Monday, August 16, 2021

ዜጎች መንግሥትን የመቃወም እንጂ “መንግሥትን የማመን ግዴታ” ሕግመንግሥቱ ላይ የለም! ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ) 8/16/2021

 

ዜጎች መንግሥትን የመቃወም እንጂ “መንግሥትን የማመን ግዴታ” ሕግመንግሥቱ ላይ የለም!

ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)

8/16/2021

እንደምን ሰነበታችሁ።

 በወያኔ ጦር ጫሪነት ትግራይን ለመገንጠልና ኢትዮጵያ እና አማራን ለማጥፋት እየተካሄደ ያለው ጦርነት በሚገርም ሁኔታ ወደ አማራ “አውራጃዎች” ድረስ በመምጣት ጡንቻው እያዳበረ የዜጎች መፈናቀልና ሞትን በማስከተሉ ምክንያት በኦሮሞዎች የብልጽግና ኦሕዴድ መንግሥት እየተመራያለው ዳካማ የመከላከል የጦርነት በአመራሩ የብቃት ማነስ ብዙ ጉዳት ደርሷል።

ጉዳት በመድረሱ ምክንያት፤ አንዳንድ የአማራ ተወላጆችና ወጣቶች፤ በራሳቸው አካሄድ ተደራጅተው የወያኔን ጦረኛ ሃይል መመመከት እንደላበቻው ሊደራጁ ሲሞክሩ፤ የወያኔ ትግሬ አገልጋይ የነበረው ዛሬ ደግሞ “የአማራ ነገድ ወኪል” ነን የሚሉ “የኦሮሞ ኦሮሙማ” መንግሥት “አገልጋይ” ከሆኑት ከደመቀ መኮንን እና የተመስገን ጥሩነህ ድርጅት ዕውቅና ውጭ በግል ተደራጅቶ ወያኔን መውጋት አይፈቀድም ሲባል ሰምቻለሁ። ካድሬዎቻቸውም  እንዲህ ሲቆሽሹበት ታዝቤአለሁ።

አብሶ የገረመኝ የነዚህ “የመንግሥት ተብየው” ወኪሎች ውሳኔ ሳይሆን የገረመኝ፤ “ኢዜማ” ብሎ ራሱን የሚጠራ  “አማራውን ማሕበረሰብ መጤ” ብሎ የሚጠራው “ኢንተርሃሙዌው የግንቦት 7 ድርጅት” የነ ደመቀ  መኮንን ቅዠት ደግፈው “ማንም አማራ ብግል ተደራጅቶ ከመንግሥት እውቅና ጎን ከመሆን ውጭ ወያኔን በጎበዝ አለቃ ተደራጅቶ መዋጋት ክልክል ነው” ሲሉ እነ የሺዋስ አሰፋ እና ግርማ የተባለው (አማራ ይሁን አይሁን አላውቅም) አንዱአለም አራጌ……ድርጅት የስተላለፉት ውግዘት ከመገረም በላይ ገርሞኛል።

እነዚህ “ቃኤሎች” አብይን ለማስደሰት ሲሉ ብዙ ርቀት እንደሄዱ ባለፉት 3 አመታት ታዝበናል። ማንም ይበል ማንም ዜጎች “ቤቶቻውን፤ማሳቸውን፤ ሚስቶቻቸውን፤ ከብቶቻቸውን፤ አካባቢያቸውን፤ቤተ እምነታቸውን፤ድምበራቸውን” በግልም ይሁን በጋራ ተደራጅተው የመጣባቸውን ጠላትን የመመከትንም ሆነ የማያምኑትን መንግሥት መመከትና ከሥልጣን ማስወገድንም ጭምር ተፈጠጥሮአዊ መብታቸው ነው።

እኛ ዜጎች በየትኛውንም ዓለም ያለው ፍጡር “መንግሥት” የሚለውንና የሚያስተላልፈውን አዋጅና ቅስቀሳም ይሁን ዜና ሁሉ የመቀበል ግዴታ የለብንም።

እውነተኛ የሆነውን የዚህ የጥፋት ዘመን እንቆቅልሽ እስከዛሬ መፍታት ያልተቻለ፤ ኢትዮጵያ  በ30 አመት ውስጥ ከዓለም ሙሉ የተለዩ ሁለት ጸረ ኢትዮጵያ የሆኑ  መሪዎች ነግሠውባታል። መለስ ዜናዊ (ለገሰ ዜናዊ) እና አብይ አሕመድ  (አብዮት ካሳዬ)። እነዚህ ሁለቱም መሪዎች የሚመርዋቸው መንግሥታዊ ድርጅቶች (የትግራይ እና ኦሮሞ ምንግሥቶች) መሪ ሆኖው የአገሪቱን ዳር-ድምበር፤ ክብር፤ ታሪክና ሰንደቃላማ በዓለም መድረክ ፊት በድብቅም በግሃድም የሚያንቋሽሹ “ስትረንጅ” መሪዎች ናቸው።

 አገሪቱን ለማፍረስ በሕግ የተደነገጉ 44 የጎሳ ባንዴራዎች አዘጋጅቶ፤ ለሚገነጠሉ ጎሳዎች አንቀጽ አዘጋጅቶ አገር ለማፍረስና ያገሪቷን ጥንታዊ የባሕር በሮቿን ለጠላት በማስረከብ የሚኩራራ ርዕሰ ብሔር የታየው በኢትዮጵያ ብቻ ነው። አብይ አሕመድ በመለስ ዜናዊ አካሄድ እና ሕገመንግሥት የሚጓዝ የፋሺሰትና ናዚ ስልት አራማጅ ግለሰብ  ነው።ስለ ፋሺስቶች እና ናዚዎች አሰራር መጽሐፍት አንብቡ። ሰውየውም ሆነ ወያኔዎች የናዚና ፋሺስቶች የአብሮነታቸውን ርዕዮት በግልጽ በነዚህ መጽሐፍቶች ውስጥ ብግልጽ ታዩዋቸዋላችሁ።

ኦሮሞ ተብሎ በተከለለው ክልል አማራዎች ሲጨፈጨፉ አብይ አሕመድም ሆነ ሽመልስ አብዲ በሩዋንዳ ውስጥ “ሙጎኔሮ፤ ክብሊራ ፤ ኪጋሊ፤….እና የመሳሰሉ የሩዋንዳ ገጠሮችና ከተሞች  በቱትሲ  ነገድ ላይ የዘር ጭፍጨፋ የተካሄደ ያህል እነዚህ ሁለት ሰዎች  በሚያስተዳድሩት አገርና ክልል “አማራዎች ፤ ጋሞዎች፤ ክርስትያኖች እንዲሁም ጉራጌዎች..” ጭፍጨፋ ሲካሄድባቸው “ድርጅታቸው እና አንዳንዴም በግሃድ እራሳቸው በቀስቃሽ ንግግር” ተባባሪዎች ነበሩ።

አባገዳዎች ልክ እንደ ሩዋንዳ ካቶሊክ ፓስተሮች “ባሌ” ውስጥ አማራ ባሌን ለቆ እንዲወጣ አዋጅ ሲታወጅ ተባባሪዎች ነበሩ።  የቱሲዎችን ጭፍጨፋ ያካሄዱ “ዜሮ ኔትወርክ እና ቡሌት ግሩፕ” የተባሉ ኢንትረሃሙዌ ወረበሎችን አደራጆች የሚመስሉ  እንደ እነ “ጃዋር መሓመድ እና ኦነግ” የመሳሰሉ “የዘር ጭፍጨፋ መሃንዲሶች” በመንግሥት ወጪ በሪፑብሊካን ጋርድ ጠባቂዎች እንዲጠበቁ ያደረጉ “ነበሰገዳይ ወረበሎችን” ሲያሞካሹ የነበሩ ወንጀለኞች ናቸው። ስለዚህም አማራው መንግሥትን አንወጋም፤ ግን ብግል እንደራጃለን፤ አናምናችሁም ካላቸው ምክንያት አላቸው።መከራከር አያስፈልግም። በቃ! የመርሳት ሱስ አለን እንዴ!!      

በዚህ ግለሰብ መመሪያ የሚመሩ እነ ደመቀ መኮንን እነ ገዱ አንዳርጋቸው፤ ተመስገን ጥሩነህ ወዘተ….ባለጊዜዎቹ እኛ ነን ስለዚህ በኛ ስር የሚሰጥ ነፃነትና መደራጀት እንጂ ከኛ ውጪ ነፃ ዜጋ የራሱ ነፃነት የለውም ይላሉ።  ‘እኛ  መንግሥት ነን” ፤ መንግሥት ማለት “ሕዝብ” ማለት ነው ይሉናል።

 ፈላስፋው ጀርመናዊው ፍሬዴሪክ ኒቺ ደግሞ  “መንግሥት የክፉዎቹ ሁሉ ክፉ አውሬ” መሆኑን ይነግረናል።  እንዲህ ይላል።

“መንግሥት ማለት በሁሉም ቋንቋዎች የሚዋሽ አፍ ነው። መንግሥት የተፈጠረው ለኒህ እልፍ አእላፍ ሰዎች ነው። ግን …  እንዴት እንዴት እንደሚያባብላቸው ብቻ ተመልከቱልኝ። ሲያላምጣቸው፤ መልሶ መላልሶ ሲያኝካቸው አያችሁልኝ?“ ይላል ‘ኒቺ’።

አዎን በአውሬዎች መሃል ተከብበን በቀጥታም በተዘዋዋሪም እያላመጡ መልሰው መላልሰው አኝከውናል። “ኒቺ” መንግሥት ሲሞት ቀስተደማና ይወለዳል’ ይላል። ኢትዮጵያም በቀስተዳመና መቀነትዋ ዙርያ ብቅ ብላ እንደጥንቱ ሰንደቃላማዋን ይዛ የዚህ ስርዓት ሞት ታበስራለች።  አንድ ቀን! 

ስለዚህም በዚህ በዛሬው ጦርነት ማንኛውንም ዜጋ ወያኔን ለመውጋትም ሆነ ቤተሰቦቹን እና አካባቢውን ለመጠበቅ በግልም ይሁን በጎበዝ አለቃ ተደራጅቶ የወያኔን የብረት አጥር ለመስበር (ለጊዜውም ቢሆን መንግሥት ተብየውን ለመውጋት በይደር አቆይቶ) መንግሥት ተብየውን እስካልወጋ ድረስ የመደራጀት መብቱ ተፈጥሮአዊ እንጂ “አፍግፍግ” እያለ ሕዝብን ለጥቃት አጋልጦ፤ ጦሩን እያስማረከ የሚያስፈጅ እና ጠላትን ከሚያስታጥቅ መንግሥት ጎን የመሰለፍ ግድቴ የለውም።

የአማራ ገበሬና ወጣት ተማሪ በጎበዝ አለቃ ልደራጅ ካለ ጥሩ ተደራጅቶ አገሩን ይከላከል። መንግሥት አስፈላጊውን ትጥቅ እና ስንቅ ጫማና ብርድልብስ ከለገሰው እሰየው፤ ካልሆነ ግን እንደ ጥንቱ ወላጅ አርበኞች ወላጆቻችን ምንም የሚያነጥፈው አንሶላም ሆነ ብርድልብስ ባይኖሮውም በደረቁ መሬት ላይ በተከፈተው የኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የተዘረጉትን የወላጆቹ ኮከቦች ደርቦ ኢትዮጵያን የመከላከል መብቱ ተፈጥሮአዊ ነው።

ዜጎች መንግሥትን የመቃወም እንጂ “መንግሥትን የማመን ግዴታ” ሕግመንግሥቱ ላይ የለም!

አመሰግናለሁ

ኢትዮጵያ ለዘላም ትኑር!

ጌታቸው ረዳ Ethio Semay

Tuesday, August 3, 2021

የባህርዳሩ ጸረ ትግሬ ዘመቻ ዛሬም እንደቀጠለ ነው ጌታቸው ረዳ ኢትዮ ሰማይ ዋና አዘጋጅ 8/3/2021 ፈረንጅ አቆጣጠር

 

የባህርዳሩ ጸረ ትግሬ ዘመቻ ዛሬም እንደቀጠለ ነው  

ጌታቸው ረዳ

ኢትዮ ሰማይ ዋና አዘጋጅ

8/3/2021 ፈረንጅ አቆጣጠር

አንባቢዎቼ እንደምን ሰነበታችሁ፤



በውስጥ አገርም በውጭ አገርም ሆናችሁ በምንም ከማንም ፖለቲካ ቡድን ያልወገነው የወንድሜን መታሰር ያሳሰባችሁና ለማስፈታት የጣራችሁ ወገኖቼ ሁሉ እያመሰገንኩዋችሁ፤ በሌላ በኩል ግን “ትግሬ በመሆናችሁ በምናችሁ እንመናችሁ?” “ስለዚህም መጥፋት አለባችሁ” ብላችሁ የወያኔ ጀሌዎች ከነበሩት ከነተመስገን ጥሩነህ እና ከነደመቀ መኮንን ዓሊ ሥርዓት አብራችሁ የኛን መጥፋት ስትጽፉልኝ ለነበራችሁ “የጎስታፖ” ተከታዮች ምኞታችሁ ሰምሯል ደስ ይበላችሁ።

ዛሬም ወንድሜ ያለምንም ወንጀል እና የክስ ዝርዝ “አቃቤ ሕጉ” ወንድሜን አስሮ ከሥራው አፈናቅሎ ፍርድቤት ስያንገላታው ከርሞ ምንም ማስረጃ ማቅረብ ስላቃተው እንደገና “ዳኛውን” ያለምንም ማሳመኛ ክስ ለአንድ ወር ቀጠሮ በመጠየቅ “ፌደራል አጣሪዎች ከአዲስ አባባ መጥተው እስኪያጣሩ ደረስ” ጭለማ እስር ውስጥ ይቆዩ በማለት ንጸሁን ወንድሜን በማሰቃየቱን ቀጥለውበታል።

ሥርዓቱ የስም ለውጥ እንጂ ወያኔ አዋቅሮ የፍትሕ እና የዜጎች መብት ምን እንደሆነ የማያውቁ  ብዙ ግብዞችን  አሰቀምጦት እንደተወው ነው አሁንም ዜጎች በማሰቃየት ላይ እየቀጠለበት ያለው።

“አብይ አሕመድ ጸረ አማራ እንጂ ጸረ ትግሬ አይደለም” ብየ በዚህ ፌስ ቡክ ስከራከርለት መቆየቴ ስሕተተኛ እንደሆንኩ አሁን አብይ ጽረ ትግሬ መሆኑንም ጭምር በተግባር አረጋግጦልኛል።

ፋሺሰቱ መሪያችሁ አብይ አሕመድ “ሳናጣራ አናስርም” ሲል የነበረው ዛሬ ንጹሃን ትግሬዎችን አስሮ ቤተሰብ ፍርድቤት እንዳይገቡ በማገድ፤ ይባስ ብሎ ታሳሪውን በቂ ጊዜና  የማነጋገሪያ ጊዜ ሰጥቶ ቤተሰቡን እንዳያነጋግሩት በሩቅ እንዲነጋገሩ በማድረግ ይኼው የጀርመን የዘር ጽዳት ሥራ ባሕርዳር ከተማ ውስጥ ተከስቶ እንደገና አንድ ወር ቀጠሮ በመስጠት ንጸሁን ወንድሜን እያንገላታው ይገኛል።

አሳዛኙ ነገር አሰሪዎቹ በአማራ ክልል የደህንነትና የአስተዳደር ባለሥልጣናት በኩል ያለምንም ወንጀል ትግሬዎች ዘመቻ እንደተከፈተባቸው እርሱም መታሰሩን እያወቁ በሦስት ቀን ወደ ሥራ ካልመጣህ በፈቃድህ እንደለቀቅክ እናስታውቃለን በማለት “ማስተወቅያ” ለጥፈውበታል። የደመቀ መኮንን ሥርዓት እያደረገ ያለው አስሮ እንደገና የወደፊት ህይወታቸው አንዲበላሽ እያደረገ ነው።

እንግዲህ በዚህ ግፍ የተማረሩ ትግሬዎች ህይወታቸው ተመሰቃቀሎ ሥራ አጥተው በብስጭት ወደ ወያኔ ጦር ተቀላቅለው “ኢትዮጵያን” ብያውኩ ተጠያቂው እራሱ የአብይ አሕመድ እና የደመቀ መኮንን ሥርኣት መሆኑን አንባቢዎች ግንዛቤው ውስጥ አስገቡልኝ። ወያኔዎች እያጠናከረ ያለው እራሳቸው አብይ እና ደመቀ መኮንን ናቸው።

አማራም ሆነ ኦሮሞ ወይንም ትግሬ ያለ ምንም ወንጀል ሳይፈጽም ታስሮ ነጻ ከወጣም ቢሆን “ሥራው ተነጥቆ ሲቆየው” ሰርቶ ቤተሰቡን ማስተዳዳር ካልቻለ ወደ ጫካ ገብቶ ሥርዓቱ ቢፋለም እንዴት ሊፈረድበት ይችላል? ኢትዮጵያ ልምድ ያለው አስተዋይ እና ሁነኛ መሪ አጥታለች ሰል የነበረውም ከዚህ በመነሳት ነው።

 በዚህ ሁኔታ እኔ የብዙ አመት ጠንካራ መንፈስ ባይኖረኝ ኖሮ “ከዛሬ ጀምሮ ኢትዮጵያ አንሆንም “ትግራይ ታሸንፋለች” ብለው የትግራይ ሪፑብሊክ ምስረታና ኢትዮጰያን ወደ ማወክ” ወደ ወያኔ ከተቀላቀሉት ከእነ “አብርሃ በላይ” ጋር እቀላቀል ነበር። ሆኖም የኔ አስተዋይነትና ልበ ሰፊነት ባይጨመርበት ኖሮ ስለ አማራ  የዘር ማጽዳት ሲኮንን የነበረው ይህ ከፊታችሁ ያለው አንድ ብርቱ ትግሬ ዛሬውኑ ኢትዮጵያ አንድ ታጋይዋ ከጎንዋ ታጣው ነበር። ሆኖም እንዲህ ያለ የዘር ፖለቲካ የሚከተል መንግሥት የሚፈጽመው ባሕሪ መሆኑን ስለማወቅና የጀርምን ናዚ ባሕሪዎችንም መጠነኛ መጻህፍቶችን ስላነበብኩ አቋሜን አይፈታተነውም።

የሚገርመው ደግሞ “አብይ አሕመድ” ለማስመሰል ትግሬዎች ለመደለል በትግርኛ መልእክት እያስተላለፈ “በጎንግን”  ንጹሃን ትግሬዎችን እስር ቤት እየከተተ ትግሬዎች በማስቆጣት ወያኔዎች ተጨማሪ ድጋፍ እንዲያገኙ እያደረገ ነው። እንዲህ ያለው ሥራ በማድረግም ይመስላል ከትግራይ ሕዝብ ሸሽቶ ወደ አማራ ድምበር በመጠጋት ወያኔዎችን የልብ ልብ ስጠቶአቸው እያየን ያለነው።

ለማንኛውም አዲስ አባባ ያላችሁ መሪዎችም ሆናችሁ እባሕርዳር ከታማ ያላችሁ የመንግሥት ጠበቃዎችና የደህንነት እና እስተዳዳር ባለሥልጣናት የፖሊስ ሹማምንት ከ3 አመት በፊት የነበረው ከወያኔ አወዳደቅ የቅርብ ትዝታ እንዴት መማር እንደልቻላችሁ የሚገርም ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ስለዚህም ወንደሜን በደምብ ስለማውቀው ያለምንም ወንጀል አስራችሁ ከማንገላታት ወንድሜን ለቀቅ አድርጉት።

ለማንኛውም “የፌደራል አጣሪ” መጣ አልመጣ  ንጹሃንን በማንገላታት እና ከሥራቸው እንዲባረሩ ምክንያት መሆን የእናንተም ሥልጣን ዝነተ ዕለት ሥልጣን ላይ ስለማትኖሩ፤  ለናንተ ለወደፊት ዕድላችሁም ሆነ ለኢትዮጵያ ጎጂ እንጂ ጠቃሚ እንዳልሆነ ምክሬን ላስተላልፍላችሁ እሻለሁ።

በመጨረሻም  ይህንን የጎስታፖ ጀርምን ናዚዎች የዘር ማጽዳት አሰራር ፖሊሲ እንዲቆም ዜጎች ሁሉ እንድታወግዙት እጠይቃለሁ። በተለይ የዘር ማጽዳት የተፈጸማባችህ የ30 አመት አማራ ወንድሞች እና እህቶች ይህንን ስራ አስቀያሚ መሆኑን ይጠፋችሗል ብየ አልገምትም። ስለዚህም የዘር ማጽዳት ኢትዮጵያ ውስጥ ላንዴና ለመጨረሻ እንዲቆም ይህ ሥርዓት መቃወም የግድ ነው። በተለይ ፌስ ቡክ ላይ ሆናችሁ “የተጠቃንበት ሰብአዊ በመሆናችን ስለሆነ ከመጠቃት ነጻ ለመውጣት አንደወያኔቹ የእንሰሳ ባሕሪ እንከተል” ብላችሁ ወጣቱን አማራ እንሰሳ እንዲሆን ግድያ ውስጥ እንዲሰማራ የምትቀሰቅሱ ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋችሗል።

ከወንድሜና ከቤተሰቦቼ ጎን ለቆማችሁ በውጭም በውስጥ አገርም ያላችሁ ወንድሞች እና እህቶች ሁሉ ምስጋናየ የላቀ ነው።

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ