፍተኛ ዘመቻ ተደረገበት። ይህ ደግሞ ሊረጋ ነው ተብሎ ብዙ ተስፋ የተጣለበት የአናርኪሰቶቹ የፖለቲካ ጥሪ ‘ከውጭ ይዞት የመጣበትን መጥፎ የሴራ ባሕሪውን’ ገና እግሩ መሬት ሳይረግጥ በልደቱ ላይ የጊንጥ መርዙን በመርጨት ግጭት መፍጠር  ጀመረ።

ልደቱ አያሌውም በጨዋ ፖለቲካ ብርሃኑ ነጋን ጋብዞ በሚዲያ እንወያይ ብሎ ሲጋብዘው ግብሩን/ባሕሪው ስላወቀ “አልቀርብም ብሎ ተሸማቀቀ”። ልደቱ አያሌው ብርሃኑን ጋብዞ ለውይይት መጥራቱ ክብር አስሰጥቶታል። እኔ በበኩሌ ተገቢውን ክብር ሰጥቼዋለሁ። 
  
ይቀጥል እና ብርሃኑ ነጋ ከአስመራ ይቅርታ ተደርጎለት በምረት ወደ አዲስ አበባ እንዲገባ ስለተደረገለት ለደስታው ‘ፌስታ’ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ (?) ሰንጋ ጥሎ አሸሸ ገዳየ ሲረግጥ የገዛ ታጋዮቹ ብዙ እሮሮ አቅርበውበት የገዛ ጓዱ ንኣምን ዘለቀም በቅሬታ ከድርጅቱ ተሰናበተ። ይህ ሰው ሰሞኑን ደግሞ በተካነበት የማፍረስ ፖለቲካዊ ሴራ ተጠቅሞ ከፖለቲካ ወደ “ቄሳቄስነት” ባሕሪ የተለወጡ ብርቱ ሲባሉ የነበሩትን ፖለቲከኞች (ለምሳሌ እንደ እነ አንዷለም አራጌን የመሳሰሉትን) ባመሰባሰብ “በአናርኮ ፋሺስቱ ድርጅት” ‘በኦሆዴድ’ ሥልጣን በተመዘዘቺው በብርቱካን ሚዲቅሳ “ትብብር ይደረግላቸው ደብዳቤ ሸኚነት ድጋፍ” ኢዴፓ’ የተባለው የነ ልደቱ አያሌው ድርጅት ሳይከስም “ከኢደፓ ጋር” አዲስ ፓርቲ መስረተናል ብለው ብርሃኑ ነጋ መሪ ሆኖ ሴራ ጎንጉኖ ከልደቱ አያሌው ጋር የነበረው የፖለቲካ ቅራኔ ለመቀስቀስ ሆን ብሎ የቋጠረውን “ቁርሾ” እንደገና ስቀስ ልደቱ አያሌውም ‘ሂደቱ’ በሴራ የተቀናጀ እውነትነት ያልተከተለ “ሕገወጥ ነው” ሲል ተቃውሞውን ለዜና ዘጋቢዎች ቃለ መጠይቅ ሰጥቷል።

ይህ የውህደት አሰራር እውነትም ‘ሕገወጥ’ ብቻ ሳይሆን እንደገና ፖለቲካውን አታካራ ውስጥ ከትቶ ብርሃኑ ነጋ በለመደው ‘የማምታታት’ ፖለቲካዊ ባሕሪው ተጠቅሞ ቅንጅት ላይ በፈጠረው የማፍረስ እና የንትርክ ክስተት በመፍጠር ዛሬም በተመሳሳይ አየሩን እንደገና ለመበከል መዘጋጀቱን የሚያሳየን ምልክት ነው።

የሚገርም ነው! ወይ አዲስ አበባ! የአብይ ድርጅትና የለማ መገርሳ ‘ወንጀለኛው ኦሆዴድ’ እየጎነጎነው እና እየሰራው ባለው አዋኪ መንፈስ ምክንያት የተበከለው አየር እንዳይበቃት ብርሃኑ ነጋ መልሶ አየሩን ተጨማሪ አዲስ አበባበአታካራ ብጥብጥ ሊበክላት እንደገና እየሰራ መሆኑን ስንመለክት አሁንም ወይ አዲስ አባባ! ምኑ ጉደኛ ከተማ ነች? የሚያሰኝ ነው።

የተማረው ለሕዝባችን ጠንቅ ነው እያልኩኝ ስጮህ የነበረው ዛሬም ያው የተበከሉ “ኦልድ ስታብልሽመንት” ወጣት ፖለቲከኞችንም እየበከሉ ስለሆነ ከፖለቲካው ካልተወገዱ ያንን የተበከሉበትን ባሕሪ ይዘው የአገሩቷን ህይወት መልሰው መላልሰው ወደ ባሰው ብጥብጥ እንደሚወስዷት የተነበይኩይትን ትንበያ ያው ህየው እየሆነ የምታዩት ክስተት ነው። የብርሃኑ ነጋ ድረጅት እንደምታውቁት ‘የአንድነት ሃይሉን’ በተለይም አማራውን እጅግ አድርጎ የሚጠላ መሆኑን (ከድርጅቱ የተሰናበቱ አባላቶቹን ያቀረቡት ስሞታ እና ክስ ልብ ይለዋል) እና ካሁን በፊትም አማራ እና ትግሬ ለዘመናት ስለገዙን አሁን የመግዛት ጊዜአችን ወደ ደቡብ ሊሂቃን መዛወር አለበት ብሎ በግንቦት 7 ጋዜጣ አሳትሞ እንዳስነበበን የምታውቁት ታሪክ ነው። የግንቦት 7 አመራሮች (አበበ ቦጋለ የተባለ የፖለቲካ ዋሾም ጭምር) አመራሮቹ በዚህ ጉዳይ ሲጠየቁ ይህንን መጻፉን አናውቅም ፤ ወይንም አልተመለከትኩትም እንዲህ የሚል ካለ እንደገና እመለከታዋለሁ….ወዘተ እያሉ ሲያምታቱን እንደነበር የምታወስ ነው። ያንን ያላነበባችሁ ስለምትኖሩ ታሪክ ነውና እነሆ እንዲህ ይላል፦

የግንቦት 7 ድምጽ ቁጥር 25 ጥቅምት 27/2001 ዓ.ም ርዕሰ አንቀጽ

“ከትናንት በስቲያ ለባርነት ሲሸጡና ሲለወጡ የነበሩ ጥቁሮች ዛሬ ለአሜሪካ ፕረዚዳንት መመረጥ ከቻሉ በአገራችን ኢትዮጵያም ለአሰርት-መቶዎች አማታት እየተፈራረቁ ሱገዙን የነበሩትን የአማራና የትግሬ ሊሂቅ የኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎት እስከሆነ ድረስ ቦታው ለደቡብም፤ ለኦሮሞውም፤ ለአኝዋኩም ለመልቀቅ ፈቀደኛ የማይሆንበት ምክንያት የለም” (የግንቦት 7 ድምጽ ቁጥር 25 ጥቅምት 27/2001 ዓ.ም ርዕሰ አንቀጽ)

በማለት መጪው የመንግሥት ዘመን የሚገዙን የደቡብ እና ኦሮሞ ሊሂቃን መሆን እንዳለባቸው ነው እንግዲህ ስላለፈው ምሬቱ እያወሳ ለመጪው ገዢዎቻችን እነማን መሆን እንደሚገባቸው ሲገልጽ የነበረው።

እንግዲህ ብርሃኑ ነጋ እና አንዳርጋቸው ጽጌ በጋዜጦቻቸው እየነገሩን የነበሩት መጪው ምርጫ በኢትዮጵያዊነት እውቀት የተላበሰና ቅን እና ሰብአዊነት የታጠቀ ማንኛውንም ዜጋ እንዲመራን ከመወትወት ይልቅ አገዎችን ሶማሌዎችን አማራዎችን ትግሬዎችን… እና የመሳሰሉ ዜጎች አግልሎ ከደቡብ እና ኦሮሞ ሊሂቃን ማስተዳዳር እንዳለባቸው ነበር በርዕሰ አንቀጹ ሲቀሰቅስ የነበረው። የርዕሰ አንቀጹ ብልት ስንሰነጥቀው በውስጡ ብዙ ምስጢር እንዳለው ግልጽ ነው። የመልእክቱ ፍሬ ነገርም ግንቦት 7 ከጸረ አማራው ከዋለልኝ መኮንን የቀዳውአማራ እና ትግሬ እየተፈራራቁ ….” የሚለውን ፍሬ ነገርን ነው እንደገና ከብዙ አመት የዋለልኝ ሕልፈት በላ የዋለልኝን ክርክር ከመቃብር አወጥቶ ግንቦት 7 ነብስ ዘርቶለት በዛው ትርክት እንድንዳክር የጣረው። ይህ ደግሞ የዘር ፖለቲካ የተንተራሰ ቁልጭ ያለ ዘረኝነትን ለማስፋፋት መስበክ ነው።

ተራ ዜጋው ‘ከማንም ይምጣ ከማንም ጎሳ ሰላም ካስመጣልን የምንፈልገው ያንን ነው” ሲል የግንበት 7 ፖለቲከኞች ግን እነሱ ባመላከቱን ክልሎች የተወለዱ ሊሂቃንን በፈረቃ እንዲገዙን መቀስቀስ ጎሰኛነታቸውን ሳይደበቁ ያሳዩበትን ጋዜጣዊ ርዕሰ አንቀጽ ነው። ለዚህ ነበር ‘ያ የዚያ ጎሳ ሊሂቅ ገዝቶናል አሁን ደግሞ ተራችን ነው’ እየታባለ የኢትዮጵያውያን ትላልቅ ዋርካዎች/ፋና ወጊዎችን/ በስልት እና በግልጽ እየገደሉ ካገር እንዲወጡ እያደረጉ አገሪቷ ያለ ከዋክብት አስቀርተው በትናንሽ ሰዎች እየተመራች መከራዋን በማየት ላይ ያለቺው።

አሁንም የአናርኮ ፋሺስቱ ድርጅት (ኦሕዴድ) መሪ (አብይ) እንደ እነ ብርሃኑ ነጋ የመሳሰሉ ‘የሥልጣን ጉጉተኞችን’ አየሩን እንዲያቃዉሰት ወደ ጎኑ በማስጠጋት በጣም ጥቂት አሉ የተባሉ እንደ እነ እስክንድር ነጋ የመሳሰሉ ከዋክብቶችን በማጨለም “Wiping out remaining icons of Ethiopianity” የተሰኘ ሃዳዊ ዘመቻው ሲቀጥል እያየን ነው። ቀስ ብሎም በታወቁ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞች እንደ እነ ቴድሮስ ጸጋየ፤ርዕት ዓለሙ ወዘተ…. የማሳሰሉ ውጭ በቀል ሳይሆን ‘አውተንቲክ ኢትዮጵያዊነትን’ (ኦረጋኒክ ኢትዮጵያዊነት) የሚያራምዱትን የማጠልሸት ሙከራ እየተደረገ ነው።

እንዲህ ያለ ሴረኛ ስልት በወያኔ ዘመን ነበር። አለቅላቂዎችም እንዲሁ። ዛሬም በአብይ አሕመድ መሪነትም ጎልቶ እየታየ ያለው እነ ብርሃኑ ነጋን በማስጠጋት የግንቦት 7 ጋዜጠኞች እነ ሲሳይ አገናን፤ አበበ ገላው፤ መሳይ መኮንን እና ተማሩ የሚባሉ አስቂኝ አይነቶቹ ምሁራን እንደ እነ ጥበበ ሳሙኤል ፈረንጅ፤ በዕድሉ ዋቅጅራ… የመሳሰሉ ምሁራኖችን ደጋፊ በማግኘት አብይን የሚተቹ ተቺዎች ላይ ‘እንደ ተርብ በመረባረብ’ አብይም ተቺዎቹን ሊዝት እና ሊወነጅላቸው ዕድል ተከፍቶለታል (ለእስክንድር የዛተበትም ለዚህ ነው)። ብርሀኑም ከባሕሪው የተነሳ ለዚህ ሴራ ተመራጭ ያደርገዋል። አስገራሚው የብርሃኑ ነጋ የስልጣን ጉጉተኛነቱ የአብይ አሕመድ ድጋፍ ለማግኘት ሲል አብይ አሕመድ “እስክንድር ነጋ የመሰለ ጀግና ጋዜጠኛ እና አዲስ አበቤ ተከታዮቹን” እንዲያ ሲንገላቱ እና በአብይ አሕመድ ሲዘለፍ (ጀግና እንዲባሉ መታሰርን የሚናፍቁ ብሎ ያለውን ልብ በሉ!) እና ሲወነጀሉ (ይህን የ አብይን ውንጀላ አትርሱ- “….በአዲስ አባባ በሚመለከት ጉዳይ ላይ እውነቱን ለመናገር እኔ ያልተመቸኝ “መፈንቅለ መንግሥት የሚመስል ጉዳይ ስለሆነ ነው” (አብይ አሕመድ)። በማለት በመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እስክንድርን  ወንጅሎ “ወደ ግልጽ ጦርነት እንደሚገባ” የዛተበትን ዛቻ እንዳይበቃ ብርሃኑ ነጋ ያችን ዕድል ተጠቅሞ ለአብይ አሕመድ ድጋፉን በእንዲህ ገልጾለታል፡-

ብርሃኑ ነጋ አዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ጸረ አማራ ከሆነው “አ ኤም ኤን” ከተባለው የተገንጣይ ኦሮሞ የፕሮፓጋንዳ ማሰራጪያ አውታር ላይ ቀርቦ ባደረገው ቃለ ምልልስ ስለ አብይ እና አዲስ አበባ (አስክንደር ነጋ ባለ አደራ) ጉዳይ ሲመልስ እንዲህ ይላል።

አኔ አብይን ሙሉ ለሙሉ አምነዋለሁ!!!” ካለ በሗላ፤ “ታከለ ኡማም ቢሆን (እንደ አብይ አሕመድ) አሸጋጋሪ ነው” “በሕግም ብምንም “የሌለ” ባላደራ “ምናምን” የሚባል ለኔ ብዙም እንትን አያደርገኝም……ታከለም ሆነ አብይ ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት አሻጋጋሪዎቻችን ናቸው”። ለዚህ ነው ወደ እዚያ ስለሚያሻግሩን እንርዳቸው አብረን እንሂድ የምለው።”  ካለ በላ ብርሃኑ ነጋ በመቀጠል

‘ጋዜጠኛው የለውጡ እንቅፋቶች ምንድናቸው ይላሉ?” ለሚለው ሲመልስ በሦስት ክፍሎች ከፍሎ ሦስተኛው በእንዲህ ያስቀምጣቸዋል፡

”ለወጡ በፍጥነት እየሄደ አይደለም፤ እኛ የምንፈልገው እያገኘን አይደለም ብለው በቁጭት ለውጡ ተሎ ወደ እሚፈለገው ነገር መግፋት አለበት፤ ካልሆነ ሽግሩ ወደ ሌላ ነገር ያመራል ብለው የሚፈሩ ብችኩልነት በተወሰነ ደረጃ ይህንን ለውጥ እንቅፋት የሆኑ ሃይሎች አሉ።” በማለት ብርሃኑ ነጋ በጃዋር ሜዲያ ቀርቦ የሰጠውን ቃለመጠይቁን ያገባድዳል።

የሚገርመው ደግሞ “ሶሻል ሚዲያ” ለጥርጣሬው ተጨማሪ ነዳጅ እየሆነ ነው በማለት ልክ እንደ አብይ አሕመድ ችግሩ የውስጥ (የስርዓቱ) ሳይሆን ‘ውጪኣዊ ነዳጅ’ የፈጠረው ጥርጣሬ በሽግግሩ አራማጆች ላይ እምነት እንዲታጣ ተደርጓል’ በማለት ብርሃኑ ነጋ በፌስ ቡክ ላይ ቅሬታውን አንጸባርቋል።  

ይህ ሙሉ ለሙሉ አምነዋለሁ የሚለው ደንቆራአዊ የእምነት አባባል በብርሃኑ ብቻ አልተወሰነም፡ ፀሐይ አሳታሚ የሚባለው የመጻሕፍት ሕትመት ባለቤት የሆነው ኤልያስ ወንድሙም ስለ አብይ አስተዳዳር ከ ቪ ኦ ኤው -straight talk Africa የውይይት ክ/ጊዜ ዋና አዘጋጅ ከሆነው ሻካ May 1/2019 እንዲህ ሲል ኤልያስን ይጠይቀዋል “How do you grade the Prime Minster?” መልስ (ኤልያስ) (If you ask me the report card for one year, I will put A+ (A plus)” በማለት ከሚገባው በላይ የስራ አፈጻጸም ውጤት ሰጥቶታል። ኤ ብቻ ሳይሆን ከ ኤ በላይም ሰጥቸዋለሁ’ ሲል ሻካ እራሱ “እርግጠኛ ነህ እስከዚህ ድረስ የሚደርስ ነጥብ “ሪሊ?” በማለት አግራሞቱን ገልጿል (በነገራችን ላይ አብራ ለውይይት የተጋበዘቺው የግንቦት 7ትዋ ‘ሊሊት’ (በስም ሞክሼነት እንዳይሆን እርስዋ ትሁን አትሁን አላወቅኩም) “ምንም ግሬድ አልሰጠውም! “መቆጠብን መርጫለሁ!” በማለት አስተዋይ ድምዳሜዋን መልስ ሰጥታለች። መጀመሪያ አብይን በመደገፍ ደስታውን አላስችል ብሎት ሰማይ ሲጨብጥ የነበረው የኒውዮርኩ “ተድላ አስፋው” አድ ስለነበረ ጣቢያውን ደውሎ “አብይን “ሲ/C/” አልሰጠውም’ በማለት አብይን ክፉኛ ተቃውሞታል። 

እንግዲህ እነ ብርሃኑ ነጋ ሙሉ በሙሉ እናምነዋለን “ኤ ፕላስ” ሰጥተነዋል እያሉ  የአብይ ‘የወደቀ/የሰነፈ’ የስራ አፈጻጸም ስንመረምረው፤ አውነታው ተቃራኒ ነው።

አንዴት ነው ነገሩ?!!! “የመንግስት መዋቅሮች ለኦሮሞዎች” እየተሰጠ ፤ ’ሰላማዊ ጥያቄ ያቀረቡለትን ዜጎች “እያገደ እና እያስፈራራ”፤ በሚሊዮኖች የተፈናቀሉ ዜጎችን፤ ከ18 በላይ የባንክ ዘረፋዎችን “ዝም በሉዋቸው/ታገስዋቸው/ የፈለጉት ድርጉ የሚል ለወንጀል ድርጊት የሚታገስ መሪ፤  እህቶች፤ እናቶች፤ አረጋውያን እና መነኮሳት በጋጠወጥ ተገንጣዮች ሲደፈሩ፤ቤቶቻቸው በቡልዶዘር ሲፈርስባቸው፤ ህጽናት ትምህርት ሲታገዱ፤ ቤተፀለቶች ሲቃጠሉ፤ ዜጎች በወረበሎች ታፍነው ሲጠፉ፤ መላው የሐረር ከተማ ሕዝብ  በውሃ ጥም እንዲረግፍ ቧምቧ የቆረጡ ብዛት ያለቸው የተደራጁ የከተማ ወንበዴዎችን መታገስን፤ የመዝናኛ ስፍራዎች (ሪዞልት) ማገድ እና  ባለቤቶችና ሰራተኞችን አፍኖ “ገንዘብ መጠየቅን” የመሳሰሉ ከፍተኛ ወንጀሎች ሲከናወኑ እንታገሳቸው (‘ወንጀለኞች’ ታፍነው ስለነበሩ ዛሬ ነፃነት ስለተሰማቸው ነው ይህንን የሚያደርጉ የሚለንን አብይ) በሚያስፈራ ፍጥነት ወንጀልን ያሳደገ አናርኪስት መሪ ብርሃኑ ነጋ “አብይ ሙሉ በሙሉ አምነዋለሁ” ሲለን  እነ ኤልያስ ወንድሙ ደግሞ  ኤ ፕላስ” ሰጥተነዋል፤ እያሉ አስቂኝ ምሁራዊ “የስራ አፈጻጸም ሪፖርት” በመስጠት “አዲሱ መሪያቸው” አብይ አሕመድ በሕግ አንዳይጠየቅ የወደፊት መሪ እንዲሆን በተዘዋዋሪ ቅስቀሳ ማድረግ የለመድነውን የምሁራን ውድቀት ዛሬም ከስሕተታቸው አልተማሩም።

ብርሃኑ ነጋ ስለ እስክንድር ነጋ የሚመራው የሲቪክ ማሕበረሰብን የሕዝብ ጥያቄ አይደለም፤ ሕጋዊ አይደለምብሎ ያጣጣለበትን ‘ጸያፍ’ እና አድርባይ ንግግሩ የኢሳት ጋዜጠኞች እነ ኤርሚያስ ለገሰ እና ሃብታሙ አያሌው በብርሃኑ ነጋ አድርባይነት ተገርመው” ዶ/ር ብርሃኑ ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው በማለት በይፋ ወርፈውታል።

ወደ ልደቱ ኢዴፓ እና ወደ ግንቦት 7ቱ ብርሃኑ ነጋ አዲስ ንትርክ ልውሰዳችሁ፡

የቅርቡ የልደቱ እና የብርሃኑ ነጋ ሁኔታ በሚመለከት ልደቱ አያሌው እያቀረበ ያለው ቅሬታ ‘ብርሃኑ ነጋ’ በሊቀመንበርነት እየመራው ያለው አዲስ የተመሰረተው ፓርቲ “ኢዴፓ” ጋር ውህደት ፈጽሜ አለሁ ብሎ ሌሎች ፓርቲዎችም ያሉበት ውሕደት በመሰረቱ እቃወመዋለሁ፤ ሕጋዊነትም የለውም! ሲል ልደቱ ይከራከራል። ለዚህም ብርቱካን መዲቅሳ በምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ሃለፊነትዋ ተጠቅማ ውህደት ፈጽመናል ብለው በሚዲያ በዜና መልክ ሲያስነግሩ እርስዋም ሕጋዊ እንዳልሆነ እያወቀች መቃወም ሲኖርባት አዲስ ፓርቲ ለመመስረት እየተንቀሳቀሱ ስለሆነ በሄዱበት ቦታ ‘ድጋፍ ይደረግላቸው’ ብላ ፈርማ ደብዳቤ ሰጥታቸዋለች።
ልደቱ እንዲህ ይላል።

“የፈለጉት ኦደፓን ፓርቲ ለማክሰም ነው። በሕግ ከሆነ ይህ ሴራ አይሰራም፤ብሔራዊ ምክር ቤት ውሳኔ ባልሰጠበት ሁኔታ  ኢዴፓ ከሰመ/ተዋሃደ/ማለት አይቻልም። በዚህ መልክ በሄደበት ውህደት የሚባለው ውህደት ‘ሕግ ካለ’ አይችሉም፤ ሕግ ለከሌለ ግን ይቻላል። ኢዴፓ ላይ የተሰራ ይህ ደባ የሚቀጥል ከሆነ የ27 አመቱ ስርዓት አልተቀየረም ማለት ነው። ስርዓቱ መቀየሩ እርግጥ ከሆነ “ኢደፓ” ከማንኛውም የፖለቲካ ተቋም ኢትዮጵያ ውስጥ ገንቢ የሆነ ፖለቲካ እንዲተከል ዋጋ የከፈለ ነው። እንዲህ ያለ ደባ ሲፈጸም ማየት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ባህላችን ውስጡ ምን ያህል አለመቀየሩ የሚያሳይ ነው። እንዲህ ከሆነ አሁን እየተካሄደ ያለው አዲስ ለውጥ ውጤታማ አይሆንም። ተመልሶ ይደናቀፋል። በነገራችን ላይ በኢትዮጵያ ፓርቲ የአመራር ዘመን ዕደሜ የወሰነ ብቸኛ ኢዴፓ ነው። ለ4ኛ ጊዜ 4 መሪዎችን ለውጧል (በሕገ ደምባችን ደምጽ ብልጫ እየተሰጠ)። እኛ በወጣትነታችን የሥልጣን ፍላጎት አድሮብን አያውቅም፤ አቅማችን አውቀን “እነ ዶ/ር ሃይሉ አርአያ፤ ደ/ር አድማሱ ገበየሁ እንዳወም ‘ቱ ዘ ኤክስተንት” (ርቀን በመሄድ) ብርሃኑነ ነጋ ኢዴፓ ሊቀመንብር አንዲሆን እና ኢዴፓ  ውስጥ እንዲገባ ከማንኛወም በላይ ጥረት (ሎቢ ካደረጉት አንዱ እኔ ነኝ) አድርጌአለሁ! መጥቶ እንዲመራን በሚል።” ሲል ልደቱ በሰፊው ስሞታውን አሰሰምቷል።

ልደቱ በቃለ መጠይቁ እንዳብራራው ኢዴፓ ፈርሷል ብለው እነ ዶር ከበደ ጫኔ ከብርሃኑ ጋር የውህደት ስምምነት ማድረጋቸው ሕግ የጣሰ ነው የሚለው የልደቱ አባባል ትክክል ነው። ልደቱ ሦስት ነጥቦችን አቅርቧል። 1ኛ  ጠቅላላ ጉባኤ እንድናካሂድ ተወስኖ እያለ ዶ/ር ከበደ ጫኔ ጉባኤው አንዳይካሄድ ሲሰሩ ነበር።  2ኛ አስቸኳይ አዋጅ በታወጀበት ወቅት ወያኔ ጋር ድርጅታችንን ወክለው እሳቸው እና ሁለት ሰዎች ሆነው ከወያኔ ጋር ድረድር ሲያደርጉ፤ የድረድሩ ዘገባ “የዕለት-ተለት የተደረገው ድረድር” እያመጡ የተነጋገሩበትን ሃሳብ ወደ ፓርቲው እያመጡ ኣቋም እና ውይይት እንድንሰጥበት ሲያደርጉ የነበረውን በጎ ሃላፊነታቸውን በገዛ ፈቃዳቸው አቆሙት። በዚህ ሁኔታ ፓርቲው እና ድርድሩ ተነጣጠለ። ስለዚህ እንደማንኛውም ዜጋ ሲደረግ የነበረውን ድድር በሚዲያ መስማት ጀመርን። እኛም  ሁኔታው ስላሳሰበን የድርጅቱን ሕግ የጣሰ ስለነበር የወሰኑት ውሳኔ/ድድር በድርጅቱ መወሰን ሲገባው እራሳችሁ መወሰናችሁ ሕግ የጣሰ ነው ስንላቸው ሊቀበሉ አልፈለጉም። ስለሆነም ከሃላፊነታቸው እንዲወርዱ ተደረገ። የምርጫ ቦርዱም የድርጅቱ ብሔራዊ ምክር ቤት የሰጠው ምክንያት እና ውሳኔ አልቀበልም አለ (ወገንተኛ ሆኖ ከነሱ ጋር አበረ)።.....ብሔራዊ ምክር ቤቱ የሚሰጠውን ውሳኔ ነው የሚያስፈጽመው እንጂ ስራ አስፈጻሚው ብሔራዊ ምክር ቤቱ ያልወሰነውን ምክር ቤቱን ሳያሳውቅ በፈቀዱ ሊወስን አይችልም (በመተዳደሪያ ደምቡ የተቀመጠ ነው)። ከዚያ ከኢዴፓ/ብሔራዊ ምክርቤት የሚቀርብ ማንኛውም አቤቱታ አንቀበልም ተብሎ “በር ተዘጋብን”። ምርጫ አስፈጻሚውም ብሔራዊ ምክርቤት እያለ “እነ ዶ/ር ከበደ ጫኔ ማለትም 4 ሰዎች እንደ ፓርቲ አውቅና ሰጥቶ ‘ምክር ቤቱን’ አላወቅህም አለው። 

ስለዚህ ስብሰባም መግለጫም እንዳንሰጥ ታገድን ማለት ነው። ምርጫ ቤቱም እውቅና ለነሱ ሰጠ። ስራ አስፈጻሚውም ከድርጅቱ ውጭ መሆናቸውን እና ሕገ ደምቡን በመጣሳቸው ሃሳባቸው እንዲቀይሩ ብናወያያቸውም ‘አሻፈረን” አሉ። ስለዚህ ስራ አስፈጻሚው ውሳኔ አሳለፈባቸው። እነሱም ወደ ፍርድ ቤት ሄደው ያለ አግባባብ የማሕበሩ ጸሐፊ ማሕተሙን ለእነ ዶ/ር ጫኔ እንዲያስረክብ ትዕዛዝ ተላለፈ። ይሕ ውሳኔ ደግሞ “የወገንተኛው የብሔራዊ ምርጫ ምክር ቤት ውሳኔ በመመርኮስ ነው”። ድርጅቱ ባንክ ቤት ውስጥ አስቀምጦት የነበረው ወደ 400መቶ ሺሕ ብር በሦስት ሰዎች ፌርማ ተፈርሞ መውጣት እና መንቀሳቀስ የሚገባውን የድርጅቱ ገንዘብ ምርጫ ቤቱ በስልጣኑ በደብዳቤ ለባንኩ በመጻፍ ለነ ዶ/ር ከበደ ጫኔ እጅ ተፈርሞ አካውንቱ እንዲተላለፍ ትዕዛዝ አስተላለፈ። ይህ ደግሞ የድርጅቱ ሕገ ደምብ ጥሶ በማያገባው ገብቶ ምርጫ ቦርዱ የድርጅቱን አካውነት ለነሱ አስተላለፈ። ፍረድ ቤቱም የመተዳደሪያ ደምባችንን ሳይፈትሽ የምርጫ ቦርድ የወሰነውን ወገንተኛ ውሳኔ ተቀብሎ ለግለሰቦች ውሳኔ ሰጠ (2010 ዓ.ም)

ከዚያም ይላል ልደቱ፤-

“የተቃውሞ መግለጫ አወጣን። ተቃውሞአችን የሚለው “ምርጫ ቦርዱ ከሕግ ውጭ ጣልቃ በመግባት ያለ አግባብ ፓርቲያችንን አፍርሶታል” የሚል ነው። (ሓምሌ 2010)። ስለዚህ ኢዴፓን የሚወክለው ብሔራዊ ምክር ቤት እንጂ 4 ሰዎች አይደሉም። ምክር ኢቤቱ 25 ሰዎች አሉት። ከሃያ አምስቱ ውስጥ 15ቱ ስራ ላይ ነን ያለነው። ምልኣተ ጉባኤው 13 ሰው ነው። ቀሪዎቹ 5 ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ውጭ አገር በመሄዳቸው በፓርቲው ጋራ አይደሉም ያሉት። ሌሎቹ 4 ሰዎች ግን አሁን ከነ ዶ/ር ጫኔ ያሉ ሰዎች ናቸው። ስለዚህ 4 ሰው እና 15 ሰው እንዴት አድርጎ ነው የድርጅት ውክልና ሊኖራቸው የሚችለው?” ሲል ልደቱ ይጠይቃል። የኢዴፓ ውክልና ሕጋዊ ሊኖሮው የሚችለው ምልኣተ ጉባኤ ሲከናወን ብቻ ነው። ያ ደግሞ ይኼው ወረቀቱ ላይ ተፈርሞ እንደምታዩት 15 ሰው ነው። ለዚህ ኢሕአዴግ በነዚህ ሰዎች በኩል ውዝግብ እንዲፈጠር ሕጋዊ ልሆነ ጣልቃ በመግባት ኢዴፓን እንዲፈርስ አድርጓል። ምርጫ ቦርዱ ደግሞ “ድርጅታዊ ተልዕኮ” ስለነበረው በግልጽ አፍርሶናል።

ለውጡ ከመጣ በላም ይህንን አንስተን ከዶር አብይ ጋር ተነጋገርን፡ የተፈጸመብንን ግፍ ማመልከቻ አቀረብን።  ጠ/ሚኒሰቴሩ ይህንን ጉዳይ አላቀውም ፤ይህ ጉዳይ አሁን መግለጫ ስትሰጡ ነው ያወቅኩት ብለውናል።ሁለተኛ ጊዜ ደግሞ ማመልከቻውም አልደረሰኝም አሉን። ማመለክቻውን ቀን እና የተሰጠበትን ማስረጃ አሳየናቸው። እሳቸውም ተመለከቱት እና ‘እሺ’ አንግዳውስ (እዛ ቁጭ ብየ እንዳለሁ) ለምርጫ ቦርዱ ስልክ ደውለው “ጉዳዩ ይጣራላቸው” ብለው ስልክ ደወሉለት። ለ5 እና 4 ወር በራቸወን ዘግተው ‘አናነጋግርም’ ብለውን የነበሩን የምርጫ ቦርድዋ ሰብሳቢው እሳቸው ስልክ ከደወሉላቸው በላ ‘በስልክ እንድናናጋግራቸው ጠሩን” (ሴትዮዋ ብርቱካን ከመሾምዋ በፊት የነበሩት ሰብሳቢ ናቸው)። እኛም ሄደን አነጋገርናቸው። ያለፍንበትን ሂደት አነጋገርናቸው፤ እሳቸውም ደነገጡ። ከዚያ በላ የማጣራት ሂደት እንዲጀመር እና እንደገና እንዲጣራ ተባለ። የማጣራቱን ሂደት ከማለቁ በፊት ሴትየዋ ከስልጣን ተነስተው በምትካቸው ወ/ት ብርቱካን ተሹመው መጡ።

አሁንም ከወ/ት ብርቱካን ጋር ተገናኝተን ተወያየን። የማጣራቱን ሂደት ተጠናቀቀ። ማጣራቱ ተጠናቅቋል፤ ወሰኔ ለመስጠት “ብሔራዊ ምርጫ መቋቋም አለበት” አሉን ወ/ት ብርቱካን። “እሺ ብለን” የሰጡትን ውሳኔ ተቀበልን። በነገራችን ላይ ስናስረዳቸው በመግባባት ነበር። እሳቸውም የቤት ስራቸውን ሰርተው አጣርተው ነው የጠበቁን። እንዳውም ከነ ደ/ር ጫኔ ጋር ቁጭ ብላችሁ እንድትወያዩ ብለው ሲያነጋግሩን እነ ዶ/ር ከበደ ጫኔ አንወያይም ብለው ነው ጥለው የሄዱት። ችግሩን ለመፍታት የተከረበትን መፍተሄ አንቀበልም ብለው ጥለውት ሄዱ።

ከዚያ በላ ምርጫ ቦርዱ ተቋቁሞ ውሰኔው ምንም ይሁን ምን ለመቀበል ተዘጋጅተን ምርጫ ቦርዱ እስኪቋቋም ድረስ እየተጠባበቅን ባለንበት ሰዓት ነው እነ ዶ/ር ጫኔ ኢዴፓ ከሌሎች ፓርቲ ውህደት ፈጽመናል በማለት መግለጫ ሰጡ። ይህ ደግሞ ሕገ ወጥ ነው አይቻልም። ሁለተኛ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ግንኙነት የማድረግ ፤ውህደት የመፍጠር ውሳኔ መስጠት የሚችለው ብሔራዊ ምክር ቤት ነው። አንቀጽ 9 13 ነጥብ 4 ላይ ይህንን በሚመለከት ከማንኛወም ፓርቲ የሚደረግ ግንኙነትም ሆነ ውህደት የሚወሰነው ኢዴፓ በብሔራዊ ምክር ቤት ነው ይላል። ብሔራዊ ምክር ቤቱ ከወሰነ በላ ውሳኔው ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ ያጸድቃል ይላል (2006 ዓ፣ም ተሻሽሎ በወጣው ደምባችን ውስጥ)። በዚህ መሰረት አይደለም ብሔራዊ ምክር ቤት መሰብሰብ  ጠቅላላ ጉባኤም አልተሰበሰበም አልወሰነበትም። ሊሰበሰብም ሊወስንም አይችልም፡ ምክንያቱም “ምርጫ ቦርድ እገዳ ጥሎበታል”።  መሰብሰብ ይቻል እንኳ ቢኖር አብዛኛው አባል (ማጆሪቲው) እኛ ጋር ስለሆነ ውሳኔ መስጠት ካለበት  እኛ ጋር ያለው አብዛኛው አባል ነው። የተወሰኑ ሰዎች ከመሰላቸው ፓርቲ ጋር ሄደው በኢደፓ ስም ውህደት ፈጽመናል ሊሉ አይችሉም። 

 ሚዲያዎች ሃላፊነት አላችሁ። ምርጫ ቦርድ እስኪቋቋም ጠብቁ ተብለን ውሳኔ እየተጠባበቅን እንዳለ ውህደት መፈጸም ሕገ ወጥ ነው። እናንተ ሚደያዎች ፓርቲዎች እንደተዋሃዱ አድርጋችሁ ዜና መሰራጨታችሁ ስሕተት ነው።

ሌላው የሚገርመው ነገር ደግሞ “እነዚህ ውህደት ፈጽመናል ብለው እያወሩት ያሉት የውህደት እንቅስቃሴ አይደለም። ምከንያቱም ለምርጫ ቦርድ ማመልከቻ ጽፈው “አዲስ አገር አቀፍ ፓርቲ ልናቋቁም ስለሆነ ፌርማ እንድናሰባስብ የትብብር ደብዳቤ ይሰጠን ብለው ማማለክቻ አቅርበዋል።” ምርጫ ቦርድ ደግሞ “ያንን ደብዳቤአቸው መሰረት አድርጎ እነ ፕሮፌሰር ብርሃኑ አዲስ አገር አቀፍ ፓርቲ ሊያቋቁሙ ስለሆነ በየክልሉ ፌርማ ለማሰባሰብ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ትብብር ይደረግላቸው’ ተብሎ በወ’ት ብርቱካን ፌርማ የድጋፍ ደብዳቤ ሰጥቷቸዋል። ያ ሂደት ውህደት ሳይሆን አዲስ ፓርቲ የማቋቋም ሂደት ነው። 

.....ውህደት ልታደርግ ከሆነ ሕጋዊ መሰረት ኖሮህ “ፌርማ ማሰባሰብ” አያስፈልግም። እንዴት ውህደት መፍጠር ንዳለብህ፤ እንዴት ግምባር መፍጠር እንዳለብህ ሕግ አለ። ለምሳሌ ግንቦት 7 ብትወስድ ሕጋዊ እውቅና ስለሌለው የሌለውን አውቅና ተጠቅሞ “ውህደት” ሊፈጽም አይችልም። መጀመሪያ ፓርቲ መሆን አለበት፡አሁምመ ፓርቲ አይደለም! ከሌሎችጋር ሆኖ አዲስ ፓርቲ ለመመስረት ስራ እየሰራ ነው። ስለዚህ ውህደት ሳይሆን አዲስ ፓርቲ ማቋቋም ነው መባል የነበረበት። ስለዚህ ኢዴፓ ከስሞ ሌላ ፓርቲ መስረተናል ብለዋል። እኛ አልከሰምንም የራሱ የድርጅቱ መተዳዳሪያ አንቀጽ አለ ፤  እሱ አልተፈጸመም። ሴራው እኮ ትልቅ “ፕላንደር ነው”! የምርጫ ቦርድ ያለ ሥልጣኑ እጁን በማስገባት የባንክ አካውንት ገንዘብ ለ4 ሰዎች እንዲሰጥ ማድረጉ እጅግ “ወንጀል” ነው። እኛ እንደ ዜጎች መደራጀታችንን ተነፍገን መሰብሰብ መወሰን አልቻልንም። ባጠቃላይ ኢሕዴግ የወሰደው እርምጃም ሆነ ግንቦት 7ም የወሰደው ያለው እርምጃ ቅንነት የጎደለው ነው። ቅን አይደለም።

ከፖለቲካ እና ከድርድር ተገፍተን ከፖለቲካ ውጭ እንድንሆነ ተደርገናል። እነ ብርሃኑ ነጋ ሆን ብለው “ኢደፓን” በዚህ ስልት አክስመው ለማለፍ ስለሚፈልጉ ልክ የፓርቲዎች ውህደት ንደተፈጸመ አድርገው ቅስቀሳ እያደረጉ ነው። እናንተም ይህንን ተቀብላችሁ ነው እያስተጋባችሁ ያላችሁት። የሴራ ፖለቲካ ምርጫ 97 አክስሮናል፤ ዛሬም ከዚያ አልተላቀቅንም። አልተማርንም።  )” ይላል ልደቱ አያሌው። (ናሁ ቲ/ቪ ከሰጠው ቃለ መጠይቅ በከፊል ያገኘሁት

ለዚህ ነው ብርቱካን መዲቅሳ የብርሃኑን ባህሪ እያወቀች፤ የኢዴፓ ጉዳይ እንጥልጥል ላይ ያለ መሆኑን እና “የምርጫ ቦርድ እስኪመሰረት ቆዩ ብላ” ለሁለቱ የኢዴፓ ተከራካሪ ወገኖች ውሳኔ በመስጠት ያስተላለፈቺውን ውሳኔ እያለ ‘እንደገና’ ንደ አዲስ ለነ ደ/ር ከበደ ጫኔ፤ብርሃኑ ነጋ፤አንዷለም አራጌ… የሰጠችበትን የድጋፍ ደብዳቤ እንዳለ እያወቀች “ውህደት” ፈጽመናል ብለው በይፋ በሚዲያ መግለጫ ሲሰጥ የምርጫ በርዱ “ጆሮ ዳባ” ብሎ ማለፉን የሚያሳይ እውነትም ልደቱ እንዳለው “በልደቱ እና በጓዶቹ የሚመራው ኢዴፓ” በመጪው የፖለቲካ ሜዳ እንዳይገባ የተደረገ ሴራ ነው ተብሎ መውሰድ ይቻላል። ልደቱ ለአብይ ያለው ድጋፍ ምን እንደሆነ ባላውቅም እንደ እነ ብርሃኑ ነጋ እና አንዷለም አራጌ ሙሉጭ ያለ “ድጋፍ” ስላልሰጠው ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለኝ። ለዚህም ይሆናል ‘ምርጫ ቦርድ’ ተብየዋ ብርቱካን መልስ እንድትሰጥ ስትጠየቅ “አጣርተን እንነግራችለን” ብላ መስርያቤቷ ለናሁ ቲ/ቪ መስ እንዲሰጥ የተደረገው። ያም ሆነ ይህ የድሮ ፓለቲከኞች በበሰበሱበት ጎዳና ዛሬም ወደ አታካራ አስገብተውናል።

 ስለዚህ  ባጠቃላይ ልደቱ የሚለው፦ ምርጫ ቦርዱ የመተዳደሪያ ሕጋችንን በመተላለፍ  በፍርድቤት እና በቦርዱ ፖለቲካዊ ተልእኮ እነ ደ/ር ከበደ ጫኔ ጥለውት የሄዱትን ጽ/ቤት ቁልፉን እና የድርጅቱን ማሕተም እንዲረከቡ ተደርጎ እኛ አቤቱታችንን የሚሰማን አጣን። ወደ ፍርዴ ቤት ሄዶ ይግባኝ መጠየቅ አንችልም ፤ ምክንያቱም የምርጫ ቦርዱ ፖለቲካዊ ተልዕኮ ስለነበረው ከንቱ ዙረት ይሆንብናል ብለን ትተነው ነበር። ዛሬም ይኼው ውሳኔ ሳይሰጠን ጠብቁ እየተባልን ከፖለቲካው እንድንገለል ተደረጓል። ይላል ልደቱ አያሌው።
ይኼ በጣም አስገራሚ ነው። የበሰበሰ የፖለቲከኞች ባሕሪ ዛሬም አንደ አዲስ ብርሃኑ ነጋ እና መሰሎቹ አየሩን ለመበከል ዝግጁነታቸውን ማየት ችለናል። ብርሃኑ በኢደፓ ብቻ ሳይሆን በእስክንድርም በአማራውም የጎነጎነው ሴራ የሚያሳየን ብርሃኑ መለወጥ የማይችል መሆኑነ ነው።   

እስኪ ወደ ላ ልመልሳችሁ እና ላገባድድ።

 “ግንቦት ሰባትን ያቋቋሙትና የሚመሩት ብርሃኑ ነጋና እራሱ የመረጣቸው ከራሱ ነገድ የመጡ ጉራጌዎች፣ብሎም ሌላው የደቡብ ሰው ታደሰ ብሩና ኢዮኤል እንዲሁም እንደ ነዓምን ዘለቀ የኢትዮጵያን አንድነት በጎሪጥ የሚያዩ ሥብስቦች ናቸው።” ይላሉ ከበደ በለው የተባለ ጸሐፊ። እውነትም ናቸው ለማለት የሚያስችል ንግግራቸውን ስናስታውስ የሚገርም ነው። ለምሳሌ የግንቦት ሰባቱ ነዓምን ዘለቀ ”ኢትዮጵያ የምትባል አገር እና የኢትዮጵያ አንድነት ብቻ ሲባል “ስፎኬት” (suffocate) ያደርገኛል” ሲል ተደምጧል። የአትዮጵያ አንድነት ሲባል እስትናፋቻውን የሚያፍን፤ ለመስማት የሚቀፋቸውና አስጠሊታ እንደሆነባቸው ነው እንግዲህ የዚህ ድርጅት አመራሮች በግልጽ እንዲህ ያለ አስገራሚ የመድረክ ንግግሮች ሲያደርጉ የነበሩት።

ብርሃኑም አማራ ብሎ የሚጠራቸው ሟቹ ኢንጂኔር ሃይሉ ሻውልም እንዲህ ሲል ሲተቻቻው ነብር “መለስ የሚባል ትግሬ አስወግደን ሃይሉ የሚባል አማራ ለማስመጣት ነው ትግላችን?” በማለት የሰውየው የፖለቲካ ባሕሪ ከመተቸት ይልቅ በነገዳቸው በኩል በመግባት ነገዳቸውን ዋና መከራከሪያ ነጥብ አድርጎ ሲከራከር ነበር።        

ጋዜጠኛ እንዲህ ሲል ብርሃኑን ይጠይቃል፡- ስለ ‘የብሔር ፖለቲካ’ እንደ ግንቦት 7 ያላችሁ ፖሊሲ ምንድነው?

 ብርሃኑ
ንቅናቄ ስለሆንን ስለ ብሔር ፖለቲካን በሚመለከት ፖሊሲ የለንም። የወስድነው ወይንም የምንተቸው አቋም የለንም።” (ብርሃኑ ነጋ)

ስለ ኦነግ በሚመለከት የሰጠው አስተያየት እንዲህ ይላል፦

ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ አንድነት ጥያቄ አላቸው የሚባሉ ድርጅቶች እንደ ኦነግ የመሳሰሉ ድርጅቶች እንኳን አሁን ባለፉት ሁለት አማታት በተደረጉት ውይይቶች በኢትዮጵያ ውስጥ እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እስካለ ድረስ መገንጠልን “የሞት የሽረት” አላማ አድርገው እንደማይታገሉለት በግልጽ እያሰቀመጡበት ያለበት ጊዜ ላይ ነን ያለነው አሁን።እዚህ ስብሰባ ከመምጣቴ በፊት ኢመይሌን ስመለከት ያገኘሁት አንድ ኢመይል የኦነግ ሃይሎች እንደምታውቁት ለሁለት ተከፋፍለው ላለፉት ሁለት አመታት “ሞር ኦር ሌስ - ፓራላይዝ” ሆነው የቆዩበት “ኢንቫይሮንሜንት” ነበር። ይህን በሚመለከት የዕርቅ ድርድር ስያደርጉ ነበር፡ትናትና የህንን ዕርቅ ድርድር ጨርሰው ተስማምተዋል (ይህንነ ካለ በሗላ ከአዳራሹ ‘ደናቁርት ካልቶች’ የቀለጠ ጭብጨባ ይደመጣል)። ይኼ በጣም ስግኒፊካንት የሆነ “ዴቬሎፕሜንት” ነው።አንዱም በጋራ እንዳንታገል ችግር ሆኖ የነበረው በዚህ የኦነግ ክፍፍል ነው። ይህንን ክፍፍል ካቆመ ለኢትዮጵያ የሚደረገው የነፃነት ትግል አብረን እንደምንቆም ቅንጣት ያክል ጥርጥር የለኝም! (ጭብጫባ ይደመጣል)። ይልና በመቀጠልም-…

ይህ ደግሞ ሕዝቡ እርስበርሱ ይባላል ስንባል የነበርንበትን ስሕተት መሆኑን መመለስ የሚችል እርምጃ ነው። እኔ አስከገባኝና እስከማውቀው ድረስ እንደ ግንቦት 7ትነቴ በኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ያሉት መሰረታዊ ልዩነቶች “ከሞላ ጎደል” የተመለሱበት ደረጃ ላይ ነው (አየ ብርሃኑ!! ይህ ደግሞ ዛሬ ከምናየው ሃቅ የሚጣረስ ውሸት ነው!!!) -(ትንተናው የተጣሉ የተራራቁ ፤ያልተስማሙ ገንጣዮች/ኦነጎች/ አንድ መሆናቸው ላገራችን አንድነት መድህን ነው ከሚለው ቀጣፊ እምነቱ ተነስቶ ነው እንዲህ እየተቸ ያለው። ተባብረው የሚሰጡት መግለጫና ቻርተር ምን ንደሆነ የምታውቁት ነው::)

ብርሃኑ በመቀጠል፤-ወያኔ ከጣልን በላ፡ሚለውን ንግግሩም እንዲህ ይላል፡

“ወያኔን ለመጣል ብቻ ሳይሆን ወያኔ ከጣልን በላ ለምንመሰርተው “አንድነት” የኢትዮጵያን አንድነት ሊያስጠብቅ እንሚችል ከሞላ ጎደል ማረጋጋጥ የሚቻልበት ደረጃ መድረሳችንን ማረጋገጥ ይቻላል። ይህ “ ዚስ ኢዝ ‘ቬሪ ኢምፖርታንት’ ዴቬሎፕመንት ነው”። ይኼ ደግሞ ዝምብሎ የመጣ አይደለም፡ ለሁት አመት ለሦሰት አመት ብዙ ልፋት እና እንቅስቃሴ የተደረገበት ነው። ወደ ውጤቱ ለመድረስ ብዙ ሰዓታትና ክርክሮች ተካሂደውበታል። 
 
 (የኦነግ ኦሮሞዎች ልዩነታቸውን አቻችለው “አንድ ሆነዋል” እያለ እንደ ‘ብስራት/አስደሳች/ ዜና” ቆጥሮት ወደ ኢትዮጵያዊነት ተመልሰዋል እያለ ነው ብርሃኑ። አሁን ያለው ደግሞ “አረጋግጠናል ሲለን የነበረው ማረጋገጫ ኦነጎች አንድ ሆነው ‘ምን እያደረጉ” እንደሆነ እነ በቀለ ገርባ እነ ሌንጮ፤ እነ ጃዋር ምን እየሰሩ እንደሆነ የምታዩት ሃቅ ነው። ብርሃኑ እንዴት እንደሚዋሽና አድማጩን ለማስጨብጭብ ብልጠቱን ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ ማረጋጋጫ ነው)።

እንደምታውቁት ይላል ብርሃኑ፤

 እንደምታውቁት ማሕበረሰባችን የነፃነት ችግር ሳይሆን “የመተማመን ችግር ነው ያለው”። ወያኔ ከወደቀ ምንም ነገር አይመጣም! እመኑኝ ነኝ የምላችሁ ምንም ነገር እየመጣም! የሚጣ መጥፎ ክስተት ቢኖር “እሱ/ወያኔ/ ላለመውደቅ የሚያደርገው ጉዳት ብቻ ነው። ኢትዮጵያ ካሁን በላ ትገነጣጠላለች የሚለው ራቢሽ ካሁን በላ አይኖርም። ሁሉም በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ነው ወደ ሥልጣን የሚወጣው። “ያ በማጭበርበር ሥልጣን መያዝ አክትሟል። “ዘመዶቼ የተበላ ዕቁብ የሚሉት ዓይነት ነው።  ዊዝ ኮንፊደንስ ነው የምነግራችሁ!  ብርሃኑ ኦነጎች ወደ ኢትዮጵያዊነት ወደ አንድነት ትግሉ ተቀላቅለዋል እያለ ነው “ኮነፊደንስ” የሚለው ቃል ሲጠቀምበት የነበረው።

እንዲያ እያለ ነበር ብርሃኑ ተከታዮቹን ሲያጃጅል እና በስሜት ስካር በየአዳራሹ እየሰበከ “የመተማመን ችግር ከሞላ ገደል ተቀርፏል ሲል የነበረው”። ኦነጎችን እንመናቸው ወያኔ ከወደቀ ምንም ነገር አያመጡም! እመኑኝ ነኝ የምላችሁ; ምንም ነገር እይመጣም! የሚመጣ መጥፎ ክስተት ቢኖር “እሱ/ወያኔ/ ላለመውደቅ የሚያደርገው መፍጨርጨር ብቻ ነው። እያለ ሲያጃጅለን ከርሞ ዛሬ ኦነግ ምንም ነገር አያመጣም ሲል የነበረው የብርሃኑ ነጋ ውሸት ተጋልጦ “እኛ እንደተነበይነው” ባስገራሚ ክስተት “ኦነጎች ከአስመራ ወደ አዲስ አበባ ከገቡ በላ አገር ውስጥ ከነበሩት ከሌሎች ‘ኦሮሞ ድርጅቶች’ ጋር ግምባር ፈጥረው የመጀመሪያ ጦርነት የከፈቱት ከግንቦት 7 ደጋፊዎች እና የግንቦት 7 ሚዲያ ከሆነው ኢሳት ቴ/ቪ ላይ ነበር”።  የሚገርም ነው! አይደለም እንዴ?
  •  በመጨረሻ ኦነጎችን እና የማሳሰሉትን ድጋፍ ሰጥቶ አንድነት ሃይሉን  ሲያንኳስስ ኢሳት የግንቦት 7 ድርጅት ስለነበረ” የብርሃኑን ትዕዛዝ ለመፈጸም  የኦነጎችን ባንዴራ ኢሳት ቴ/ቪዥን ውስጥ እየተውለበለበ ‘የኦነግ ወታደሮች’ እንዴት ወደ ድል ተራራ እንደወጡ ኢሳት ሲሰብክበት የነበረውን ጉደኛ ታሪኩን ለማንበብ ይህንን የዶ/ር ማንከልክሎት ሃይለስላሴን ሰነድ የጻፉትን አንብቡ “ 
  • (A deliberate and outright deception--part I Part II Part III by Dr.Mankelkilot Haileselassie )
ይህ ከታች ያለውን የብርሃኑ ንግግር ላስምርበት እና  በዚህ ልደምድም፡

“አንድ ሰው ባንድ ስብሰባ ሲናገር የሰማሁት ነገር አለ፤ ‘የኢትዮጵያ አንድነት ካልተቀበሉ በቀር ይላሃል!!! እንዴ!? እኔ የምለው መጀመሪያ ኢትዮጵያውያን ናቸው፡ የመቀበል አለመቀበል ብሎ ነገር ምንድነው? የምንሰጣቸው እና የምንቀማቸው አይደለም “ዜይ ኣር ዋት ዘይ ኣር?” በደል ደርሶብናል ስላሉ “የሁላችን ስራ ነው”። እንዲህ ያለ ወሬ ከማናፈስ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን….” በማለት ለግንጣላ ተነስተው እኛ ኢትዮጵያውያን አይደለንም፤ ኢትዮጵያዊነት በላያችን ላይ የተጫነብን እንጂ እኛ “ኦሮሚያ’ ነን እያሉ በግሃድ እና በጽሑፍ በፕሮግራም ቀርጸው “ኢትዮጵያዉያን አይደለንም አገር እናፈርሳለን” እያሉ እየተከራከሩ እየታወቀ ‘ብርሃኑ ነጋ’ እነሱን በመከላከል አገር ወዳዶችን “ወሬኞች” እያለ ጥንቃቄ አድርጉ እያለ ኢትዮጵያውያኖችን ያስጠነቅቃል። 

ዛሬ  አብይ ኦነግን በአንቀልባ አዝሎ “በእሽሩሩ ኦነግ” መዘሙር እየተጓዘ፤ ዜጎች ከአዲስ አባባ ውጡ! አዲስ (ፍንፍኔ) የኦሮሞዎች ናት! እያሉ ባንክ ዘረፋ ገብተዋል። የብርሃኑ ነጋ ኦነግን አትጠራጠሩ ፕሮፓጋንዳ እና “እመኑኝ! እመኑኝ!” ዛሬ እውነታውን “ኮንፊዴንሱን” አየነው። ብርሃኑ ዛሬ በልደቱ አያሌው እና በእስክንድር ነጋ የሚያሴረው ሴራ የሚነግረን ነገር ካለ ብርሃኑ ለሥልጣን ሲጓጓ የነበረው የብዙ አማታት ጉጉቱ እውን ለማድረግ እየሮጠበት ያለውን ፖለቲካዊ ውስልትናው ተጠቅሞ ወደ ቄሳዊ የሰበካ ባሕሪ የተለወጠው “ጀግናው አንዱአለም አራጌን’ ምርኩዝ በማድረግ ወደ ሥልጣን የሚወጣበትን መወጣጫ መሰላሉ እያበጃጀ ግርግሩን እየተጠቀመበት መሆኑን ነው።
አመሰግናለሁ! ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ አዘጋጅ)