Friday, September 27, 2019

ስደንጋጭ ሚስጥራዊ መረጃ፦ በህወሓቱ ጌታቸው ረዳ እና በግብፁ የደህንነት ኃላፊ የተዘጋጀው ፕሮፖዛል! (ስዩም ተሾመ) September 27, 2019 (posted -Ethio Semay)


አስደንጋጭ ሚስጥራዊ መረጃ፦ በህወሓቱ ጌታቸው ረዳ እና በግብፁ የደህንነት ኃላፊ የተዘጋጀው ፕሮፖዛል! (ስዩም ተሾመ)
September 27, 2019 (posted -Ethio Semay)
The mercenary TPLF fool Getachew Reda conspiring with Ethiopia's enemies with the Arabs and Egypt in particular


The mercenary TPLF fool Getachew Reda conspiring with Ethiopia's enemies with the Arabs and Egypt in particular

በምስሉ ላይ የሚታዩት አራት ሰዎች ስም፤ ከግራ ወደ ቀኝ፡-

1- የግብፅ ደህንነት መስሪያ ቤት ኃላፊ ካሊድ ፋውዚ (khalid Fawzy)

2- ፍልስጤማዊው መሃመድ ዳህላን (Mohammed Dahlan)

3- ለግዜው ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ፣

4- የህወሓት ሥራ አስፈፃሚ አባል የሆነው አቶ  ጌታቸው ረዳ ካሕሳይ ናቸው።

መሃመድ ዳህላን የግብፅ ድህንነት መስሪያ ቤት ቅጥረኛ ሲሆን ነዋሪነቱን በተባበሩት አረብ ኢሜሬት ነው። ይህ ግለሰብ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በነበረበት ወቅት አደራዳሪ መስሎ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ነበር። በዚህ አጋጣሚ ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የፈጠሩት ወዳጅነት ከዱባይ ከተማ እስከ ካሪቢያን ደሴቶች ድረስ ለሽርሽር እስከመሄድ አድርሷቸዋል። በሁለቱ መካከል ያለው ወዳጅነት ከራሳቸው አልፎ በምስሉ ላይ ከምታዩት የግብጹ ደህንነት ኃላፊ ካሊድ ፋውዚ (khalid Fawzy) ጋር ወዳጅነት እንዲመሰርቱ አስችሏቸዋል። የአራቱ ሰዎች ምስል ያለበት ፎቶ የተነሳው እዚሁ አዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ ውስጥ ነው። …….

…..ከጥንት ዘመን ጀምሮ አንድ ያልተቀየረ የግብፃዊያን ታሪክ ቢኖር ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር ያደረጉት ሙከራ በሙሉ በሽንፈት መጠናቀቁ ነው። ህወሓቶች ከግብፃዊያን ጋር በመመሳጠር የኢትዮጵያን ጥቅምና ሉዓላዊነት የሚፃረር ፕሮፖዛል ማዘጋጀታቸው ግን ሀገርን ከመሸጥ ተለይቶ አይታይም። በተለይ የህወሓት/ኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆነው አቶ ጌታቸው ረዳ ከውጪ ሀገር ደህንነት ኃላፊዎች ጋር በመመሳጠር ለፈጸመው አሳፋሪ ድርጊት በሀገር ክህደት ሊጠየቅ ይገባል።(ስዩም ተሾመ)

No comments: