Monday, November 27, 2023

በዕብሪታቸው ለውርደት የተዳረጉት በ5000 ዘመናችን ታይቶ የማያውቅ የትግራይ ፋሺሰቶች አስደማሚው መጨረሻቸው The Fascists of Tigray, who were humiliated by their arrogance, have never been seen in 5000 years. ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 11/27/2023

 

በዕብሪታቸው ለውርደት የተዳረጉት በ5000 ዘመናችን ታይቶ የማያውቅ የትግራይ ፋሺሰቶች አስደማሚው መጨረሻቸው

The Fascists of Tigray, who were humiliated by their arrogance, have never been seen in 5000 years of our history

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

11/27/2023

ፋሺስቶች ዕብሪተኞች ናቸው ፤በዛው ልክ አወዳደቃቸው አያምርም። ጣሊያኖች የሞሶሊኒ የመጨረሻው ውድቀቱ “ሓምሌ 5” ብለው ይጠሩታል። የትግሬ ፋሺሰት መሪዎች መጨረሻ ኢትዮጵያውያን ምን ብለው እንደሚጠሩት እስካሁን ድረስ ስም አልሰጡትም። ሁለተኛ ዙር ስለሚኖር እስከዛው እንታገስ።

 ትግሬዎች ኢትዮጵያን ከመጥላታቸው የተነሳ ቅኝ ገዢዎችን ያንበረከከች ገናናዋ ኢትዮጵያን 27 አመት በአፓርታይድ አስተዳዳር አምበርክከው ግጠው አዋርደው ባህልዋን እንዲበላሽ አድርገው ፤ ሁሉም ስለ ወያኔ ትግሬ እንዲዘምር አስገድደው ፤ ባሕር በርዋን ዘግተው አሁን ላላው ተረኛ ኦሮሙማው ቡድን አስረክበው ወደ ትግራ ሸሹ።

በዕብሪት ተወጥረው ስለነበር፡ የትግራይን ሕዝብ ህይወት ሲጠብቅና\ በገንዘብና በሞራል ሲረዳ የነበረው የሰሜን ዕዝ ሲባል የነበረው 70% ቱ የኢትዮጵያ ወታደር በተለያዩ ማዘናጊያ ሴራ አዘናግተው በመጨፍጨፍ “ጀነሳይዳል ወንጀል” ፈጽመው ወደ ትግራይ በረሃዎች ሸሽተው እነሆ በዚህ ቪዲዮ እንደምታዩት በታሪካችን አይተነው የማይታወቅ ልብ ወለድ የሚመስል ግን እውነተኛ የውርደት ትዕይንት እንድናይ ሆነ።

ወያኔዎች ዕብሪተኞች ናቸው። ዕብሪቱ ወደ ሕዝቡም ተሻግሮ ለነሱም ለአማራዎችና አፋሮችም ጭምር ችግር አምጥቷል። ወያኔዎች ብዙ ነውር ፈጽመዋል። ነውርን ለመግለጽ እና ለመለካት በጣም ከባድ ቢሆንም ፤ነውራቸው ሞልቶ የፈሰሰ ነው። እንደ ኢንጂኔር እምብዛ ታደስ እንዳይሆኑ ከወያኔ ሰይፍ ሸሽተው አዲስ አበባና በየቦታው ያሉት ጥቂት ኢትዮጵያውያን ትግሬዎችን አይመለከትም።

በዚህ ቪዲዮ የምትመለከቱት የተማረኩት የወያኔ መሪዎችና ቁልፍ አባሎቻቸው ሲያዙ  ውጭ አገር በምቾት ግፋ በለው ሲሉ የነበሩት ምን ተሰምቷችሁ ነበር እናውቃለን። ውጭ አገር በምቾት የሚኖሩ የትግሬ ምሁራን ውርደትን እንደ አሸናፊነት አድርገው ሲስሉት ሰምተናል።  ከነሱ ይልቅ እኛ ለነሱ አፈርንላቸው።  ይህንን ውርደት ከማረም ይለቅ ዛሬም “በቅልጥማችን” የሚሉ ምሁራኖቻቻው እየገኑ መጥተዋል። ይህንን ለማድመጥ “ዩ ኤም ዲ“  እየተባለ የሚጠራው ካናዳ ያለው ፕሮፌሰር ጌታቸው አሰፋ የሚያዘጋጀው ሚዲያ እየተጋበዙ የሚያቀርቧቸው እንግዶቹ የሕክምና ዶክተሮች ሳይቀሩ የሚሰነዝርዋቸው አደገኛ አገር አፍራሽ ንግግሮች ለሁለተኛ ዙር ውርደት የሚጋብዙ ናቸው።

 “በጡንጫችን መተማመን አለበን” ይላሉ። ዛሬም ትንናትም መፈክራቸው ‘ጡንቻ ነው”።  << ወይ አማራው ወይ እኛ አንደኛችን መጥፋት አለብን፤ካልሆነ መኖር አንችልም>> እያሉ  ሳደምጥ የትግራይ ሕዝብ መጻኢ ዕድል የለመለመች አገረ ትግራይ ለመመስረት <<አማራ መጥፋት አለበት>> የሚለው ይዘውት ከመጡት የወያኔ ማኒፌስቶ ዛሬም ህያው ነው።

ይህ ዕብሪት የትግራይን ማሕበረሰብ ለሁለተኛ ዙር መከራ እያጠመዱለት መሆኑን ሳደምጣቸው እኔን የሚያስጨንቀኝ ነገር ሆኖ አግኝቸዋለሁ። በነዚህ ዕብሪተኞች ዕብሪት የተነሳ በዚህ ጦርነ ብቻ ሁለት ቤተሰብ አጥቻለሁ። የነዚህ ምሁራን ትግሬዎች ውይይት ሳደምጥ “እኛም በድለናል ሳይሆን ሁሌም 500 አመት ወደ ሗላ በመሄድ ተበድለናል የሚል ማቆሚያ የታጣለት “የቪክቲማይዘሽን” ትርክት ዛሬም ያለ ነውር ቀጥለውበታል።

 ፋሺሰቶች ውርደትንና ሞትን ምን ያህል እንደሚደፍሩት ይገርመኛል፤፡ “ዩ ኤም ዲ የተባለው ሚዲያ አድምጡ: ብዙ አክራሪ ትግሬዎችና ኦነጐችን ታደምጣላችሁ“። ባለፈው ሰሞን ድንገት ዩ ቲብ ገብቼ ሳደምጥ ዶ/ር ገብረሚካል ገ/መስቀል (ሓኪም ውጭ አገር የሚኖር) ሃይሉ ከበደ (ትግራይ ውስጥ የሚኖር- በጣም አደገኛ ጽንፈኛ ጸረ አማራ- << አንደኛችን መጥፋት አለብን>> የሚለው) ፤ ክብሮም በርሃ የታላቅዋ ትግራይ (ባይቶና ፓርቲ መሪ) እና ወደ ላ ተመልካች ጸረ ምኒሊክና አማራ ጸረ ኢትዮጵያ ፋሺሰት ቀውሰኛ ተገንጣይ) እንዲሁም ውጭ አገር የሚኖር በጸረ አማራነቱ የታወቀው ድሬዳዋ ያደገው አድዋዊው መርስኤ ኪዳነ (ለግንጠላ የሚሰራ ፋሺሰት)። እነዚህ ሁሉ ሳደምጥ በዚህ ቪዲዮ ያየነው የዘመናችን ዕብሪትና ውጤቱ እንደገና ከአሁን በኋላ እንዳይከሰት እሰጋለሃለሁ።

  ትግራይ ውስጥ ሁለት የማያባራ ግጭት ይካሄዳል ፡ <<እርስ በርስ>> (የኛ የትግሬዎች  ዝንተ ባሕሪ <ዕብሪት> ባሕላችን ስለሆነ)።  እንዲሁም ታላቅዋን ትግራይ ለመመስረት የሚከሰት አደገኛ ጦርነት። በተለይ የለኛው ግጭት እውን የሚሆነው ተገንጣይ ክንፎች፧ በሕግ እንዲንቀሳቀሱ አብይ አሕመድ ሆን ብሎ ስለፈቀደላቸው እንቅስቃሴው ያንን ዕድል፣በመጠቀም ወደ ዘንዶነት አድገው ከፍተኛ ብጥብጥ ያመጣሉ። ይህ የሚከሰተው ወልቃይትና ራያ ለመንጠቅ በሚያደርጉት ጦርነት ይሆናል።ቦታውም የፈለጉት ለግንጣላ አላማ ስለሆነ::

ይህንን ስገነዘብ በውጭም በውስጥም ያሉት ተገንጣይ ትግሬዎች አብይ አሕመድ እየሰጣቸው ያለው <<ኦክሲጅን>> በመጠቀም ሁለተኛ ዙር የዕብሪት፤ የዕልቂትና የሓፍረት ትዕይንት እየመጣ እንደሆነ ይታየኛል

በዕብሪታቸው ለውርደት የተዳረጉት በ5000 ዘመናችን ታይቶ የማያውቅ የትግራይ ፋሺሰቶች አስደማሚው መጨረሻ ይደገም ይሆን?

ጌታቸው ረዳ  - የሚከተለው ቪዲዮ ይመልከቱ



 

 

Wednesday, November 22, 2023

ሁለቱ ቴድሮሶች በአቡነ ኤርሚያሰ ያነጣጠሩት ወገንተኛ ትችት ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 11/12/23

 

ሁለቱ ድሮሶች በአቡነ ርሚያሰ ያነጣጠሩት ወገንተኛ ትችት

ታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

11/12/23

አቡነ ኤርሚያስ በወሎ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተወካይ ናቸው። አቡኑ የላሊበላ ወይንም የላስታ ማሕበረሰብ (?) ስብሰባ ተገኝተው የተናገሩት ሃይማኖታዊም ይሁን ማሕበራዊና ፖለቲካዊ ነክ ባንዳንድ ሃያሲያን ሲተቹ ባንዳንዱም ተቀባይነት አግኝተው አለፍ ብሎም የተናገሩት ንግግር ስላልጣማቸው “ይቅርታ እንዲጠይቁ” ጋብዘዋቸው አስተያየታቸው ሰጥተዋል። በዚህ ትችቴ ውስጥ አቡኑ ስለተናገሩት ንግግር የሚያተኩር አይደለም። ምክንያቱም ከመጠን በላይ ትኩረት አግኝቶ መነጋገሪያ ሆኗል። ሳልተች የማላልፈውና ያበሳጨኝ ትዝብት ግን በፎቶግራፉ ላይ የሚታዩት በሁለቱ ቴድሮስች ላይ ነው።

ቴድሮስ ፀጋዬ (ርዕዮት ሚዲያ አዘጋጅ) እና ቴድሮስ አስፋው በሥርዓቱ ተሰድዶ በቅርቡ ወደ ውጭ አገር የተሰደደ ጋዜጠኛ አብረው በአቡኑ ላይ የሰነዘሩት ውርጅብኝ እጅግ ከማስደመም በላይ ወገንተኛነታቸው ፀያፍ መሆኑን ሳልቃወም ላልፋቸው አላልፍም።

ሁለቱ በትግራይ ሁኔታ የሚያላዝኑ ጋዜጠኞች ናቸው። የማላዘናቸው መነሻ ደግሞ በደምብ በሚባል ወያኔዎችና ቱልቱላዎቻቸው የልብ ልብ ሰጥቶአቸዋል። ብዙዎቻችሁ እንደምታውቁኝ ስለ ትግራዩ ጦርነት ሲነሳ ከነዚህ ሁለት ጋዜጠኞች ብዙ የተራራቀ ልዩነት እንደለኝ ታውቃለካችሁ ብየ እገምታለሁ። ቴድሮስ ፀጋየ እና እኔ የትግራይ ተወላጆች ነን። ቴድሮሰ አስፋው ነገዱን አላውቅም። ጎበዝ ጋዜጠኛ ቢሆንም ከጭንቅላቱ ባለይ ለመፍንዳት የሚሞክር ከወያኔ ቱልትላዎች እኩል በሚያስመስልበት መልኩ በተዘዋዋሪ አዳማቂ ነው።

ያ ባይሆን ኖሮ እነዚህ ሁለት ጋዜጠኞች አማራ የተባሉ ቀሳውስትና ጳጳሳት በተናገሩ ቁጥር እንደ “ደሮ” እያንዳንዷን ቃላት እየለቁሙ ለወራትና ለሰዓታት ለትችት አቅርበው ሲተለትሉዋቸው ስናደምጥ እጅግ ዘረኛ ንግግርና የዘር ማጥፋት ቅስቀሳ የሚናገሩ የትግራይ ቀሳውስትና ጳጳሳትና ፖለቲከኞች ላይ ሲደርሱ ግን ምላሳቸው የተሸበበ ነው። ጥያቄው ለምን? የወያኔ ትግሬዎች ቱልትላነት ካልሆነ ሌላ መጠሪያ ካለው ላድምጣችሁ።

  “ሃይማኖትና ፖለቲካ” ተዋህደው ፖለቲካው ሃይማኖትን የሚመራው” ሆኖ እያየን ነው። ይህ ግልጽ ነው። በተለየ እና በሚታይ መልኩ “ትግራይ እና ኦሮሚያ” አብያተ ክርስቲያናትና እስልምና ዕምነት ተቋማት ሁሉ በሚዋሹ ቀሳውስትና ሼኮች እየተመሩ ናቸው። ዝርዝር አልገባም (ብዙ ስለተባለለት)። ምዕመኑ “ነገዳውያን ቀሳውስትን” በመከተል የራሱን ሃይማኖቱን በማርከስ ላይ እንደሆነ እያየን ነው።

ቴድሮስ ጸጋዬን ስንመለከት አማራ ጳጳሳት ወይንም ቀሳወስት ላይ ሲደርስ በራሱ ነገድ ቀሳውስት ላይ ሲደርስ እፅ እንዳጨሰ ሰው አነገቱን ደፍቶ ለመናገር ይደበራል። ትናንት አቡነ ኤርሚያስ ላይ ከቴድሮስ አስፋው ሆነው ሰፊ ፕሮግራም ሰርተው አረፋቸው እስኪደፍቅ ቃላት እስከሚያጥራቸው ድረስ አቡኑን እንደ ወረቀት ሲቀዳድድዋቸው ነበር የዋሉት። ምክንያቱም ተብሎ ቢጠየቅ አማራ በመሆናቸው ወደ እሚል ድምዳሜ እንደርሳለን። ምክንያታዩም ሁለቱም ቴድሮሶች እኔ እስካደመጥኳቸው ድረስ በትግራይ ቀሳውስት ላይ ለዘብተኛዎች ብቻ ሳይሆን ዝምተኛዎች ነበሩ።

ለምሳሌ፤

ካሁን በፊት ቴድሮስ ጸጋየ ያልከነከነው “የባለጌው” የአውስትራሊያው “ጸረ አማራውና ጸረ ኢትዮጵያ የሠረቀ ብርሃን” <<ሂትለራዊና ሁቱ-ኣዊ>> ንግግሮችን በራሱ ሚዲያ ጋብዞት ምን እንደተነጋገሩ እንመልከት፦

አባ ሠረቀ ብርሃን በአደባባይ የተናገረውን ላስታውሳችሁ፡

እንዲህ ይላልለ፦

<< (አማራ የጠራ ዘር) ስሌለው ከዚያም ከዚያም ተጠራቅሞ የመጣ ዘር ስለሆነ አማራ የሚባል ዘር የለም ! ቢኖርማ ያስብ ነበር። ስለዚህም ነው ፤’የአማራ ሕዝብ ኢትዮጵያ፤ ኢትዮጵያ’ የሚለው። የራሱ የሚባል ዘር የለውም። ከዚህ መጣ ስለማይባል፤ ከትግራይ ከዚያም ከዚያም የተወጣጣ (ስለሆነ) ራሱን ችሎ የመጣ ዘር ስሌለው ‘ሁልጌዜ ሊሸፈን የሚፈልገው ኢትዮጵያ በምትባለው (አገር) ነው’። ለዚህ ነው ሌላ ነገር አይናገርም። ኢትዮጵያዊ ነኝ ብቻ የሚለው።…….

<<………ኦረሞም ኦሮሞኖቱን ይዞ ኢትዮጵያዊ ነው፤ ትግራይም ትግራዋይነቱን ይዞ ኢትዮጵያዊነቱን ይዞ ነው የመጣ፡አማራ ግን አማራነቱን ይዞ ኢትዮጵያዊነት የሚለው ስሌለው፤አማራ የሚባል ዘር ስሌለው፤ ’የሚንጠለጠልበት ዘር ስሌለው’ ኢትዮጵያ በሚለው ተሸፍኖ እየሰራ ስለመጣ “Shame on you! በጣም አፍርባችለሁ።….. >>

<<………..የትግራይ ሕዝብ ሆይ! በትግራይ እየተካሄደ ያለው ጀነሳይድ እነዚህ አካላት ክደውሃል፡ አማራ ክዶሃል! እመነኝ! እመነኝ! አስረግጬ እነግርሃለሁ። ኢትዮጵያ የምትባል ብትከድህም እግዚአብሔር አልካደህም!”>>

ሲል የወያኔው ማሌሊት ባለጌው ቄስ ሰረቀ በርሃን <<አማራ የፀዳ ዘር ሳይሆን ከዚያም ከዚያም የተጠራቀመ ያደፈ የቆሸሸ ደም “የበታች ዘር (ሎው ካስት)” ነው፤ ሲል በግሃድ ሳይደብቅ በዜና ማሰራጭያ “በትግ’ናዚ” አዋጅ”  ሳይሸማቀቅ አስረግጦ (ሃይላይቱን -አድምቆ) ነግሮናል።

ባለጌው የወያኔ ትግራይ ቄስ እንዲህ ሲል የርዕዮት ሚዲያ ቴድሮሰ ጸጋዬ ወደ ፕሮግራሙ ጋብዞ፤ <<ይቅርታ መጠየቅ ካለበዎት የሚሉበት ነገር ካለ ዕድሉን እነሆ>>፡ በማለት አባ ሠረቀ ብርሃንን ጋብዞ ያለ ምንም “ከባድ ጥያቄና ሊቀርቡ የሚገባቸው ሰረቀ ብርሃን የተናገራቸው የቪዲዮ ሰነዶች ሆን ብሎ የሆነች ትንሽ መናኛ የንግግሩ ክፍል በሴለፎኑ ለአድማጮቹ  በማስሰማት እራሱንም አስገምቶ ሠረቀ ብርሃንን እንደልቡ እንዲጋልብ አድርጓል”  ለድፍረቱ ይቅርታም ሆነ ንስሃ መግባት ቀርቶ “አሁንም ያልኩትን በድፍረት እደግመዋለሁ፡ የሚከራከረኝ ካለ ይምጣ” ሲል ዘረኛ ድንቁርናውን ድፍረቱ ታብዮበታል። ከእያንዳንዱ ውሸት በስተጀርባ ለማታለል መነሳሳትን የሚገፋፋ ታላቅ የጣዖት አምልኮ ትግራይ ውስጥ አለ የምለው ለዚህ ነው። ቴድሮስ ይህ ሁሉ ጉድ አድምጦ <<ይቅርታ መጠየቅ ካለበዎት የሚሉበት ነገር ካለ ዕድሉን እነሆ>>በሚል ሸኘው። ይህ የቴድሮስ ፀጋዬ ወገንተኛ ባሕሪው በሰረቀ ብርሃን ብቻ አልተገታም በአሉላ ሰለሞን (የሩዋንዳው -----የትግሬው ካቡጋ) እንዲሁ ደግሞታል።

<< ትግራይና ኢትዮጵያ ምን እና ምን ናቸው? ከዚህ በህዋላስ ወዴት?” በሚል ርዕስ አሉላ ሰለሞን ካሁን በፊት ያወጃቸው የጥላቻ አዋጆቹን አስመልክቶ ወደ ፕሮግራሙ ጋብዞት እንዲያብራራ ጠይቆት አሉላ ለጥያቄው ሲመልስ አዋጆቹን እያጣመመ እንዳሻው ሲመልሳቸው ቴድሮሰ ሆን ብሎ አሉላ በጽሑፍና በድምፅ ያወጃቸው 10ቱ የአሉላ የዘር ቅስቀሳ አዋጅ “ወንጀል” መሆናቸውን እያወቀ ቴድሮስ ከ10ሩ ውስጥ ነጠላ አዋጅዋን ብቻ መዝዞ እንዲያብራራለት ጠይቆት አሉላ እንዲያ እያወላገደ አንዳንዴም እንደ ጀግንነት ቆጥሮት ዘረኛ አዋጁ “ግቡን የመታ ስኬታማ” እንደሆነ በደስታ ሲገልጽለት ቴድሮስ ፀጋየ አሉላን አጥብቆ ላላመጠየቅ እንዲህ ያለ ወንጀል በቸልታ ዝም ብሎ እንዲያላግጥ ለቅቆታል።

ጸረ አማራ ፕሮፓጋንዲስቶች ወደ ቴድሮስ ሚዲያ ሲቀርቡ ቴዎድሮስ ያለወትሮው እንደ ንብ ሲናደፍ የነበረው ምጡቅ ምላሱ “ሆን ብሎ” ሲሸብበው በተደጋጋሚ አይቻለሁ። እንደፈለጉት ሲጋልቡ እያደመጠ ዝም ብሎ “የፈለጉትን ሲያቦኩ” ይለቃቸዋል። እንደ ቴድሮስ የመሰለ የጥያቄና መልስ ልምድ ያለው “ሕግ የተማረ ሰው” እንዲህ ወርዶ ሳየው ምንም እንኳ በተለያየ ጎራ ብንሰለፍም እንዲያ ያለ ምጡቅ ሕሊና ጠውልጎ በትግራይ አክራሪ እቡይነት ተሸብቦ ሳየው አዘንኩኝ።

ቴድሮስ ጸጋዬ የአሉላ ሰለሞንም ሆነ ሠረቀ ብርሃን የቀሰቀሱት ዘረኛ አዋጅ በተነገሩ የዘረኞቹ ነጥቦች ተስማምቶት ካልሆነ በስተቀር ቴድሮስ ባለው የሕግ ዕውቀት አሉላንም ሆነ ባለጌው ቄስ ሠረቀ ብርሃንን  የሚወጥርበት መሟገቻ ፍሬ ነገር ያጣል ብሎ መገመት የዋህነት ነው።

 አሉላ ሰለሞን የደረሳቸው 10ቱ የጥላቻ መመሪያዎች ፈረንጀቹ እንደሚሉት ሕብረተሰባዊ ኑሮን የሚያደፈረስ “የሞት ቲኬት” የሚሉት ነው። ይህ አደገኛ ጥሪ ያወጀው የትግሬው “ ሐሰን ንገዜ” (የሩዋንዳው መንትያ) አሉላ ሰለሞን በሚገርም ሁኔታ ጋዜጠኛ ቴድሮስ ጸጋዬ አቅልሎ ማየቱ አንድ ቀን በዚህ ርዕስ ሰዎች አንስተው በታሪክ ይወያዩበታል።

አሉላ አፍጥጦ ሳያፍር እንዲህ ያለውን ቴድሮስን ያላስገረመው የሰለሞን አባባል ላስታውሳችሁ፤

<< የተጋባችሁ ካላችሁ ተፋቱ፤ ያልተጋባችሁ ካላችሁም አትጋቡ የሚሉ አስተያየቶች ብዙ ለቅስቀሳ ውለው ተመለክቻለሁ። “ጋብቻ”  የምተለዋ ቃል፤ ሰዎች አትኩረዋል፤ ጓደኝነትም ጭምር አንስቻለሁ። ቴድሮስ ቤተሰቦችህ ጭምር ሲሰቃዩ ቤተሰቦችህ ያሉበትን ሁኔታ የማይጠይቅ ጓደኛ ነው ብሎ ተደላድሎ የሚቀጥል ሰው ካለ ልታሳዩኝ ይገባል። ከዚህ ሰው ጋር ወዳጅነት መቀጠል አያስፈልገኝም የማለት መብት አለህ።” እያለ እራሱን ከወንጀል ነጻ ለማድረግ ሲመጻደቅና ሰለሞን ሁሉንም እንዳሻው ለብዙ ደቂቃዎች እንዲዘባርቅ ዝም ብሎ ሲለቀው  ነበር

በታወጀባቸው አማራ ማሕበረሰቦች ህይወትና ጋብቻ ግን ችግር ፈጥሬ ይሆናል የሚል ልብህ ውስጥ አለ ወይ? ብሎ አልጠየቀውም ፤ ቴድሮስ ያሳሰበው በዚህ ተንተርሶ በትግሬዎች ላይ የደረሰው ችግር ብቻ ነበር ትኩረቱና ልቡ! ያውም አዋጁ “ስሕተት” በሚል ቀላል ስሕተት አድርጎ  መሳሉ ይገርማል።

ቴድሮስ ሰለሞንን እንዳሻው እንዲዘባርቅ ከለቀቀው በላ እንዲህ ሲል ደመደመው፤

<<ማድረግ  ከሞራላዊ ከማሕበራዊ ዕይታ አንጻር ነው ጥያቄው የነተነሳው እና ባጭሩ ንገረኝ እና ወደ ሌላ ርዕስ እንገባለን። >> የሚል ረዢም ጊዜ እንዲዘላብድ የለቀቀው አልበቃ ብሎት ባጭሩ ንገረኝ እና ወደ ሌላ ርዕስ እንገባለን። ብሎ ደመደመው።

እንደምታውቁት ቴድሮስ ጸጋዬ ዳኒኤል ክብረት እንዲህ አለ ፤ሞገስ እንዲህ አለ፤ አቡነ ኤርሚያስ እንዲህ አሉ ፤ሚሊሺያው ጳጳስ እንዲህ አሉ፤ እገሌ እንዲህ ጻፈ፤ እገሊት እንዲህ ተናገረች እያለ እየተነተነ ጠረጴዛን የሚደበድብ በንዴት የሚንጨረጨር ሰው ነው። በትግራይ ሰው የተጻፉት ስለ 10ቱ ቃላት የጥላቻ ሕጎች በሚመለከት እና በባለጌው ቄስ ሠረቀ ብርሃን የተነገሩት ንግግሮች ግን መንጨርጨሩንስ ተውት ማታለላቸውን እንዳያሰናክልባቸው በጥንቃቄ ነበር የያዛቸው።

ይህ ሁሉ የቴድሮሰ ፀጋዬ ወገንተኛነት (ፓርቲዛን) ዛሬም ቀጥሎበት አቡነ ኤርሚያስ ጋር ሲደርስ ግን ሌላ አባሪና አጋዥ ጋዜጠኛ ቴድሮስ አስፋውን ጋብዞ አቡኑን እስኪበቃቸው ድረስ ሲሰድቧቸውና ሲያሳንስዋቸው ዋሉ። ሠረቀ ብርሃንንም ሆነ አሉላ ሰለሞን ወይንም “ታላቅዋ ኢትዮጵያ” የሚል ተረት ተረት ቅዠት የሚቃዡ አሉ፡  ታላቅዋ ኢትዮጵያ የሚለው ትልቅነት የትግራይ እንጂ እንደሚቃዡት አይደለም”>> ብሎ የተኩራራው የወያኔው ጌታቸው ረዳ ጋር ሲደርስ ግን እንኳን አጋዥ ጋዜጠኛ ጋብዞ ሊተቻቸው ጭራሽኑ እነሱንም ጋብዞ የባሰውኑ እንዲያቦኩ ዕድል እንደሰጣቸውና እንዳከበራቸው እናውቃለን።  ሚስኪኑ አቡኑ አሳዘኑኝ፤ የዘረኛነት ቃል እንኳ አልወጣቸውም ፤ግን ልክ እንደ የፖለቲካ ተንታኝ ተቆጥረው ሚዲያው ሁሉ አረፋውን ሲደፍቅባቸው ነበር የዋለው ያደረው። ይህ ወገንተኛነት ወይንስ ሚዛናዊ ጋዜጠኛነት ትችት?

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

 

 

 

 

 

 

 

Friday, November 17, 2023

የአማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ እና ቀዳማይ ወያኔ ያስተላለፉት አረመኔአዊ አዋጅ ተመሳሳይነት ጌታቸው ረዳ ( የ Ethiopian Semay ድረግጽና ፌስቡክ ዋና ድረግጽ አዘጋጅ)

 

የአማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ እና ቀዳማይ ወያኔ ያስተላለፉት አረመኔአዊ አዋጅ ተመሳሳይነት

ጌታቸው ረዳ

( የ Ethiopian Semay ድረግጽና ፌስቡክ ዋና ድረግጽ አዘጋጅ)

11/17/23

ብዙዎቻችሁ ለአመታት እንደተከታተላችሁኝ አማራው ምሁር እና አሁን የሚንጫጫው ወጣት ሳይነሳ ስለ አማራው ሕልውና እንዲነሳ ብዙ እንደጣርኩና አማራ ነን ከሚሉትም እንደተገለልኩና እንደተዘለፍኩ የምታውቁ ይመስለኛል። ዛሬ የአማራ ተጋድሎ የብረት ትግል ከተጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ብዕሬን ወደ ወቀሳ ሳሾል እያዘንኩ ነው። እነሆ ወደ ትችቴ ልግባ።

 አማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ እና ሌሎች በሌላ ስም የሚጠሩ ፋኖዎች ማን እንደሚመራቸውና ልዩነታቸው ስማቸውም በደምብ ጥናት አላደረግኩምና እባካችሁ ጠቁሙኝ። እኔ ግን የማውቀውና የገመትኩት “ፋኖ” የሚል አንድነት ያለው መጠሪያ መስሎኝ ነበር አሁን ግን ብዙ ቡድን እንዳለ ነው እየታዘብኩ ያለሁት፤ ሆኖም አንባቢዎች እንድትረዱኝ  በሃሳብ መስጫ ሳጥን ውስጥ ልዩነታቸውና መሪዎቻቸው ብታስረዱኝ እወደላሁ። ብዕሬን በማነሳበት በሚከተለው (አማሐራ ሕዝባዊ ፋኖ) በተባለው ድርጅት አርበኛ ፋኖ እስክንድር ነጋ እንደማይኖርበት ተስፋ አደርጋለሁ። ካለበትም ጠቁሙኝ።

ሰሞኑን በሕዳር 6/2016  ዓ.ም “አማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ” የሚል አንድ ጥሪ አስተላልፎ ነበር። ጥሪውም በዚህ በለጠፍኩት ቪዲዮ ታደምጡታላችሁ።ጥሪው አረመኔነትና ድንቁርና የተሞላበት እንዲሁም የሃይማኖት ዕምነቶችና የሰንበቴ፤ ዕድርና ማሕበረሰቦች ድርጅቱን በሚቃወሙ እና ቤተሰቦቻቸው ጭምር ምን ማድረግ እንደሌለባቸው በጥብቅ ያዛል።

ነገሮች ለማገናዘብ፤ የዚህ ድርጅት ጥሪ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ለማነጻጻር እንዲመቸን ሦሰት ድርጅቶች ማለትም በብረት ትግል ሲታገሉ ከነበሩት ከቀዳማይና ከዳግማይ ወያኔ የተላላፈ አዋጅ/ጥሪ/ እንዲሁም በሰላማዊ ትግል ሲታገል ከነበረው የ1997 ቱ የቅንጅት ሕዝባዊ ጥሪና ‘’አማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ’’ ከተባለው ጋር የተላለፉት ጥሪዎች ተመሳሳይነትን ልዩነታቸውን እንዲረዳን በየተራ እንመልከታቸው።

 መጀመሪያ በቅንጅት ጊዜ የነበረው ሕዝባዊ ጥሪ

ሕዝቡ ተቃውሞውን በሚከተሉት ሁኔታዎች እንዲገልጽ ጥሪ አድረጎ የነበረውን ከግርድፍ ትውስታዬ በግሌ የማስታውሰው ያስተላለፈው መግለጫ ጥቂቶቹ ላስነብባችሁ።

የቅንጅት መግለጫ በተቃዋሚዎቹ ላይ ያስተላለፈው የትግል ውሳኔ፡

<<እቤት በመቀመጥ (ወደ ስራ አለመሄድ/የቁጭ አድማ) ተቃውሞውን መግለጽ። 5 ቀን የሚቆይ የእቤት መቀመጥ አድማው የሚጀምረው ለእስላሞች ክብር እና ወንድማዊ ደስታ ለመካፈል ሲባል ሮሞዳን የተባለው እስላሞችን በዓል ካለፈ ነበር። 

በኢሕአዴግ ባለቤትነት የሚካሄዱ የንግድ ተቋማት አንደ አምባሰል፤ጉና፤ዲንሾ፤ዎንዶ፤ዳሸን ቢራ ፋቭሪካ እና ሜጋ የመሳሰሉት ሕዝቡ ግብይት እንዳያደርግ።  ከንግድ ድርጅቶቹ አልፎ በቁጥጥሩ ስር የሚገኙ የዜና ማሰራጫ ራዲዮኖች (ድምፂ ወያነ ትግራይ፤ ፋና፤ኢ FM 97.1  FM 96.3 የመሳሰሉ) እና እንዲሁም በጋዜጦቹ ላይ የንግድ ማስታወቂያ አለማድረግ፤ ስርዓቱ የሚያስተላልፋቸው ዜናዎች እና ቅስቀሳዎች እንዳያነብ እና እንዳያዳምጥ። በምትኩ የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮን እና ዶቸቬለ አንዲሁም ትንሳ ራዲዮ የመሳሰሉት ከውጭ የሚሰራጩ  የዜና አውታሮች ችን ማድመጥ።

ስርዓቱ የሃይል እርምጃ በወሰደ ቁጥር፤ በኢሕአዴግ አባላት እና እንዲሁም የተጭበረበረውን ምርጫ በግድ ተቀበሉ እያሉ ሰላማዊ የፖለቲካ ተቃወሚ አባሎችን እና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጉልበት በማሳየት፤ በመደብደብ፤ በማሳሰር፤በመግደል፤ በመሰለል፤በማስፈራራት ሕግን በመጣስ መብት የሚረግጡ የስርዓቱ ደጋፊዎች ሁሉ ሕብረተሰቡ እንዲያገላቸው።ቅንጅት ማንኛውም የቅንጅት አባልም ሆነ ደጋፊ ከላይ ከተጠቀሱ ምክንያቶች ውጭሃይማኖትን እና ጎሳንመሰረት ያደረገ ማሕበራዊ ማግለል እንዳይደረግ በጥብቅ አሳስቧል።>>  (ግርድፍ ይዘት ጌታቸው ረዳ EthiopIan Semay Editor) የሚል ነበር

እንግዲህ ከላይ እንደተጠቀሰው ቅንጅት <<ሰላማዊ የፖለቲካ ተቃወሚ አባሎችን እና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጉልበት በማሳየት፤ በመደብደብ፤ በማሳሰር፤በመግደል፤ በመሰለል፤በማስፈራራት ሕግን በመጣስ መብት የሚረግጡ የስርዓቱ ደጋፊዎች ሁሉ ሕብረተሰቡ እንዲያገላቸው።>> የሚል መግለጫ እንጂ ቅንጅትን በሚቃወሙ “ቤተሰቦች ላይ ጭምር” ማሕበራዊ ግለላ እንዲደረግላቸው ጥሪ አላቀረበም

በአንጻሩ << የአማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ>> የሚባለው ተዋጊ ሃይል  ያስተላለፈው ጥሪ ግን በሚቃወሙትና በሥርዓቱ ደጋፊዎች ብቻ ሳይሆን እርምጃዎች እንዲወሰድባቸው ያወጀው በቤተሰቦቻቸውም ጭምር ነው።

እንዲህ ይላል።

<< የአማራ ሕዝብ ሆይ ! አንተን በጠላትነት የፈረጁህ ሃይሎች ጥላሸት እንዲቀቡህ (ያደረጉት) ደማቅ ታሪክህ በትውልዱ መስዋዕትነት የመጨረሻው ትንቅንቅ እየተደረገ ይገኛል፡ ስለሆነም በውጭም በውስጥ አገርም ያላችሁ አማራ ወገናችን የሕልውና ተጋድሎ እስኪቋጭ ድረስ በቻልከው ሁሉ እንድትደግፍ የአማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ የሚከተለው ሕዝባዊና አማራዊ ጥሪ ያደርጋል፡……..”

ካለ በካስገረሙኝ ከጥሪዎቹን አንዳንዶቹን ልጥቀስ፡

1ኛ- በአሁኑ  ሰዓት ሠርግ ለማሠረግ ያሰባችሁ ፤ ተስካር ለማውጣት ያቀዳችሁ፤ክርስትና ለመደገስ የተዘጋጃችሁ ይህ የሕሊና ተጋድሎ እስከሚጠናቀቅ ድረስ እንድታራዝሙት ስንል አማራዊና ወገናዊ ጥሪ እናቀርባለን።

በ3ኛ- ደረጃ የጠቀሰው ሌላው ያስገረመኝ ጥሪው ደግሞእንዲህ ይላል፤

<<ለሥርዓቱ ያደሩ አማራ የሆኑ የሚሊሺያ የአድማ ብተና ቤተሰቦችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከዕድር ፤ከሰንበቴ ማሕበርና ከሌለቹ ማሕበራዊ ና ግብረገባዊ (“መስተጋብራዊ” ለማት ይመስለኛል አንባቢው “ግብረገባዊ” ሲል) ሥርዓቶች ባስቸኳይ እንዲገለሉ ስንል ጥሪ እናቀርባለን።>>  ይላል።

ሌላው ደግም 4ኛው እንዲህ ይላል፡-

<< የሚሊሽያና አድማ በታኝ እንዲሁም የመሳሰሉት እርምጃ ተወስዶባቸው ሞተው ሲገኙ ፍትሃት እና ልቅሶ እንዳይደረግላቸው” ጥሪ ያስተላልፋል።>> ሕዳር 6/2016 የአማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ።>>

እስኪ አንድ ባንድ እንመልከታቸው።

<<1ኛ- በአሁኑ  ሰዓት ሠርግ ለማሰረግ ያሰባችሁ ፤ ተስካር ለማውጣት ያቀዳችሁ፤ክርስትና ለመደገስ የተዘጋጃችሁ ይህ የሕሊና ተጋድሎ እስከሚጠናቀቅ ድረስ እንድታራዝሙት ስንል አማራዊና ወገናዊ ጥሪ እናቀርባለን።>>

ይህ አዋጅ ተመሳሳይነቱ በብላታ ሃይለማርያም ረዳ የተመራው ይትግሬው  የቀዳማይ ወያኔ ሳይሆን በመለስና ዜናዊ የተመራው ዳግማይ ወያነ ጥሪ በትግሉ ወቅት ማንኛውም ገበሬ ሰርግ እንዳያከናውን፤ክርስትና እንዳያስነሳ፤ ተስካር እንዳይዘክር ወዘተ ከሚለው ጋር  ይመሳሰላል።ከዛው ቃል በቃል የቀዳውም ይመስላል። ይገርማል!

እንዲህ ያለ ማሕበራዊና ሃይማኖታዊ ሕጎችን ባንድ ተዋጊ ሃይል ጥሪ ሲታገድ ይህንን ጥሪ ተላልፎ እምቢ ብሎ የተገኘ ሃይማኖተኛና ማሕበራዊ አከናዋኝ ቅጣት፤ እስራት፤ግድያ ውርሻ ፤መገለል  ወዘተ…….የመሳሰሉ ያልተጠቀሱ ዕርምጃዎች ሊፈጸምበት ይችል ይሆናል ማለት ነው። ይገርማል።

 ይህ ነው ትግል ማለት ?  ይህ ነው ሕዝባዊ እሴቶችና ሃይማኖቶችን ማክበር ወይስ ሃይማኖትና ማሕበረሰባዊ ዕሴቶችና ክንዋቤ ነፃነቶችን “በቁጥጥር ሥር ማድረግ”? ቀስ ብሎ ነገም እንደ ወያኔ መላውን አማራ ሲቆጣጠር ቤተክርስትያናትን እና መስጊዶችንም ጭምር በሥሩ እና ለራሱ ጠቀሜታ አዋጅ እያወጀ በሥሩ እንዲውሉ ማድረጉ አይቀሬ ነው ማለት ነው።

ወደ ቀዳማየው ወይኔ አዋጅ ድግሞ ልውሰዳችሁ፡

በቀዳማይ ወያኔ እንኳን መቃወም ቀርቶ በትግሉ ሕግ አምላክ ቁም ተብሎ ትግራይ ውስጥ አልቆምም ያለ የሚከተለው መገለል ጥሪ ተላልፎበት ነበር። ከመጽሐፌ ጥቂቱን ልጥቀስ፡

ድሮ በሃይለስለሴ ዘመን አንድ ሞገደኛም ሆነ አንድ ሰው ወደ ሕግ ለማቅረብ እንሂድ ስትለውበሃይለስላሴ በሕግ አምላክሲባል ነበር። የመሳፍንቶች እና የነገሥታት ዘሮች የሚበዙበት እና የሚወለዱበት አካባቢ አንደርታ አውራጃ በቀዳማይ ወያኔ ለንጉሥ ሃይለስላሴ አንገዛም በማለት “12 ገረብ” (አስራ ሁለት ጅረት/ድርጅቱን ተሰብስበው ባቋቋሙት ኣካባቢ የገጠር ማሕበሮች) በሚል ስም ጊዜያዊ የአማጽያን መንግሥት ሕዝባዊ ባይቶ/አሰምብሊ) መስርቶ በነበረበት ወቅት ደግሞዝባን ገረብ” (በገረብ ሕግ አምላክ) በማለት አንድ ሰው እንድትቆም ተማጽኖህ ካልቆምክ፤ ወይንም በገረብ ሕግ ዳጅነት ላለመዳኘት እምቢ ካለ የገረብ ሕግ ረግጦ እንደሄደ ተቆጥሮ የሚከተሉት በሕግ የጸደቀ የገረብ አዋጅ ይፈረድበታል።

(1)-የገረብ ሕግ ያላከበረ ታምሞ የአልጋ ቁራኛ በሆነበት ወቅት አግዚአብሔር ይማርህ ተብሎ በማንኛውም ጐብኚ እንዳይጎበኝ፤

(2)- በሃዘን ጊዜ ጥናቱን ይስጥህ ተብሎ አንዳይጠየቅ

(3)-ከሕዝብ እና ማሕበራዊ ግንኙነት እንዲገለል። የሚሉ ነበሩ።

ይህ የሚያመለክተው ባለጠመንጃዎች በሃሳብ ያልተስማማቸውን ሕብረተሰቡን በቁጥጥር አድርገው አዋጅ በማወጅ የሌላውን ነጻነት “ሰብአዊነትን” በሚጻረር መልኩ እንዴት እንደሚጋፉት ያሳያል። ፋኖ እያደረገ ያለውም በሚቃውሞዋቸው ቤተሰቦች ጭምር ጭካኔ አውጇል። የተቃዋሚያቸው አሞት  ሕክምና እንዳይደረግለትም ያካተተ ነው። የፋኖ ሙርከኛ ተዋጊዎች ግን ሆስፒታል ተኝተው ሲታከሙ ቆይተው ኦሮሙማው መንግሥት ወታደሮች እያወጡ ረሽነዋል። ይህንን ደግሞ ፋኖ ሲቃወመው ሰምተናል። ታዲያ ተቃዋሚያቸው ሲሞት ፍትሃትና ሕክምና እንዳይደረግለት ጥሪ ካደረጉ ከኦሮሙማው መንግሥት ጭካኔ በምን ይለያል? ባህልን እና ሃይማኖት ነክ ተያያዥ ነገሮችን መነካካት ለምን አስፈለገ? ኢህ ለጠላት ጥሩ የቅስቀሳ መሳርያ ማቀበል አይደለም ወይ?

በርካታ አመታት የታገልኩለት የአማራ ሕልውና ትግል ለመውቀስ ስገደድ እያዘንኩ ነው። ካሁኑኑ የኔን ምክር ሰምቶ እርማት ካላደረገ ትግሉ ወደ “የወያኔ ትግሬያዊ ባሕሪ” ሳይጓዝ አይቀርም የሚል ፍራቻ አድሮብኛል። እንዴት የሞተን ሬሳ አትቅበሩ ፍትሓት አታድርጉ ብሎ ጥሪ ያደርጋል፤ ቄሶችን ያስፈራራል? እንዳይቀበር ማለትስ ምን ማለት ነው?

ወደ ሌላው ጥሪው እንሻገር።  እንዲህይላል፡-                                                           

<<ለሥርዓቱ ያደሩ አማራ የሆኑ የሚሊሺያ የአድማ ብተና “ቤተሰቦችን” ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከዕድር ፤ከሰንበቴ ማሕበርና ከሌለቹ ማሕበራዊና ግብረገባዊ ሥርዓቶች ባስቸኳይ እንዲገለሉ ስንል ጥሪ እናቀርባለን።>

ከላይ የ1997 ቱ በእነ ሃይሉ ሻውል ፤ ልደቱና በእነ ብርቱካን ሲመራ የነበረው ከቅንጅት ላንድነትና ለዲሞክራሲ ድርጅት የተላለፈው ጥሪ እንዳስነበበኩዋች

ቅንጅት  <<የስርዓቱ ደጋፊዎች ሁሉ ሕብረተሰቡ እንዲያገላቸው።>> ሲል የአማራ ሕዝባዊ ሃይል ፋኖ የተባለው ደግሞ <<ለሥርዓቱ ያደሩ አማራ የሆኑ የሚሊሺያ የአድማ ብተና “ቤተሰቦችን” ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከዕድር ፤ከሰንበቴ ማሕበርና ከመሳሰሉ ማሕበራዊ ትስስርና መስተጋብሮች ባስቸኳይ እንዲገለሉ ስንል ጥሪ እናቀርባለን።>> ይላል።

ድርጅቱ ለመሆኑ የተማሩ ሰዎች አሉት? ምንም የፖለቲካ ሱታፌ በሌሉበት ምስኪን ህጻናት፤ሽማግሌዎች፤አካለስንኩላን፤ አቅም የሌላቸው ዕርጉዞች፤ ቤተሰቦቻቸው ጭምር ገበያና ሱቅ ሄደው እንኳ እህልና ሸቀጣሸቀጥ ገዝተው ልጆቻቸው እንዳይመግቡና እንዲከለከሉና አንዲገለሉ ከጎረቤቶች ጋር ቡና እንዳይጣጡ ለርሃብ ተጋልጠው እንዲሞቱ ውሳኔ አስተላልፏል።ይህ አረመኔነት ወይስ ነፃ አውጪነት?

አማራ በእንደዚህ አይነት ድንቁርና ነፃ መውጣት ይችላል? በፖለቲካ ንኪኪ የሌላቸው ቤሰተቦችን፤ እመጫቶችን፤ ዕርጉዞችን፤ህሙማንን ከማሕበራዊ እንቅስቃሴና ግብይት እንዲገለሉ ማድረግ አምሐራዊ ባሕል የተከተለ ነው? ስንሰማው የነበረው “አማሓራዊ ደግነትና ባሕል” ሲባል የነበረውስ ይህ ነው?

ትግሉን ላለማደናቀፍ በጣም ስጠነቀቅ ነበር የቆየሁ ፤ አሁን ግን ሳላስበው ወደ እዚህ አይነት ንዴት ሲጨምሩኝ ካሁኑ ጥንቃቄ ካላደረጉ ከነሱ በፊት እንደነበሩት ድርጅቶች እንዳንበረከኩኳቸው ሁሉ ለወደፊቱ ብዕሬ ወደ እነዚህ እንዳይዞር እየሰጋሁ ነኝ። ስለዚህ የብረት ትግል “ትዕግሥት፤ ጥንቃቄ፤ሰብአዊነትና ዕውቀት” ታጥቆ መጓዝን ስለሚጠይቅ እርማትና ጥንቃቄ እንድታደርጉ እጠቁማለሁ። የዚህ ድርጅት መሪዎች እነማን ይሆኑ? እስኪ አንባቢዎቼ ጠቁሙኝ። ይህ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምን ቢደረግለት ይድን ይሆን?

ጌታቸው ረዳ  (Ethiopian Semay ድረገጽ አዘጋ