Saturday, November 29, 2008

የኢሳያስ አፈወረቅ የባሕር ላይ ዉንብድና ተግባር

ግንኙነቱ እየጠነከረ የአካባቢዉ ሁኔታ እየተለወጠ ሲሄድ በSeptember 2008 የአዉሮጳ ሕብርት የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮች ስብሰባም በአፍሪቃ ቀንድ እየታየ ያለዉ አሳሳቢ ክስተት ካገናዘበ በሗላ ወታደራዊ ክንዋኔዎችን ለማካሄድ የሚያስችለዉን ዕቅድ አጸደቀ። ቀጥሎም በተመሳሳይ መንገድ የአሜሪካ መንግሥት የአፍሪካ ቀንድ አድሚራል ፊሊፕ ግሪን ከየመን ጋር የባሕር ላይ ዉንብድና ለመግታት አሕጉራዊ የመተላለፊያ የቀ ይ ባሕር ቀጠናዎች ጸጥታን ለመቆጣጠር እንዲያመች ወታደራዊ የጋራ ትብብርን በሚመለከት ዉይይት ተደረገ።
ይህ በሚሆንበት ጊዜ አሜሪካ አንዲት መርከብ የተጠለፈች መሆኗን ካሳወቀች በሗላ፤ ወደ ኤርትራ የዉሃ መስመር በመቅዘፍ ተሰወረችዉ ነብረትነትዋ የኢራን የሆነች መርከብ ለመከታተል ወደ ኤርትራ የዉሃ መስመር የመግቢያ ፈቃድ ለማግኘት መርከቧን ለጠለፏት ሽፍቶች $7 ሚኒሊዮን ዶላር እንደከፈለ የተለያዩ ጋዜጦች አስተጋቡ ። አሜሪካ $7ሚሊዮን ዶላር ትክፈል እንጂ በተዘዋዋሪ መንገድ ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ጀምሮ የአካባቢዉ ጸጥታ በብቸኝነትና በበላይነት ለመቆጣጠር የነበራትን ጥም በደረግ ጊዜ አጥታዉ የነበረዉን ዕድል ከሰሜን አትላንቲክ ኔቶ ጋር ሃይሏን በማዋሃድ ወደ ቀይ ባሕር ቀጠና በማዝገም፡”የጥቁር ዳማና ጠረጋ ዘመቻ” ለማድረግ የተጠናከረ እንቅስቃሴ ለማድረግ ዕድሉን አገኘች። ሩሲያም በበኩሏ ከሴፕተምበር 2008 መጨረሻ ገደማ ጀምሮ በሶማሊያ የባሕር ደንደሶች ተዋጊ መርከቦቿን ለማንቀሳቀስ ዝግጁ እንደሆነች’ና ሲያስፈልግም ተዋጊ መረከቦቿም ስራ ላይ እንደሚዉሉ በተጓዳኝ አስታወቀች። ይበልጥ መስህቡ እየጎላ ሲሄድ M.V.Faina የተባለች መረከብ ከጠለፈች በሗላ የት እንደምታርፍ በቅጡ ያልታወቀ ታንክ እና ወታደራዊ ዕቃዎችን ጭና ስትጓዝ የነበረችዉ ንብረትነትዋ ይኩረይን የሆነች በሗላ ላይ በSeptember 28/2007 በኤርትራ ማርሳዎች(ወደቦች) በብርጋዴር ጄኔራል ፍጹም ገብርሕይወት ተረካቢነት የጫነቺዉ መሳሪያ ማራገፏን ከተደረሰበት በሗላ የአትላንቲክ ኔቶ ጦር ወደ ቀይ ባሕር ቀጠና የዉግያ መርከቦችን በመላክ አሰመርቶ ነበር። በወቅቱ የባሕር ሃይሉ አዛዥ የነበረዉ ብርጋዴር ጀኔራል ፍጹም ገ/ሕይወት ነዉ። ከጊዜ በሗላ የኤርትራ የባሕር ሐይል አዛዣነት ስልጣኑን ለመጄር ጄኔራል ሑመድ ካሪካሪ በሕዳር November 18/2007 እንዲለቅ ተደርጓል ። ለስልጣኑ ቅሚያ ምክንያትም ኢሳያስ አፈወረቂ የኒኩሌር አተላ ወደ የኤርትራ የቀይ ባሕር ዉሃዎች እንዲጣል የመፍቀዱን ጉዳይ በመቃወሙ ነዉ። ዛሬ እጅግ አሳሳቢ እየሆነ የመጣዉ የባሕር ጠለፋ ዉምበድና እየበረታ መሄዱና ቢያንስ አስከ 61ጊዜ የመርከብ ጠለፋ ሲካሄድ መርከቦቹን ለማስለቀቅ የተከፈለዉ ገንዘብ ወደ 300 ሚሊዮን ዶላር እንደሚጠጋ ይነገራል። የፕረዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ አስተዳደርም በመርከቦች ጠላፋ እና ከኑክሊየር አተላ መጣያ በሚገኝ ገንዘብ ተግባር ላይ ተጠምዷል። Sirius Star ሳይረስ ስታር ተባለችዉ መርከብ 2ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ጭና ካሳዉዲ ዓረብያ ስትጓዝ ከመጠለፏ በፊት November 14/2008 ወደ 15 አጥቢያ ክዉ ብሎ ጸጥ ባለዉ ሌሊት በ5ፈጣን ጀልባዎች ተሳፍረዉ በጀኔራል ፍጹም ገ/ሕይወት ሸኚነት-ኮሎኔል መሓሪ ደስታ፤ ካፒቴን ያሲን ፈረጅ ካፒቴን ሓሰን ፍካክ የሚመሩት 46 ዘመናዊ ትጥቅ የታጠቁ የኤርትራ የባሕር ሃይል አባላች አቅጣጫቸዉን ወደ ሕንድ ዉቅያኖስ አዙሮዉ በመቀዝፈ ተጓዙ ። ዕሁድ November 16/2008 በዛዉ ዕለት ንብረትነቷ የአሜሪካ የሆነች US bounder tanker ወደ ደቡባዊ ምስራቅ ሞምባሳ አካባቢ በምትጓዝበት ወቅትም ብርጋዴር ጄነራል ጠዓመ (መቐለ) ከሶማሊያዉ የእስላሞች ሕብረት ግምባር የሽምቅ አባል ኮማንደር አይዘን ሑሴን ከማል ከተባለ ቀደም ብሎ በኢራን የባሕር ሃይል አባል የነበረ በዜግነቱ ኩርድ የሆነ አብሮዉ ከአስመራ ወደ ኬኒያ የጥድፉያ በረራ አድርገዉ ነብር። Syrus Star የተባለች ካሁን በፊት ከተጠለፉት መርከቦች እጀግ ግዙፍ የሆነች መርከብ በሶማሌ ጫፍ በፑትላንድ አካባቢ የመጠለፉ ዜና ሲሰማ፤ነገሩ በፍጥነት እየተባባሰ መሆኑና የነገሩም ዉስብስብነት ይበልጥ አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ ጠላፊዎቹን እና የዉስብሰቡን ሁኔታ አድኖ የማግኙትን ጉጉት ይበልጥኑ ከፍ ሲያደርገዉ፤”ከበስተጀርባዉ ያለዉ ጥቁር መጋረጃ” እንዲገለጥ በር የሚከፍት መሆኑን የአሜሪካ የማዕከላዊ የስለያ ድርጅት ያምንበታል። በዚህ ትኩረት ላይ የፕረዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ አስተዳደርም በመረከብ ጠለፋ እና ዝርፊያ እንዲሁም ቀይ ባሕርም የመርዘኛ ቆሻሻዎች መጣያ እንዲሆን በማድረግ በዛ የሥራ ትኩረት ተጠምዶ ይታያል። የመርከብ ጠለፋዉ ዉምብድና በጣም በመጧጧፉ በቅርቡ የኮሮሽያ ፤የፊሊፕኖ እና የፓልንድ መርከቦች የባሕር ጠለፋ ሰለለባ ሆነዋል። የጃፓን የቻይና ዘመናዊ አሳ አጥማጅ መርከብ እንደዚሁም ኬሚካል የጫነች የቱርክ መርከብ ስትጠለፍ የኤርትራ ባሕር ሃይል ወዲያ ወዲህ ሲወራጭ ነበር። በወቅቱ ተከታታይ የጠለፋ ክስተት ከታየ በሗላ የአሜሪካ መንግሥት በህዳር (November 2008) ዜጎቿ ብቻ ሳይሆን የአዉሮፓ ዜጎችም ጭምር ወደ ኤርትራ እና ወደ ሶማሌ እንዳይጓዙ ጥብቅ ማሳጠንቀቂያ የሰጠዉ። ተያይዞም በዛዉ ወር በህዳርNovember 19/2008 ደግሞ የአዉሮጳ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮች የአሜሪካን መግለጫ በመከተል የሶማሊ እና የኤርትራን ሁኔታ በመገምገም አምባሲዎቻቸዉ በተጠንቀቅ እንዲቆዩ እና ዜጎቻቸዉም ወደ እነዚህ አገሮች እንዳይጓዙ አገደች። ይህንን በመቃወም የኤርትራ መንግሥት የፈረመበትን የተባበሩት መንግሥታት ተስማምተዉ ያጸደቁትን አንቀጽ 36ትን ዉል በማፍረስ በዲፕሎማቶች ላይ ጥበቅ ፍተሻ በማካሄድ ይገኛል። ይህ ክስተት የኔቶ ወታደራዊ ቺፍ አድሚራል ዳኒኤል ቤንጃንኩዝ በOctober 2008 የተናገረዉ “ዕቅዳችን ከወዲሁ እየተጠራቀመ ያለዉን አስፈሪዉ ጥቁር ዳመና መበተን ነዉ!!!” በማለት ያስተጋባዉን ማስገንዘቢያ የ አሜሪካ የባሕር ሃይል ወደ ቀይ ባሕር ዉሃዎች ማዝገሙ አና የአሜሪካ መንግሥት (ኖቨምበር) 11/2008 ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ እየተናኮሰችዉ ያለዉን አሳት እና በሌላ በኩል በጁቡቲ ላይም የምትጭረዉ የጠላትነት እሳት በመገንዘብ የፈረንሳይ የባሕር ሃይል ጦሮች ወደ ራስ ዳሜራ መገስገሳቸዉ እና ጁቡቲ አካባቢ ያሉት የጀርመን ጦርም በተጠንቀቅ መሆናቸዉን ስንመለከት “ሁኔታዉ ወዴት እያመራ ነዉ?” የሚለዉን የዉጥረቱ ሁኔታ አሳሳቢነት አሁንም እንዳለ ነዉ። የአሜሪካና የአወሮጳ ሕብረት በጣምራ እያካሄዱት ያለዉን ጸረ ሽብር እና የባሕር ላይ ዉንብድና የመከታተል ዘመቻ በመቃወም የኤርትራ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኖቨምበር 20/2008 የሰጠዉ የቁዋሜ መግለጫዉ ላይ የቀይ ባሕር ዉሃ የኒኩልየር አተላ መጣያ እየሆነ ነዉ በማለት ያወጣዉ መግለጫዉንም ጭምር ድርጊቱ የሚፈጽሙት ወገኖች እነማን እንደሆኑ በስም ሳይገልጽ በደፈናዉ ተሽቀዳድሞ መክሰሱ -አንድ ዓይኗ ሌላዉን ሸዉራራ ዓይን ብላ አስቀድማ የመሳደቧን ጉዳይ “ሳትቀድመኝ ልቅደማት” ዓይነቱ መግለጫ አዉጥቷል። ያካባቢዉ ተነካኪ ሁኔታ ቢነኩት በቀላሉ ሊቀጣጠል የሚችል ዉጥረት በበዛበት ቀጠና ላይ ሆኖ፤ በዉጥረቱ ላይ ገብቶ ባለበት ሁኔታ የድሮዉ የአሜሪካ ፕረዚዳነት ቢል ክሊንተን መንግሥትነቴን ሊገለብጥ ሲያሾር ነበር በማለት የኤርትራ ፕረዚዳንተ ኢሳያስ አፈወረቅ ደጋግሞ የከሰሰዉን ፓርቲ እና የቢል ክሊንተን ባለቤት የሆኑት ዛሬ በኦባማ አዲሱ አተዳደር የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመሆኑን ዜና ጋር ተያይዞ የ አካባቢዉ ዉጥረት ወደየት ሊያመራ ይችላል የሚለዉን ጥያቄ ያስነሳል? ከአካባቢዉ ዉጥረት በተጨማሪ የኢራን የባሕር ሃይል ወታደራዊ ባለሞያዎች ወደ ዳህላክ የመግባታቸዉን ጨምሮ የኤርትራ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ እንደዚሁም በሕባዊዉ ሠራዊቱና በአዛዦቹ፤የሕግደፍ ዉስጣዊ ዉጥረትና የካቢኔ ሚኒስትሮቹ በሌላ ገጽ ያለዉን ሁኔታ ምን ይመስላል? ይቀጥላል…. ።

No comments: