Saturday, September 28, 2024

መልዕክተ ጌታቸው ረዳ ለመላው የፋኖ አመራሮች በሙሉ ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 9/28/24

 

መልዕክተ ጌታቸው ረዳ ለመላው የፋኖ አመራሮች በሙሉ

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

9/28/24

                                                                                    

ይህ ልዩ መልዕክት በ16ኛው ክ/ዘመንና በ1983 ዓ.ም በተለያዩ ወራሪ ጎሳዎች የተለወጡ የቤተ አምሐራ የክ/ሃገር ፤ የከተማ ፤ አውራጃ፤ የወረዳ ፤ የወንዝና የሸንተረሮች የስም ለውጥ በሚመለከት ነው።

ከላይ በተጠቀሱት ዘመኖች  በወረራ አመጽ ወደ ሌላ የጎሳ መጠሪያ ስም የተለወጡ ሥያሜዎች እንዳሉ ይታወቃል። እናንተ ፋኖዎች ነፃ ባወጣችሁዋቸው ቦታዎች ሁሉ በሃይልና በሴራ የተለወጡ የቦታ ስሞች ስትደርሱ ወደ ጥንታዊ ስያሜአቸው እንዲለወጡና ጥንታዊ ስማቸውም በዝረዝር ይዛችሁ እንደገና  እየሰየማችሁዋቸው ሕዝቡም በምትሰጥዋቸው የስም ዝርዝሮች እንዲጠራቸውና በፍትሕ በፖሊስ ተቋማት በመሳሰሉ ተግባዊ እንዲሆኑ ስያሜን ነፃ የማውጣት ኦፐሬሺን የትጥቃችሁ መርሃ ግብር ውስጥ በሕልውና ትግላችሁ ውስጥ በሁለተኛ ረፍ ጎን ለጎን እንዲካሄድ  ጥሪ አስተላልፍላችኋለሁ።

ስለዚህ የጥዬ ዋና መልዕክት ይህ ታስቦበት የማያውቅ አዲስ ጥሪ ተግባራዊ እንድታደርጉት ለማስተላለፍ ነው። “’’ሕግ ያልገዛው ነፃነት ሃይል ይገዛዋል”” ይህንን አስታውሱ!

ያነሳሳኝ ምክንያት ልግለጽ። ሰሞኑን አንድ የልብ ወዳጄ “ዐምሓራ-ኀብራዊ ማንነቱና ተግዳሮቱ” የሚል ከደራሲ ባንተአምላክ አያሌው ባለ 617 ገጽ የተጻፈ መጽሐፍ እንዳነብ ጠቁሞኝ አማዞን ውስጥ አግኝቼው ማንበብ ጀመርኩ። መጽሐፉን ያገኘሁት ትንናት ነው።  ደራሲው ያበገነው የኦነጎችን ደባ በማንሳት “በዛሬው አጠራር “ወሎ” ተብሎ የተጠራው የጥንት ስሙ “ቤተ አምሓራ” የኦሮሞዎች መሆኑን የሚሰብኩ ኦነጎችና ጸረ ኢትዮጵያ ሃይላትን ማቆሚያቸው የት እንደሆነና የአምሓራው ምሁር ዳተኛነትና ዝምታ ተጨምሮበት ይህ የስም ለውጥና የመሬት መስፋፋት ነጠቃ እስከመቸ መቀጠል እንዳለበት ሲጠይቁ ወደ ሕሊናየ የመጣ ለዚህ መልስ አስገኚው “ፋኖ” አንደሆነ  ተሰማኝና መልዕክት ማስተላለፍ አለብኝ ብየ ወሰንኩ።

ይህም ተግባራዊ ለማድረግ መርሃ ግበሩን ለማስፈጸም ከፋኖ በላይ ሌላ ኃይልና ምሁር እንደማይኖር ስለማምን “ዘመቻው አሁንኑ ይጀመር” ዘንድ በተንቀሳቀሳችሁባቸው በነዚህ ቦታዎች ሁሉ ነፃ ባወጣችሀዋቸው አዳዲስ አስተዳደር በሾማቸሁባቸው አውራጃዎች ወረዳዎች ቀበሌዎችና ከተሞች ሁሉ  በጥንት ስማቸው እንዲጠሩ (አንደ አመላችሁ አምሓራ ትግል ውስጥ ትግሬ ምን አገባው ካላላችሁኝ በቀር ዝምታንና ኢፍትሓዊ አመጽን የማብቂያው ወቅቱ አሁን ነውና) ዝርዝር ጥናት አድራጋችሁ ተግባራዊ እንድታደርጉ እጠይቃለሁ።

አመጸኞቹ ዛሬም ቢሆን አምሓራውን እያስወጡ አሁንም በደረሱበት ቦታ ሁሉ አዳዲስ ስሞች እየሰየሙ እያየን ነው። አናንተም ይህንኑ “በቃ ማለት በቃ ነው!” የሚል መልዕክት የምታስተላልፉበት መንገድ አሁን እየመከርኩዋችሁ ያለውን የሕልውናችሁ “ሁለተኛው ኦፔረሺን” ነው።

ለምሳሌ ልጥቀስ (እናንተም ጨምሩበት)

አዲስ አበባን ለኦሮሞ ባለ ጊዜ ሹሞኞች ፤ አባ ገዳዎችና ሕዝብ ሰብስበው ሲናገሩ “ፍንፍኔ” እያሉ እነ አብይ አሕመድ ሳይቀሩ ይህ ስም በመጥቀስ የስም ለውጥ እያለማመዱዋቸውና ሕጋዊ ለማድረግ ነው። ታስታውሱ እንደሆነ ደንቆሮው የ አሜሪካ አምባሳደርም አዲስ አባባን “ፍንፍኔ” ብሎ በመግለጫው እንዳሰራጨ ታስታውሳላችሁ።

ስለዚህ ዓለም ያወቀው ሕጋዊ  ስሟ አዲስ አበባ  አዲስ አበባ ነው።

ሀገረ ሕይትን አምቦ ብለውታል ዓለም ማያን ሃሮ-ማያ ብለውታል፤ ናዝሬትን አዳማ ብለውታል፤ ደብረዘይትን  ቢሸፍቱ ብለውታል። ቤተ አምሓራን ወሎ ብለውታል፤ አንጎትን ራያ ብለውታል፤ ቢዛሞን ወለጋ ብለውታል፤ግራርያን ሰላሌ ብለውታል፤ ደዋሮን ሐረር ብለውታል፤ አናርያን ኤሊባቡር ብለውታል፤ፈጠጋርን አርሲ ብለውታል፤ ወዘተ….ወዘተ…..ወዘተ…።

ከዚህም በማያያዝ ደራሲው የዶ/ር ምስጋናው ታደሠ  መጽሐፍ ከቤተ አምሓራ እስከ ወሎ በሚል መጽሐፍ በገጽ 134 የተጠቀሱ የጥንቱ ቤተ አምሓራ አካባቢዎች ተስፋፍተው በመጡ ኦሮሞ ጎሳዎች ስም ተሰይመው ጠፍተዋል። ወረሂመኒ፤ ባሶ፤ ጋባቴ፤ ቃሉ፤ ቆቦ፤ ኮምቦልቻ፤ አቧሬ፤ አራርሳ፤ ለጎ ጎራ፤ግንደ ጎራ፤ ወረኖሊ፤ ተሁለደሬ፤ ቦረና፤ ለገሃዲ፤ ለጋምቦ፤ የመሳሰሉ የቤተ አምሓራ ስሞች የኦሮሞ ጎሳዎች የአካባቢውን ስም ቀይረው በራሳቸው ስም የሰየሟቸው ቦታዎች ናቸው (134 ዶ/ምስጋናው ታደሠ - ባንተአምላክ አያሌው  ገጽ 87)

በስለዚህ በዚህ የዓይን አውጣ ድፍረት ዛሬም እየቀጠለ ስለሆነ አንድ ቦታ ላይ እልባት እንዲያገኝ 1) አምሓራ እንዳይኖር እየተፈጸመበት ያለውን ጭፍጨፋ ለማስቆም ጠመንጃ መታጠቃችሁ አስፈላጊ አንደነበር ስወተውታችሁ መኖሬን ብዙዎቻችሁ ስለምታስታውሱት ሕልውናችሁን ለማስከበር መፋለማችሁ ቀዳሚው ኦፔረሺን (ኦፐረሺን ሕልውና) ሲሆን 2ኛው የሕልውናው ኦፔረሺን ዘመቻው ክፍል ደግሞ የባሕልና የቦታ ስም ለውጥ መደረጉን ወደ ጥንታዊና ታሪካዊው ቦታው መመለስ “የባለርስት ሕጋዊነት ኦፐረሺን” ማረጋገጫ ስለሆነ አንድ ሕዝብ ታሪኩና ስሙ ተነጥቆ “አምሓራ” በሕይወት እያለ “አምሓራ የሚባል ነገድ የለም” የሚለው ዘመቻ ከቦታ ነጠቃና የስም ለውጦች የተያያዘና የስም ለውጥ የተደረገበት ዋና ምክንያትም ያንን ለማረጋገጥ እንደሆነ ማወቅ ብልህነት ነው።

ሰላም እንሰንብት!

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

Monday, September 23, 2024

ባዶ ቤት በቁንጫ ይወረራል! ሽግግርና ድርድርድር ከማን ጋር? ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 9/23/24

 

ባዶ ቤት በቁንጫ ይወረራል! ሽግግርና ድርድርድር ከማን ጋር?

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 9/23/24

በሙሶሎኒ የፖለቲካ ዘረመል የተደቀሉ የወያኔ ትግሬዎች በአገር በቀል “ጣሊያናዊ ቅኝ ግዛት” ሥልት ተቃኝተው ኢትዮጵያን በዘርና በቋንቋ ሸንሽነው ስተዳዳር አማራን፤ አማርኛ ቋንቋን፤ በጣሊያኖች ቦቴ ተረግጣ ወድቃ የተነሳቺው ብሔራዊ ሰንደቃላማችንን እና የአማራ መደበቂያ ብለው የጠርዋትን ኦርቶዶክስ ሃይማኖታችንን በጠላትነት ቀለበት እንዲታዩ ዓልመው ለማጥቃት ሥልጣን የተቆጣጣሩት ትግሬዎች ያንን ሲፈጽሙ ለ27 አመት ለነሱ ያልተምበረከከው ኢትዮጵያዊ ዜጋን ደግሞ ገድለው፤ ዘርፈው፤ ቀጥቅጠው ካሸበሩት በላ መሪያቸው በፈጣሪ ትዕዛዝ ተወገደ። ጥቂት ዓመታት ከገዙን በላ የተቀሩትም በሕዝቡ እምባ ከሥልጣን ተወገዱ። ሲጠረጉ፤ በምትካቸው የተተካው አድፍጦ የቆየው አገልጋያቸው ነበር።

አገልጋያቸውም ኦሮሙማ በሚል ድብቅና ግልጽ ፕሮጀክት አንግቦ ወደ ሥልጣን የወጣው ኦነጉ አብይ አሕመድም ነብሰ-ገዳዮችን፤ ወንጀለኞችን ፤ አጭበርባሪዎችን ፤ አገር ገንጣዮችን አክራሪ የሃይማኖት ጀሌዎቹንም ሁሉም ያለ ምንም “ቁጥጥር እና ውል” ወደ አገር እንዲገቡ በማድረግ “ረገብ ብሎ” የነበረው ግንጠላቸውን እና የመግደልና የሽብር ጥማታቸውን ለማስቀጠል ባንዴራቸውን ሳይቀር ማውለብለብ እንደሚፈቀድላቸው ቃል ገብቶላቸው ገብተዋል። በገባላቸው መሰረት፤ ኢትዮጵያን ዛሬ ባለችበት አሳዛኝ ክስተት እንድትገባ አደረግዋት። እርሱም ሥልጣኑን እርካብ አጥብቆ በመያዝ ሰላም አመጣለሁ ብሎ ይቅርታ ጠይቆ ያታለለውን ሕዝብ ለኑሮ ውድነት፤ ለስደትና ለባሰ ዕልቂት ዳረገው።

ይህ እንዲህ እያለ፤ እዚህ ላይ ታሪክ መርሳት የሌለበት ተጠቃሽ ሰው ባገሪቱ ብቻውን የተስፋ ሻማ አብርቶ ከጥቂት ተከታዮቹ ጋር ሰለማዊ ትግል እታገላለሁ ብሎ ብዙ ዋጋ የከፈለ እስክንድር ነጋም ሲታገላቸው የነበሩት ሁለቱ ሥርዓቶች ለመጣል ወይንም ሥርዓት ላማስያዝ ሕዝቡ እንዲያግዘው የተቻለውን ያህል ቢጥርም ሕዝቡም እንደ ወትሮው “ዳተኛ” ሆኖ ብቻውን ተስፋ በመቁረጡ “አፓርታይዳዊው ሥርዓት” በጥይት እንጂ በሰለማዊ እንደማይገረሰስ ውሳኔ ደርሶ ጫካ ገብቶ ፋኖን ተቀላቀለ። ብዙዎቹም የእርሱና የመሰሎቹ ኮቴ በመከተል ጫካ ገብተው ዛሬ አታላዩና ኦነጋዊውን  ሥርዓት እያዋከቡት ይገኛሉ።

ለብዙ አመታት “አማራው ወደ ጫካ ይግባ” ስል ብቸኛ ውትወታ ሳሰማ የነበርኩኝ እኔም ውትወታየ ግብ መትቶ እነሆ እንደተፈለገው ጫካ የገቡት “ፋኖዎችም” ባንድነት ባይታገሉም እሰይ የሚያሰኝ አመርቂ ተስፋ እየገነቡ ነውና አማራው እንደ ድሮ  ፋሺሰት ትግሬዎችም ሆኑ ናዚ ኦሮሞዎች የለመዱበትን አማራን የመናቅ ባሕሪያቸው ሁለቴ እንዲያስቡበት አድርጓቸዋል። አሁን መበርታት ብቻ ነው።

ሁኔታው እንዲህ እያለ”  ውጭ አገር የሚኖሮው ልደቱ አያሌው ኢትዮጵያዊያን ምሁራንና ፖለቲከኞችን እንዲሁም ወያኔዎችና ኦነጎችን በመጋበዝ በርዕዮት ሚዲያ (ቴድሮስ ፀጋዬ በሚያዘጋጀው ድረገጽ ቲ/ቪ) በርከት ያሉ የውይይት ክፍሎች ባመስተናገድ “ከአብይ ገሃነም መውጫ ”“ሠላም አንዴት ይምጣ?” “ዘላቂ ሰላም፤ሃቀኛ አገራዊ ውይይትና ድርድር በአዲስ የሽግግር ሂደት፤ ጭፍጨፋው እንዴት ይብቃ? | አገዛዙን ለማስወገድ ወይም ለማስገደድ እንዴት እንተባበር? ወዘተ….. የሚሉ ውይይቶችን በማዘጋጀት በርት ያሉ ከላይ የተጠቀሱት ብዙዎቹ የምናውቃቸውና በሃገረ ትግራይ ቅዠት የተቃኙ አዳዲስ የወያኔ ቡቃያዎች እያነጋጋረ ነው።

የልደቱ ሃሳብ በጎ ቢሆንም እየተከተለው ያለው ስልት ግን ድሮ ተሞክሮ የወደቀ ስልት ነው። ይሄውም ካሁን በፊት እዚህ ውጭ አገር ተሞክሮ ውጤት ያላመጣና ያውም ማሞኚያ መንገድና አክራሪ ሃይሎችና ተገንጣዮች የብዙ አምሐራ ነብስ ጭፍጨፋ እንዲካሄድ ያዘዙ ሃይላት ሰው መስለው እንዲታዩ የተጠቀሙበት መድረክ እንደነበር እናስታውሳለን (ሌንጮ ባቲን፤  ሌንጮ ለታን ፤ ዲማ ነገዎን፤ ፕሮፌሰር ሕዝቄል ጋቢሳ ፤ ጃዋር መሐመድ  ወዘተ…ወዘተ… ኦነጋዊው ወኪላቸው ወደ አዲስ አባባ እንዲገቡ ከጠራቸው በላ ምን እንዳደረጉና ምን ይናገሩ እንደነበር እናስታውሳለን።

ልደቱ ዛሬም ደግሞ ያመጣቸው እነኚያን የምናውቃቸው ሰዎች (አክራሪ ብሐረተኞችና ከአማራ ጋር አንዳትጋቡ ከተጋባችሁም ተፋቱ የሚሉ እነ (አሉላ ሰለሞን) ወይንም አማራዎች ሱቃችሁ አንድ ነገር ለመግዛት ፈልገው ኦሮሙኛ ካልተናገሩ ዕቃ እንዲገዙ አትፍቀዱላቸውአማራዎች ኦሮሞን ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው (ኦነጉ በቀለ ገርባ) እንዲሁም ከትግሬዎች ደግሞ አዳዲስ የወያኔ ቡቃያዎች ኢሳያስ ሃይለማርያም፤ እና ግደይ ምዑዝ (ኢትዮጵያ ላይ ጥላቻቸው የበረታባቸው ፤ የሃገረ ትግራይ አቀንቃኝ ብሔረተኞች) እና የመሳሰሉ የኢትዮጵያን መፍረስ የሚመኙና የሚተጉ ግለሰቦችን ኢትዮጵያን በጠላትነት የፈረጁ ኢትዮጵያ አገራችን ነች የማይሉ፤ ለኢትዮጵያ ችግር መፍትሔ ሰጮዎችና መፍትሔ አፋላላጊዎች ተደርገው በልደቱ አይን የታጩ ያንን የሰለቸን ነገር ሲደግመው እያየሁ ነው።

እነዚህ ሰዎች ከኢትዮጵያ መፍረስ ሌላ አማራጭና ፍላጎት እንደሌላቸው “ፋይላቸው” ይመሰክራል። “ቲ ዲ ኤፍ” ብለው የሚጠሩት  “ዱርየና ዘረኛ ተዋጊያቸው”  “ተጋድሎ ትግራይ ቦሎ ነቲ  ዓሻ አምሓራይ” እያሉ ሽሮና በርበሬ ሊጥ እና የመጠጥ ቤቶች ቢራና አረቄ እየዘረፉ ሰክረው ህጻናት ልጃገረዶችንና  ሴቶችን እየደፈሩ፤ ደሴን አልፈው ሰሜን ሸዋ ሲገቡ ያንን የተላኩበትን ዘረኛ ተልዕኮአቸው ለመፈጸም የታነጹበትን ዘፈናቸው እየዘፈኑና እየጨፈሩ “በተጋዳላይ ትግራይ” ቅኝት “ሓቢርና ንሕሰብ ብዛዕባና ናብራ - ሎሚስ ይኣኽለና ግዝኣት ናይ አምሓራ” (የአማራ ጨቋኝ አገዛዝ ለማብቃት አንድ ሆነን ስለ ለራሳችን ኑሮ ብቻ በማትኮር እናስብ” እያሉ የአማራን ማሕበረሰብ ከጫፍ አስከ ጫፍ እረፍት ያሳጡትን ሥርዓተ-ቢስ ዋልጌ ተዋጊያቸውን ወደ ሃገረ ትግራይ ምስረታ እንዲያስብ የሚቀሰቅሱ እነዚህ እና የመሳሰሉ የወያኔ ቡቃያዎችን ነው ልደቱ ስለ ኢትዮጵያ አንድነትና ሰላም የሚጨነቁ ናቸው ብሎ ተስፋ ጥሎባቸው እየደጋገመ የጋበዛቸው።

ልደቱ አያሌው ከተገንጣዮች ጋር አብሮ መስራት መሞዳሞድ ችግር የለበትም። ሌላ ቀርቶ ለፈርጀ ብዙ ችጋራችን ዋናው ቀያሽና ተጠያቂ የሆነው ጥቁር ጣሊያን ብለን እኛ ጥቂት ትግሬዎች የምንጠራው ለመለስ ዜናዊ ሳይቀር ልቡ የሚደማ የዋህ ፖለቲከኛ ነው። ጋዜጠኛ ያየሰውና ልደቱ ከነዚህ ዓይነት ሰዎች ጋር መሞዳሞድ ችግር የለባቸውም። ከነዚህ ጋር መተሻሸትና ማሞገስ ሥልጡን ፖለቲካ ነው ይሉታል።

ልደቱ መለስ ሲሞት ለ ለትምህርት ሄዶ እያለ  አንድ ጋዜጠኛ ስለ መለስ ሕልፈት ምን እንደተሰማው እንዲገልጽለት ሲጠይቀው እንዲህ ያለውን ላስታውሳችሁ፦

 “ኢትዮጵያ  አንድ ሰው አጥታለች!!” “መጽሐፌን አይተህ ከሆነ ተቃዋሚዎች እሳቸውን ከሚያይበት ዓይን መቀየር እንዳለበት መለወጥ እንዳለበት (እኔ ከተቃዋሚው) ለየት ባለ ዓይን ነበር የማያቸው” “ያኔ ብዙ ሰዎች እንደዚያ ብየ በመጻፌ ብዙ ሰዎች ደስ ያላለቸው እንደነሩ አውቃለሁ።ዛሬ (እኔ ያልኩትን) የኢትዮጵያ ሕዝብ በዚያ መልኩ እያሳየ ይመሰልኛል። በመሞታቸው አዝኛለሁ፡ ለቤተሰቦቻቸው፤ ለኢትዮጵያ መንግሥትም ‘ለኢትዮጵያ ሕዝብም’ መጽናናትን እመኛለሁ። የፖለቲካ ልዩነታችን እንደተጠበቀ ሆኖ በዚህ ወቅት የማይታጡ ምናልባትም ለወደፊቱ ለሃገሪቱ በጎ ተግባር ለማበርከት ዕድሉ ይኖራቸው ነበር ብየ አስባለሁ። እና “ኢትዮጵያ አንድ ሰው አጥታለች ብየ አምናለሁ!” ከፓርላማ ውጭ እኔና እሳቸው በጋለ ስሜት ስንከራከር እንደነበር እና ከዚያ መድረክ ውጭ በአካል ስታገኛቸው “ሰውነታቸውን/ (ሰብዕናቸውን) የምታየው ያኔ ነው”። እና ምናልባትም እሳቸውን የምናይበትን ዓይን ቀደም ብሎ ቢለወጥ ኖሮ የአገሪቱን ችግር ሳይሆን የመፍትሔ አካልም አድርገን አይተናቸው ቢሆን ኖሮ ‘ተገቢውን ዕውቅና እና ምስጋና’ ሰጥተናቸው ቢሆን ኖሮ ምናልባት አሁን ከሰሩት የተሻለ ይሰሩበት የነበረ ዕድል ይኖራቸው ነበር ብየ አምናለሁ።>> ይላል ልደቱ ስለ ወዳጁ መለስ ዜናዊ ሕልፈት የተሰማው ሐዘኑን ሲገልጽ

አቶ ልደቱ እያለን ያለው ‘መለስ ዜናዊ’ በአካል ስታገኘው እጅግ ሰብአዊ ነው፤ ችግር አምጪ ሳይሆን መፍትሔ አመንጪ አድርጋችሁ ብታዩት ኖሮ ተገቢውን “ዕውቅና እና ምስጋና ስላልቸራችሁት” ዕንቅፋት ስለሆናችሁበት እንጂ ለኢትዮጵያ ከአፓርታይድ ባንቱስታዊው አስተዳዳር ውጭ የተሻለ መፍትሔ ያመጣ ነበር እያለ እኛ ለመለስ/ለወያኔ/ አስተዳደር ያለመሻሻል “ዕንቅፋት እየሆንበት” እንደሆነ እኛን አምርሮ ይወቅሳል። “መለስ በማጣታችሁ ኢትዮጵያዊያን ጽናቱን ይስጣችሁ ይለናል።ይገርማል!!!

  ወያኔነት ከዚህ ወዲያ ካለ ንገሩኝ” ብየ ነበር መለስ ሲሞት ባንድ ጽሑፌ ልደቱን ተቺቸው የነበረው።

ስለዚህ የተጠቀሱት በርካታ ሰዎችና እዚህ ያልተጠቀሱ ግለሰዎች ኢትዮጵያን አማራን ሰንደቅ አላማን አማርኛ ቋንቋን እና በመሳሰሉት የአገሪቱ ምሰሶዎች መዳከምም አለባቸው ብለው ስለሚያስቡ የነሱ አካል አድርገው ስለማያዩዋቸው ከነዚህ ጋር የሽግግር መድረክ መስርቶ ሰላም ይመጣል ብሎ መቃዠት ውጤቱ አብይ ወደ ሥልጣን ሲገባ እነዚሁ የሰላም አፈላላጊዎች ተብለው የነበሩት ግልብጥ ብለው ትከክልኛ ቆዳቸው እንዴት እንዳሳዩት የምናስታውሱት ነው።

የልደቱ ሙከራ ካለፉት አወያዮች የሚለየው ነገር ቢኖር “ኦነግና ህወሓት” ወደ ኢትዮጵያዊነት ተመልሰዋል ይሉን እንደነበሩን የመድረክ አዘጋጆች ከእነ እንደ ዶ/ር ጌታቸው በጋሻው፤ ብርሃኑ ነጋ ወዘተ….የመሳሰሉት ይለያል። ልደቱ ግን በግልጽ እንደ ተጠቀሱት ባይልም፡ እባቡም ፤ ጃርቱም ፤ ዕርግቡም ፤ ጅቡም፤ ቆቁም ፤ ጊንጡም አሕያውም ፤ ሚዳቋንም…. ሁሉም አሰባስቦ በየጥሩምባቸው ያስጮሃቸዋል። ይህ ደግሞ በፖለቲካ የተፈጥሮ ሕግ የማይሰራ ነው። ወንጀል የሰሩ ሰዎች ፤ኢትዮጵያ አይደለንም የሚሉ ሰዎችና ቡድኖች መፍትሔ ያመጣሉ ብሎ መጠበቅ "ከእባብ ዕንቁላል ዕርግብ መጠበቅ ነው"።

የውይይትና የመፍትሔ አካል ይሁኑ እንኳ ቢባል (ምክሬ አገር ውስጥ ላለው ለአማራው ነው) ወቅቱ አሁን ሳይሆን ብረታችሁን አቀጣጥላችሁ፤ ታብየው የፉከራና የንቀት አፋ ከሚደፍቁ የትግራይ ብረተኞችን ኦሮሞ ብሔረተኞች እኩል ተገዳዳሪ ጡንጫ መገንባታችሁን ስታረጋግጡ ያኔ እባቡም ፤ ጃርቱም ፤ ዕርግቡም ፤ ጅቡም፤ ቆቁም ፤ ጊንጡም ፤ አሕያውም ፤ ሚዳቋንም ፤ ከብቱም…. ተሰባስበው ጡሩምባ ሲነፉ ፤ ‘የናንተንም የጡርምባ ድምጽ እንዲሰሙት ይገደዳሉ’። የጥሩምባችሁ ድምጽ ይዞ መምጣት ያለበት “በነገዳችሁ ላይ ጭፍጨፋ ያዘዙና የተካፈሉት ሁሉ የሚቀጡበት “ገለልተኛና ዓለም አቀፍ ሰዎች የሚካፈሉበት “ ፍርድ ቤት እንዲቋቋምና ወንጀለኞቹ ተመልሰው እንደ በፊቱ ፖለቲካና በከፍተኛ ሥልጣን እንዳይሳተፉ” እንዲደረግ ዓለም አቀፍ አገሮች የሕግ፤ የማሕበራዊ ፤ የሥነ መንግሥት የሽግግር ልምድ ያካበቱ የውጭ ሰዎችንና የተባባሩት መንግሥታት ታዛቢዎች ባሉበት ካልተዋቀረ ፤ የተለመደው “በሽግግር ስም መተቃቀፍ’ እዚህ እንደምንሰማው ቀልድ “ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ” ውይይት እልባት እንዲኖሮው ከፍተኛ ሚና መጫወት አለባችሁ።

ሁሉም ጎጆና ጠመንጃ ገንብቷል፤ ያልሰራው አማራ ነበር፡ ከድንፋታ ደንፊዎች ጋር እኩል ለመቀመጥ “መጀመሪያ” ደንፊዎችና ትምክሕተኞቹ የያዙትን መያዝ አለባችሁ። ገዳዮቹ ትላልቅ ዋርካዎችን ገዝግዘው ቆርጠው አገሪትዋ ባዶ ስላስቀርዋት ቁንጫዎቹ ገብተው ለበርካታ አማታት ጨፈረውባታል። አገሪቷ ሰው እንዳይኖርባት አደረጉ! አሁን ያንን መደግም የለበትም። እንደ ደንፊዎቹ ታጥቀህ ቅረብ። የ “Garbage in Garbage out” ፍልስፍና አያስፈልግም! ተሞክሮ የወደቀ ነው! ወንጀለኞችና ዘረኞች መጋፈጥ አማራጭ የሌለው አዲስ ስልት መሆን አለበት

በዚህ ዓለም ጉልበትና ገንዘብ ገዢዎችና አስከባሪዎች ናቸው። ከዚህ የዓለም ነባራዊ ሃቅ ብንሸሽም በቀጥታም በተዘዋዋሪም ለዚያ ተገዢነታችን አይቀሬ ነው። የመጎንበስ ውጤት አይተነዋል። ወዳጄ ዶ/ር አሰፋ አንደለው <<ፋሽስቶች ያሉትን ሁሉ በጭፍንነት የሚያደርጉ ሕግ የማያውቁ ናቸው!” እውነት ነው። ከዚያ ጥቃት ለመዳን መዘጋጀት ያስፈልጋል፡ “ሕግ ያልገዛው ነፃነት ሃይል ይገዛዋል” የሚባለውም ለዚህ ነው።

አበቃሁ!

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)


Sunday, September 22, 2024

አዲስ መጥረጊያ (The New Broom) ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 9/22/24

 

አዲስ መጥረጊያ (The New Broom)

ጌታቸው ረዳ 

(Ethiopian Semay) 

9/22/24

ፖለቲካዊ ትችቴን ካቀረብኩ ትንሽ ቆየት ቢልም ለዛሬ የማቀርብላችሁ እኔን ባስደነቀኝ ዘመናዊና ሃገራዊ የክሕነት ትምሕርት የተማሩ ኢትዮጵያዊያንና ኢትዮጵያዊት ወጣት ምሁራን ሃገራችን የተጠቃችበት መንገድና አጥቂዎቹ እነማን እንደሆኑ የሚገርም ምሁራዊ ምጉትና ትንተና እነሆ አንድታደምጡ አቅርቤአለሁ። ተወያዮቹ አዲስ መጥረጊያ (The New Broom) ብያቸዋለሁ።

ኢትዮጵያ በኤርትራና በትግራይ ፋሺቶች ሴራ የደረሰባት ጥቃት ጠባሳውእስከወዲያኛው የሚሽር አይደለም። ሆኖም ኢትዮጵያ ወደቀች ስትባል የመነሳት አቅምዋ በሃይማኖታችን እንደተባለውእጆችዋን ወደ ፈጣሪዋ ትዘረጋለችበተባለው ሃገራዊ መርሆ ምክንያት ደጋግማ ስትንሳ ታሪክ አሳይቶናል። ዛሬ የመነሳትዋ ምልክትም ከነዚህ ወጣቶች አንደበትና ሃይለኛ ምጉት ማየት ችያለሁ።

በሚቀጥለው ሳምንት የማቀርበው ትችት

1966 . ጀምሮ እስካሁን ድረስ ሀገራችን ለደረሰባት ጥቃት ቀዳሚ ተጠያቂዎች ምሁራን (ሁሉም ባይሆኑም አብዛኛዎቹ) ሲሆኑ፤ ከዚያ ካለፉት የጥፋት አመንጪ ምሁራንሳይማሩ ቀርተውዛሬም ፖለቲካውን በተቃዋሚነት የሚመሩ ተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎችሠላማዊ የሽግግር መንግሥትለማምጣት የውይይታቸው ተሳታፊዎችን የሚጋብዙዋቸው ተሳታፊዎቹ ብዙዎቹበአማራና በአማርኛ፤በኦርተዶክስ ተዋህዶና በሰንደቅዓላማችን ባጠቃላይ ኢትዮጵያን ለደረሰባት ግፍ ሁሉ ተጠያቂ ለሆኑት አካሎችን ታሳታፊዎች በማድረግ በተጎጂዎች ላይ ያሾፋሉ።

ይህ አካሄድ ተደጋግሞ ወያኔን ለመጣል ሲደረግ በነበነረው ወንጀለኞችን ሁሉ መድረክ የሰጠ አንዳንዴም እንደልባቸው እንዲዋኙና እንዲዋሹ ያደረገ የመተሻሸት ትግል የከሸፈ ድጋሚ አሰራር ስለሆነ ያንን በሚቀጥለው ሳምንት ይዤ እቀርባለሁ። እስከዛው ይህንን አስገራሚ ክርክር አድምጡ።

"ቤተ ክርስቲያን ለምን ራሷን መከላከል አልቻለችም?" - ክፍል 2 | ደብተራና ካህናት በአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ (1900 - 2013 .)

https://youtu.be/r-4Q8_wdkAQ?si=pI9rEv8ApMjZOvo5

 

Thursday, September 19, 2024

Getachew at the Flag Raising day Sept 6 2024

 

Getachew at the Flag Raising day Sept 6 2024



Tuesday, September 17, 2024

Getachew at the September 11 2024 / Meskerem 1/ 20217 our New Year celebration with Mayer & Santa Clara County Supervisor Cindy Chavez

 Getachew at the September 11 2024 / Meskerem 1/ 20217 our New Year celebration with Mayer & Santa Clara County Supervisor Cindy Chavez



Tuesday, September 10, 2024

የተረሳው አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ አርበኛ፣ እና የዓመቱ ምስጉን ኢትዮጵያዊያኖች ጌታቸው ረዳ መስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ ዓመት

 

የተረሳው አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ አርበኛ፣ እና የዓመቱ ምስጉን ኢትዮጵያዊያኖች

ጌታቸው ረዳ

መስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ መት

    ዛሬ በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያ ቀን፣ በዕለተ ቅዱስ ዮሐንስ በበጎ ተግባራቸው “መላው የኢትዮጵያ አገር ወዳድ ሕዝብ ሊያመሰግናቸው ይገባል” ስላልኳቸው ሰዎች፣ እንዲሁም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በዝና እና በአኩሪ ተግባሩ የሚያውቀው፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን፣ በኢትዮጵያውያን ሕሊና ትውስታ ስለተነፈገውና ስለ ተረሳ፣ ትግራይ ያፈራችው አንድ ታላቅ ኢትዮጵያዊ አርበኛ ሃሳቤን ላካፍላቹህ ወደድኩ።

  ሰውዬው በ1981 ዓ.ም አካባቢ ከወያኔ የበረሃ ትግል ወጥቶ፣ እጁን ለወቅቱ መንግሥት በመስጠት፣ የተደበቀውን የወያኔ ጸረ ኢትዮጵያነት ሴራ እና ተልዕኮ፣ አሰቃቂ የጭፍጨፋ ወንጀል፣ እንዲሁም ለድርቅ ዕርዳታ እንዲውል ከዓለም በጎ አድራጊዎች ለወያኔ የተሰጠው በሚሊዮኖች ዶላር የሚቆጠር የገንዘብ ዕርዳታ፤ እንዴት ለድርጅቱ ማጠናከሪያ እና ለመሪዎቹ መጠቀሚያ እንደዋለ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢትዮጵያና ለዓለም ሕዝብ ያጋለጠ ታላቅ ጀግና ነው።በዚህም የተነሳ የሕይወት ጉዞው በብዙ ውጣ-ውረድ የተሞላ እና አስቸጋሪ ነበር።

   ትግራይ/አድዋ ላይ የተወለደው ውድና ክቡር ወዳጄ፣ አርበኛው አቶ ገብረመድህን አርአያ፣ የሚኖረው በምዕራብ አውስትራሊያ (ፐርዝ ከተማ) ሲሆን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደረሰበት ድንገተኛ የአካል ጡንቻዎች አለመታዘዝ ምክንያት፣ የጤና ዕክል ገጥሞታል።

    ሆኖም በዚህ ክፉ ጊዜም ሆነ ቀደም ሲል፣ ብቸኝነት እንዳያጠቃው፣ የወያኔዎች እጅ አዙር ጥቃት እንዳይደርስበትና ተንከባካቢ እንዳያጣ፣ ለረጅም ዓመታት ከጎኑ ተለይተው የማያውቁት ምርጥ ኢትዮጵያዊያን እና ኢትዮጵያዊት፤ ማለትም ወ/ሮ የምስራች አስፋውበአቶ ፈለቀ ተገኝ እና በአቶ ዓለሙ መንገሻ እርዳታና ድጋፍ፣ በአረጋውያን መጠለያ ውስጥ ማረፊያ ተዘጋጅቶለት፣ እዚያው ምግብ መኝታና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየተደረገለት በእንክብካቤ እየኖረ ይገኛል።

በነገራችን ላይ ወ/ሮ የምስራች አስፋው የዚሁ መጠለያ ዋና ስራ አስኪያጅ ስትሆን፣ ከመደበኛ ስራዋ ውጭ የአቶ ገብረመድህን አርአያን የዕለት ተዕለት ውሎ፣ ያለበት ድረስ እየሄደች በቅርበት የምትከታተል ታላቅ ኢትዮጵያዊት መሆኗን ተረድቻለሁ።   

  እንዲሁም ለብዙ ዓመታት በማማከርና በአይዞህ ባይነት፣ በመጽሐፉ፣ በጽሑፎቹና ዶክመንቶቹን በአርታኢነት በመርዳት ያልተለየው፣ ሌላው የቅርብ ወዳጁ ጋዜጠኛ ቅዱስ ሃብት በላቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የገዳማት የበላይ ኃላፊ፣ የምሥራቅ አውስትራሊያና ኒውዚላንድ አሕጉረ ስብከት ሊቀጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፤ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፣ እርሱ ወደሚኖርበት አድላይድ ከተማ /ደቡብ አውስትራሊያ በመጡበት ወቅት፣ አቶ ገብረመድህን  ያጋጠመውን የጤና እክል አጫውቷቸው በጣም አዝነው ያለበት አገር ድረስ ሄደው ሊጠይቁት ቃል ገብተውለት ነበር።

ብፁዕ አባታችን አቡነ ሉቃስ ምንም እንኳን አቶ ገብረመድህን የሚኖርበት ምዕራብ አውስትራሊያ፣ በርሳቸው አገረ-ስብከት ስር ባይሆንምና በሌላ ሊቀ ጳጳስ ስር የሚተዳደር ቢሆንም፣ ቃላቸውን አክብረው አቶ ገብረመድህን ያለበት አገርና መጠለያ ድረስ በመሄድና በአካል በመጎብኘት ቡራኬያቸውን በመስጠት፣ ታላቅና እውነተኛ የሃይማኖት አባትነታቸውን ዳግም አስመስክረዋል።

 በብጹዕ አባታችን አቡነ ሉቃስ እግር ሥር ወድቄ እሳለማለሁ! ቀደም ሲልም በስቃይ ላይ ላለው፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተቆርቁረው በድፍረት አብይ አሕመድን በማውገዞት፣ ስምዎንና ክብርዎን ሊያጎድፉ ተነስተው ለነበሩት ሰዎች በጽሑፍ መልስ ሰጥቻለሁ፤ ዛሬም ብፁዕነትዎን በድጋሚ አመሰግናለሁ።

 እንዲሁም  በተለያየ ጊዜ ከገብረመድህን ጎን ለቆማችሁ፣ ስማችሁን ስላላወቅኩ ግን ያልጠቀስኩዋችሁ በጎ አድራጊዎችን፣ በአምላክ እና ገብረመድህን ስም ሳላመሰግናችሁ ማለፍ አልሻም።

ገብረመድህን የዛሬን አያድርገውና መላው የተቃዋሚ ሚዲያዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ “የእንግሊዝኛው ቢ ቢ ሲ” እና “የ ቪ ኦ ኤ አማርኛ ክፍል” ሳይቀር ለበርካታ ዓመታት እየተንጋጉ፣ ስልኩን በወረፋ እየጠበቁ ነበር ቃለ መጠይቅ ያደርጉለት የነበረው። ታዲያ ያኔ ለሚዲያቸው ፍጆታ የበቃቸውን ያህል እንዳልቃረሙ ሁሉ፤ ዛሬ ድንገት የጤና እክል አጋጥሞት ራሱን መንከባከብና የተወሰነ የሰውነቱን ክፍል እንደልብ ማዘዝ፣ ባልቻለበት ጊዜ “የት ወደቀ? የት ሄደ? ምን አጋጠመው?” ብለው አልጠየቁትም። ካሁን ቀደም ከሃዲ ሕዝብና ምስጋና-ቢስ ሕዝብ! ስል ሁሌም ያነበባችሁኝ ይመስለኛል።ታላቁ እስክንድር ነጋን እንደካዱት ማለት ነው!

   በብቸኝነት ላመሰግነው የምፈልገው የመገናኛ ብዙሃን ተቋም ቢኖር በቅርቡ ገብረመድህን አርአያን ያለበትን ሁናቴ ለሕዝብ ይፋ ያደረገውን ኢትዮ 360 ሚድያን ነው። በዚህ አጋጣሚ ለመላው የዝግጅት ክፍሉ ባልደረቦች፣ ከቀድሞ ጀምሮ ያለኝን አድናቆት፣ ለስራቸው ያለኝን ክብርና ከፍተኛ ምስጋና ሳልገልጽ ማለፍ አልሻም።

    ወደ እኔው ልመለስና ለበርካታ ዓመታት የገብረመድህን አርአያ የቤት ስልክ ሁሌ እየደወልኩ አብረን እንጫወት ነበር።ታዲያ እንደወትሮዬ ደጋግሜ ስደውል ስልኩ ተቋርጦ አልሰራ ብሎኝ የምጠይቀው ሰው አጥቼ ሲጨንቀኝ በራሴ ሚዲያ “አቶ ገብረመድህን አርአያ ያለበት  ቦታና ሁኔታ የሚያውቅ ሰው እባካችሁ ንገሩኝ ?” ብየ ጥያቄዬን አቀረብኩኝ።ይህንን ያነበበው ወዳጁ ቅዱስ ሃብት በላቸውም ስለ ሁኔታው ምላሽ ሰጥቶ አሳወቀኝ።

    ከዚያም አልፎ በቅርቡ ከገብረመድህን ጋር በክብርት ወ/ሮ የምሰራች አስፋው አማካኝነት ዳግም በስልክ እንድገናኝ አድርጎኛል። ገብረመድህን የሚኖርበት ፐርዝ ከተማ ቅዱስ ሃብት ከሚኖርበት አድላይድ በአይሮፕላን ከ3 ሰዓት በላይ ርቀት ያለው ሲሆን፣ ገብረመድህንን ለመጠየቅ ወደዚያው አምርቶ የሚፈልገውን እንክብካቤ አድርጎለት፣ ስልክ ገዝቶለት፣ ወንድማዊ እንክብካቤ በማድረጉ ደጋግሜ ምስጋናዬ አሁንም ይድረሰው።

   ባጠቃላይ እነዚህ ሩህሩሃን አገር ወዳድ ሰዎች ባይኖሩ ኖሮ፣ ዛሬ ገብረመድህን “ቤትና ተንከባካቢ አልባ አስፋልትና በረንዳ አዳሪ ሆኖ ልናገኘው ሁሉ እንችል ነበር”። በዚህ አጋጣሚ ይህ ምንጊዜም በታሪክ የሚወሳ ታላቅ ተግባር የፈፀመ ኢትዮጵያዊ ጀግና፣ ባስቸጋሪ ወቅት ህይወቱ ለወያኔ ጨካኝ ነብሰገዳዮችና ሴረኞች ለአደጋና ለግድያ ተጋልጦ፣ በዚያ ሳይበገር የሚያውቀውን የወያኔ ወንጀልና ድብቅ አጀንዳ ይፋ በማድረግ ውለታ የዋለለት የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በሕይወት ሳለ ተገቢውን የላቀ አክብሮት፣ ምስጋና እና ሽልማት እንዲያቀርብለት ጥሪዬን ማስተላለፍ እሻለሁ።

   በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን በጎ አድራጊዎችን የሚሸልሙ እዚህ አሜሪካ የተመሰረቱ ድርጅቶች እንዳሉ ሰምቻለሁ። እነኚህ ድርጅቶች፤ ለእውነትና ለወገን ከቆሙና “ፓርቲዛን ካልሆኑ” ገብረመድህን እስከዛሬ በክብር እንዲኖር የረዱትን ከላይ የጠቀስኳቸው ለሌሎች አርአያ መሆን የሚችሉትን ታላላቅ ኢትዮጵያዊያን፣ ወደ አውስትራሊያ  ደውለው በማነጋገር ተገቢውን ክብር እንዲያገኙ ማድረግ አግባብና አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁና ከድርጅቶቹ ጋር ግንኙነት ያላችሁ ሰዎች ጥቆማዬን እንድታደርሱልኝ እጠይቃለሁ።

    በመጨረሻም በሚኖርበት ከተማ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አድናቂዎቹ “ዳግማዊ አሉላ የሚል ታላቅ የክብር ስም ከሽልማት ጋር ለሰጡት ለታላቁ ወዳጄ ለአርበኛው ለገብረመድህን አርአያ፣ ለበጎ አድራጊዎቹ ወዳጆቹና አጋሮቹ ከነቤተሰቦቻቸው፣ በተለያየ ጊዜ ከገብረመድህን ጎን ለቆማችሁ፣ ነገር ግን ስማችሁን ስላላወቅኩ በጽሁፌ ላይ ያልጠቀስኩዋችሁ በጎ አድራጊዎች፣ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ መልካም የ2017 ዓ.ም አዲስ ዓመትና መልካም የቅዱስ ዮሐንስ በዓል ይሆንላችሁ ዘንድ እመኛለሁ።

    ጌታቸው ረዳ 

Ethiopian Semay ዋና አዘጋጅ

 

Wednesday, September 4, 2024

የነቀዘው አዲስ አበቤና 49 አመት ከፋሺሰቶቹ ጋር ፍቅር የወደቀው የትግራይ ሕዝብ የሚነቃው መች ይሆን? ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 9/4/2004

 

የነቀዘው አዲስ አበቤና 49 አመት ከፋሺሰቶቹ ጋር ፍቅር የወደቀው የትግራይ ሕዝብ  የሚነቃው መች ይሆን?

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay 9/4/2004

ሰላም ለሁላቸሁ ይሁን።

ከፎቶይ የሚታዩት አካልዋን ያጣች የወያኔ ወጣት ታጋይና ከታች ደግሞ የበሰበሱት የአዲስ አበባና የክ/ሃገሮች  የአብይ ወጣት ደጋፊዎች ፎቶ ነው፡

እህልና ሰው አንድ ነው። እንስሳ ብቻ ነው በባሕሪ ስለሚለይ የማይነቅዝና የማይበላሽ። እህል ሲበላሽ በሰበሰ ወይንም ነቀዘ እንለዋለን። እህልን የሚያነቅዘው ነቀዝ (በትግርኛው ነቐዝ) የተባለ ከእህሉ ጋር ተደባልቆ የሚኖር ተባይ ሊሆን ይችላል ፤ እህልን የሚያነቅዝ ሌላው ምክንያት አየር ሳያገኝ ታፍኖ የቆየ እህል ወይንም የአየር ጠባይ ነው። ሕብረተሰብም ልክ እንደ እህል ይበሰብሳል የነቅዛል! አዎ።

ሕብረተሰብንስ የሚያነቅዘው ምንድነው? መጥፎ መሪ እና መጥፎ ሥርዓት። እነዚህም የሕብረተሰብ ተውሳኮች/ተባዮች ናቸው።

ዛሬ ያላንዳች መሸፋፈን ልክ ካሁን 28 ዓመት በፊት ይህ ሕብረተሰብ የተነበረከከ ፤ሽንፈት የተቀበለ ሕበረተሰብ ነው፡ ብዬ ስልሕብረተሰብ እየዘለፍክ ነውተብዬ እንደተጨሆብኝ ሁሉ ዛሬም በድጋሚ እንድትጮሁብኝ ለመጋበዝ ሳይሆን ላመስታወስ ነው።

ትዝ ይላችሁ እንደሆነ በግልጽ አማርኛ  በውጭ ያለውም ሆነ በውስጥ  ያለው ሕብረተሰባችን ከመበስበስ ባሻገር እርከኑን ተሻግሮ እንግሊዞቹ እንደሚሉትሯትን/ሮትን” (Rotten) እንደሚሉት በስብሶ/ ነቅዞ/ ረጥቦ/ የጠላት ባንዴራ እየተሸከመ በየአደባባዩ ይንከላወት እንደነበር  ታስታውሳላችሁ (የቅርብ ትዝታ ነውናብዙዎቻችሁ የተካፈላችሁበት ክስተት ነበርና)። ይህ ባሕሪ እኛ ትግሬዎችእጋል” “የገማ/ የጠነባ እንቁላል ወይንም የሚገማ ውሃእንደምንለው ዓይነት ነበር ወቅቱ።

 ረዢም ጊዜ ሳይንቀሳቀስ እንስራ ውስጥ የኖረ ውሃም ሆኖ ነፋስ እየመታውም የሚሸት የኩሬ ውሃ አጋጥሟችሁ ያውቃል? የአገሪቷ ርዕሰ ከተማ ኗሪ ወጣት ተነስ ተብሎ ፤ ለማነሳሳት እየታሰ ተደብድበው ተሰቃይተው በግብር ያሳዩትን እነ ታላቁ እስክንድር ነጋን  ከድቶ የፈረንጅ “ዩ ትዩብ - ፕራንክ” ቀልድ እየተጫወተ በራሱ ላይ ሲያሾፍ የሚውል ከንቱ ትውልድ ሆኗል።

  ያዲስ አበባ ሕብረተሰብ ወጣትና ምሁር በስብሷል። ሕብረተሰብ ሲበሰብስ አፍንጫን አይደለም የሚሰነፍጠው የታዛቢን ዓይንና ሕሊናን ጭምር ያሸማቅቃል። በቅርቡ እያየነው ያለው ዘገባ የመንግሥት ተብየውም ሆነ ሃብታሞች ያቋቋሙዋቸው በመዲናዋ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ከፍተኛ የትምሕርት ተቋማት (ዩኒቨርሲቲዎች) ለሚቀጥርዋቸው ሠራተኞችም ሆኑ አስተማሪዎች ደሞዝ በመከልከል ቤተሰቦቻቸው እንዲሰቃዩ በማድረግ በረንዳ አዳሪ በማድረግ የነቀዙ ቱጃሮች የድሃው ሠራተኛ ወዝ የሚበዘብዙ አረመኔ ባለሃብቶች የሚንደላቁባት ከተማ ሆናለች።

አዲስ አበቤው በአመዛኙ ከትንሽ እስከ ትልቅ በተለያዩ መገለጫዎች በስብሷል። አዲስ አባቤው ብቻ ሳይሆን በብዙዎቹ ክፍለሃገሮች ያለው ሕብረተሰቡ ከነባሩ ጨዋ ማሕበረሰብ ባሕል ወጥቶ  ሂደቱና ባሕሪው በመለወጥ ራሱን ወደ ሞት ሂደት ሲያሸጋግር ይታያል።ራሱን የበሰበሰ “ግኡዝ ሕብረተሰብ” ለማነቃቃት ብዙ መስዋእት ቢደረግም አልሆነም።

የበሰበሱ መሪዎች የበሰበሰውን ሕብረተሰብ ለመስለብ እንዲያመቻቸው ሕብረተሰቡን ለ36 አመት በማበስበስ ኢላማቸውን አሳክተዋል። መሪዎች ያንን ካላደረጉየሚጫኝ አህያ አይሆንላቸውም። ልክ ግምበኞች / የሕንጻ መሃንዲሶች አልፈርስም ብሎነክሶጠንክሮ  የየዘ መሰረት (ቤዝ)  እምቢ ሲላቸው “ውሃእያፈሰሱ፤ እንዲረጥብ እያለሳለሱ እንደሚያፈርሱት ጠንካራ መሰረት ሁሉ ጠንካራ ሕብረተሰብንም ለማበስበስ” የተለያዩ ዘዴዎች በማስተዋወቅ እንደ ዋለሃ (ዋልካ) ተፍረክርኮሊጥ ሆኖ  እስከሚታጠፍላቸው ድረስሃይለኛ ስራ ይሰራሉ። የሚታጠፍ ነገርጥንካሬ ስለሌለው  ሃይልያጣል።የሚታጠፍ ሰው ስብእናውና ሞራሉ ደካማ ስለሆነ የበታችነት ስሜት ተሰምቶት ልጠፍህ ለሚለው ክፍል ሁሉ በቀላሉ ይታጠፍለታል።ተስፋ የሚባል ትርጉም የገባው ከሆነም፤ ምህረቱና ተስፋው በዛው ክፍል ይጥላል።ያችን የተነጠቀውን ተስፋውና ሰብእናው ለማግኘት በራሱ መቆም ስላልቻለ ሰላቢዎች ወደ ጠመዘዙት ለመጠምዘዝ ምቹ ሆኖ ይገኛል። ያንን ግብ ለማሳካት ሥልጣኑን የያዙት ቡድኖች ኢትዮጵያን በነገድ (በቋንቋ) ለይተው እንዲከለል ስላደረጉት፤ ባንድነት መቆም ስለማይችል እርስበርስ እየተባላ መሪዎቹ ምቹ ስለሆነባቸው ማሕበረሰቡን ወደ ፈለጉት ማዞር ችለዋል። አሁን የቀሩን የተበላሹ የትግራይና የአዲስ አባባ ወገኖቻችን አብይንና ወያኔዎችን እያሞገሱና እየተከተሉዋቸው ያለው ባሕሪ በተጠቀሰው ዘዴ ምክንያት ነው (እስተክሆልም ሲንድሮም)።

ታስታውሱ እንደሆነ የአምሓራን ሕብረተሰብ ተነስ እያልኩ ስቀሰቅስ የነበረው ብዙ ትዕግስትና መተጣጠፍ ሲያሳይ ስለነበር ነው።

  አዲስ አበቤው በእስክንደርና በጥቂት መሰል አርበኞች መሪነት ጥይት ከያዘ ኦነጋዊ ፖሊስ ጋር ሲታገል የነበረው አመርቂ የምኒልክ ጀግንነቱን ሲያሳየን የነበረው ወጣት ዛሬ አማራ በተነሳበት ወቅት ውሃ ውስጥ የገባ አይጥ መሰሉ በከባድ የምጣኔ ሃብትና የፍትሕ እጦት እየተሰቃየ እያለ ፀጥታን መምረጡ ይገርማል። ብዙ የአማራ ምሁር አማራ በመሆናቸው ብቻ በኦነጋዊው ፖሊስና በኦነጋዊው ፍትሕ እያተፈሱ ሲታጎሩ ሲራቡና ሲደበደቡ አይቶ እንዳላየ “ዳንኪራ እየመታ ነው” (ልክ እንደ ቀይ ሽብሩ ዘመን)።በዘመናችን ግፍ ሲፈጸም በግሃድ ወያኔምም ሆነ ደርግ ተፋልመናል።

አዲስ አበቤው ብቻ ሳይሆን እኔ ከተወለድኩበት የትግራይ ማሕበረሰብም ቢሆንነከሱት የፋሺሰት ጅቦች ጋር አብሮ መኖር ለምዶታል።ከመልመዱ የተነሳ የመውደድ አባዜው ዛሬም ብሶበት  ሲጨፍርና ባንዴራቸውን ለብሶ ፎቶ ሲነሳ እያየን ነው። ኩፉኛ 49 አመት ድፍንፈጣጣ ፍቅር !! ዛሬም አልለቀቀውም (ኢትዮጵያ የምታቀርብለትን ፍጆታ እየተጠቀመም ቢሆንየሃገረ ትግራይ ምስረታው ቅዠት አልለቀቀውም)።ስለጠነቡትየትግራይ ምሁራኖች ማውሳት ቆሽት ማሳረር ስለሚሆን አልነካካውም።

የትግራይ ነገር ሳነሳሐረርውስጥ ማታ ማታ ሲመሽ ጅቦች የሚቀልቡ ፡አድቨንቸሪስቶች” (ጀብደኞች) አሉ። ይህ ጉደኛ ትዕይንት የትግራይ ሕዝብ ባሕሪ እና የወያኔ ግንኙነት ታሪክ ጋር ይመሳሰልብኛል። ዛሬ ዛሬ ከመቸውም በበለጠ ሐረር” ውስጥ ማታ ማታ ሲመሽ ጅቦች የሚቀልቡ ፡አድቨንቸሪስቶች” (ጀብደኞችየጐብኚዎች መስህብ እየሆነ በካሜራ እየተቀረጸ መጥቷል። ቀላቢውም ሆነ ተመልካቹ  የሳቱት ነገር ቢኖር ጅቦቹ የቀላቢውም ሆነ የተመልካቹ ህይወትቀሳፊዎችእና ተቀናቃኞች መሆናቸው የመገንዘብ ሕሊናቸውበጊዜያዊ የመጠጋጋት የጀብደኝነት እርካታውስጥ ገብቶ ስለተማረከ፡ ከመጋቢያቸው እያሽካኩ በጓደኝነት ባሕሪ  ሥጋ እየተሰጣቸው የሚመገቡትጅቦችቀላቢ ሲያጡየገዛ ቀላቢያቸውን እንደሚበሉት ቀላቢዎቹ የተረዱት አይመስሉም።

ጅቦቹ ከቀላቢያቸው የሚፈልጉት ነገር ቢኖርመመገብነው። ቀላቢዎቹ ከጅቦቹ የሚፈልጉት ነገር ደግሞ ጀብደኛነትን ለዓለም ለማሳየትና እግረመንገድም መናከሳችሁንአቁሙ ነው። የመጠጋጋቱ የጨዋታው ትርጉም ሲመረመር ከዚህ  ያለፈ አይሆንም። መጋቢዎቹ የዘነጉት ጉዳይ ሰንጋ ቢታረድላቸውም ልጆቻችንና ከብቶቻችንን መናከስና መብላታችሁን አቁሙ ስለተባሉጅቦቹመናከሳቸውን ያቆማሉ ወይ?” ነው ጥያቄው።

የሁለቱ ፍጡራን ትካት (ኢንስቲንክት) የጭምትነት ባሕሪ የጎደላቸው ስለሆኑነካሹም” “ተነካሹምየተፈጥሮ ባሕሪያቸው እንደማይገጥም እያወቁ ሁለቱም እየተጠጋጉ እናፈራ ተባእያሉ በማያዛልቅ ጨዋታ ገብተውየበይ እና የተበይየመገዳደል ጨዋታቸው እያሳመሩ ጅቦቹ ከጀብደኛ ቀላቢያቸው አፍ ጥርስ ተነክሶ የተንጠለጠለላቸው ስጋጠጋብለው በመንጠቅ ይጎርሳሉ። ይህ አስገራሚ የገዳይና የተገዳይ ጀብደኛ ጨዋታ በካሜራ ተቀርጾ ለዓለም ሕዝብ እየታየ ነው።የትግራይ ሕብረተሰብም ባሁኑ ሰዓት  ከ1.2 ሚሊዮን የትግራይ ወጣት ተዋጊ በጦርነቱ ሲሰዋ የተቀረውም “ቱራማታይዝድ” የሆነ በስቃይ የሚኖር ማሕበረሰብ ሆኖ ለዚህ ሲኦላዊ ሕይወት ከዳረጉት መሪዎቹ ጋር በመጓዝ  ከሚበሉትና ከሚያስበሉት የሰው ገላ ከለበሱ  አራዊቶች ጋር” ተጠጋግቶ በበይና በተበይ የጨዋታ ሕግጋት አስገብተው እየበሉት እንደሆነም እያወቀ 49 አመት ካለ ሞት በቀር ምንም ካልረቡት  አራዊቶች ጋር ፍቅር ይዞት ሲያሞግስና ሲጨፍር ማየት በሽታው በቃላት ለማስረዳት ይቸግራል

አጼ ዮሐንስ ሲያውለበልቡዋት የነበሩት  ዓለም ያወቃት ባለ ሦስት ቀለማት ሰንደቃላማች ማውለብለብ ትግራይ ውስጥ “ሕገ ወጥተደርጎ ስለታወጀ፤ በምትኳ የአራዊቶቹን ባንዴራ ለብሶ እያውለበለበ በመታየት በትግራይ ነገሥታት ሰንደቅአላማ ላይ ተሳልቋል። የትግራይ ሕዝብ መበስበስ የሕገ ወጥ  ቡድን ተባባሪ መሆን ዋጋው እያስከፈለው ቢሆንም አሁንም ወደ እማያውቀው ወደ “ፋንታሲ” ዓለም መጓዙን ቀጥሎበታል። የትግራይ ሕብረተሰብ በመበስበሱ ሕገ ወጥ ተግባሮችን ሞትን እርዛትን ግንጠላን አገር ማንኳሰስን ሕጋዊ አድርጎ  ተቀብሏል ማሰብ ያቆመው የትግራይ ሕዝብ ወንጀለኞቹ በዘረጉለት ሃዲድ መጓዙን ስለመረጠሞራል ፕርንሲፕልበመጣስላገር ታማኝነት” መሆኑን አቁሟል። ምልክት በሌለው ባጭበርባሪ ጎዳና የሚጓዝ ተጓዥ ለአደጋ እንደሚጋለጥ ሁሉ፤ይህ ሕብረተሰብ ለከፋ የሞራል መበስበስ መጋለጡ ዛሬም አላቆመም።

እነ ኢዛና ፤ አምደጽዮን ፤ ቴዎድሮስ ፤ ዮሐንስ፤ ምንሊክ እና  ተፈሪ እየኖሩበት ያለውን ሰፊ አገር ሲመሰርቱ ያችን ሰንደቃላማ ይዘው ነበር ታሪክ የሰሩ። ሆኖም ዛሬ በነዚህ ኩታራዎች ብልግና ሰንደቅአለማቸው ወደ አፈር ሲጣል እና ሲረገጥ ቢያዩ ምንኛ ባለቀሱ!?

ዛሬ አዲስ አበቤውና ትግሬው በተመሳሳይ የበሰበሰ ጎዳና እና ትርዕት እየተጓዘ መሆኑን ስንታዘብ ያሳዝናል።

ካነበብኩት አንድ መጽሐፍ ውስጥ 1500 አመት በፊት የሮም መሪዎች በመበስበሳቸው ለታላቋ የሮም መንግሥት መበታተን ምክንያት እንደሆነ አንብቤአለሁ። የበሰበሱ መሪዎች አገር ሲመሩ የበሰበሰ ሕበረተሰብ ያፈራሉ። አገር ባይፈርስም በውስጧ የታቀፈው ሕብረተሰብ አቅፈውት ሲጓዙ የነበሩት ተቋማት (ሰትራክቸሮቹ) ስለሚፈርሱ የሕሊና መፍረስ ስለሚገጥመው ባስተሳሰቡ መካን እና የበሰበሰ ማሕበረሰብ ይሆናል ማለት ነው።

ዛሬም የበሰበሰና የነቃ መሕበረሰብ ሚናው እየለየ መጥጧል።   ፍትሕለሚጠይቁ ፋኖዎች ሲያናንቁት የነበረው እነሆ ዛሬ አጥራቸው ውስጥ ብቅ ሲል ባንዳዎች ሌሊቱንም ሆነ ቀትር መተኛት አልቻሉም። ወንበራቸው በፋኖ ተነጥቆ ፋኖዎች ተቀምጠውበታል (እሰየው!!) አሳምነው ጽጌ ምነው ብቅ ባልክና ፍሬሕን ባየህ!?

ትግሉ አብይ እስኪወገድ መቀጠል አለበት።እንቅስቃሴውእንዳይጠለፍ ሕዝብ ነቅቶ መከታተል የዜጎች ግዴታ ነው እያልኩ ለአመታት የምጮኩበትን የትጥቅ ትግል አማራው ተግባራዊ ማድረጉ ቅቤ አጠጥታችሁኛል። በሃገረ ትግራይ ሥካር ተመርዞ ሃገረ ትግራይ ወደ እሚላት ሃገረ ጽልመት እየተጓዘ ያለው 49 አመት ከፋሺሰቶቹ ጋር በፍቅር የወደቀው የትግራይ ሕዝብና አዲስ አበቤውስ መች ይሆን የሚነሱት

ጌታቸው ረዳ