Wednesday, January 27, 2021

የወያኔ ታጋዮችና የትግራይ ሕዝብ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ፖሊሲው በቀጥታም በተዘዋዋሪም የማይነጣጠሉ ትስስሮች አድርገዋል ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ) 1/27/2021

 

የወያኔ ታጋዮችና የትግራይ ሕዝብ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ፖሊሲው በቀጥታም በተዘዋዋሪም የማይነጣጠሉ ትስስሮች አድርገዋል

ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)

1/27/2021

ይህ ርዕስ ለማቅረብ የተገደድኩበት መነሻ፤ ያለፈው የወያኔ እና የትግራይ ሕዝብ ቁርኝት (እስካሁንም የቀጠለው የሞቀው ድጋፍና ፍቅር) እንዳልነበረ ለማድረግ በየሚዲያው የማደምጣቸው አሽቃባጭ ምሁራን እንደ እሬት ስለመረሩኝ አውነታውን ላስቀምጥ። ያው ድሮም የሸዋ ትግሬ ወይንም ጸረ ትግሬ የሚል ስም ስለተለጠፈብኝ፤ ተቃዋሚዎቼ ለኔ አዲስ ስላልሆኑ እውነታው ዛሬም ቢመራችሁ የሆነውን ላስቀምጥላችሁ መረጥኩ።

ሁለት ጉዳዮችን እንመለከታለን ።

 

ወያኔን ወደ ሥልጣን ያመጣው ከሰማይ የመጡ ጦረኞች ሳይሆኑ፤በትግራይ ሕዝብ ትግልና አውቅና ነው። ወያኔና የትግራይ ሕዝብ በመተባበር ያካሄዱት የ17 አመት ዕድሜ ያስቆጠረው ረዢሙ ቢላዋ ያነጣጠረው ልክ የጀርመን የናዚዝም የዘር ፣ የፖለቲካ እና የግዛት ምኞቶችን በአንድ ዘር ላይ የበላይነት ለማሳካት እንዳደረገው ሁሉ በትግራይ ክ/ሃገር የተነሳው የብሔረተኛው ህወሓት ጦር ተመሳሳይ ነበር እንጂ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች፤ ምሁራኖችና ትግሬዎች እንደሚወሻክቱት ስለ ዲሞክራሲ እና ስለ አንድነት ጥበቃ የተደረገ ትግል አልነበረም። ስለ ዲሞክራሲ ማምጣት ትግል ተውትና ስለ አንድነትና ሉዓላዊነትን በከፋ መልኩ እንዴት እንደተከናወነና ማን እንዳከናወነው እናውቀዋለን! አደለም እንዴ? ። ኢትዮጵያን ወደብ አልባ ያደረገው ማን ነበር? “ትግሬዎች ናቸው’ አደለም እንዴ?

አሁንም የቆየው “ትግሬዎች በዘመነ ወያኔ ልዩ ተጠቃሚዎች” አልነበሩም ሕዝብና ድርጅት ለያይተን እንመልከት የመባለው የተሳሳተው መስመር በዚህ ጦርነትም ብሶበት ምሁራኑና ጋዜጠኞች ሲያሽቀብጡ እየደመጥኩ ነው።

 

በጣም የሰለቸኝ ደግሞ የትግራይ ሪፑብሊክ ለመመስረት የተነሱት የትግራይ ብሄተረኞቹ ከጦርነቱ በኋላ በለስ ቀንቷቸው ከረጅም ጊዜ በኋላ መንግሥትነት ከያዙ በሗላም ይሁን ዛሬ ከሥልጣን ከተወገዱም ቢሆን የትግራይ ሕዝብም ሆነ ተጋዮቹ በጅምላ ጭፍጨፋ እና ከወያኔ የዘር ማጥፋት ፖሊሲ ጋር በተያያዙ ሌሎች ወንጀሎች ውስጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተሳትፎ አላደረገም፤ የተደረገው ፍልሚያ ለዲሞክራሲና ለአንድነት ነበር የሚል አፈታሪክ አሁንም መቀጠሉ የሚገርም ነው፡፡

አሁን እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት በትግራይ ላይ ርሃብ መከሰቱን አስመልክቶ በተከታታይ በዜና አውዶችና ውይይቶች የሚጋበዙ ምሁራን የሚሰጡት አስተያየት የማደምጠው ይትግራይ ሕዝብ በ17 አመቱ በታላቁ ሴራ አልተካፈለም ፤ ከዚያም አልፎ የትግራይ ሕዝብ በዘመነ ወያኔ ከሌሎች “አፓርታይድ ክልሎች” የተለየ ጥቅም አልተደረገለትም ሲሉ አድምጫለሁ።  ይህ መስመር ከእውነት የራቀ ነው ፡፡ ለማን እንዳደሩ ባላውቅም “አድርባይነትም” ነው።

ምሁራኖቹ የተዘረጉት የልማትና የትምሕርት የጤና “ሱፕራ እና ኢንፍራ” የሚባሉት እስትራክቸሮች/ተቋማት/ ምን ያህል ስፋት እንዳላቸው እያወቁም ቢሆን በቅርቡ ስለተከሰተው ርሃብ ምክንያት አስታክከው ትግራይ ላይ ምንም የልማትና የጤና፤የትምህርት ስላልተደረገ ሕዝቡ ባጭር ወቅት ለርሃብ ተዳርጓል የሚል ክርክር ማስተጋባት ጀምረዋል። በየ ጉሙዝና ኦሮሞ ክልሎች እየታረደና እየተፈናቀለ ያለው የአማራ ማሕበረሰብ ይህንን ቢሰማ ምን ይል ይሆን? ዛሬም እኮ ትግሬዎች ሳይሆኑ አማራዎች ናቸው መፈናቀሉና መታረዱ በገፍ እየተፈጸመባቸው ያለው። የጀነሳይድ ተመራማሪው “ዶ/ር ግሬገሪ እስታንተን” እንደተነበዩት ቢሆን ኖሮ ዛሬ ትግሬው ነበር በየ ክልሉ የዘር ጽዳት ሊደርሰው የነበረው። አንዳንድ ክስተቶች የታዩ ቢሆንም “ያ የተተነበየውና የተፈራው ጥቃት ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋነት እንዳይከሰት አድርጎታል።

ትግሬዎች ወያኔ ንጉሥ በመሆኑ ትግሬዎች ከዚህ ንጉሥና ቡድን ምንም አልተጠቀሙም የሚል ክርክር ለመማፍረስ ለበርካረታ አመታት በማስረጃ በመጽሐፍ በተለያዩ ሰነዶች አቅርበን ገልጸናል። ሌላ ቀርቶ ለምሳሌ ወያኔዎች ወደ ሥልጣን ሲገቡ ኤርትራኖችና ትግሬዎች ለነገዳቸው ጥቅም ለማስጠበቅ ሲሉ ሲያደርጉት የነበረውን “አገር አቀፍ ዘረፋ”

The pillage of Ethiopia by Eritreans and their Tigrean surrogates Paperback – January 1, 1996 by Assefa Negash (Author) Amazon የሚገኘው በዶ/ር አሰፋ የተጻፈውን መጽሐፍ ማንበብ ማስረጃ ይሰጣችሗል።

 አልተጠቀመም ባዮቹ ግን እስከዚህችኛው የጦርነት የርሃብ ወቅት ምንም ተጨባጭ ሰነድ አላቀረቡም። ማስረጃ ብለው ሲናገሩ ያደመጥኩት ነገር ቢኖር፤ ለምሳሌ በቅርቡ ምኒልክ በተባለው “የዩትዩብ ሚዲያ” ቀርበው ያደመጥኳቸው የታሪክ የሕግ እና እንዲሁም ጋዜጠኞች የሚል ማዕረግ ያላቸው ምሁራን “የትግራይ ሕዝብ በወያኔ ዘመን ልዩ ጠቀሜታ ያልተደረገለት መሆኑን ማስረጃው በሁለት ሳምንት ዕድሜ ያስቆጠረው ጦርነት 4 ሚሊዮን ለርሃብ መዳረጉ “ልዩ ጠቀሜታ ሳይደረግለት ሃብት ሳያጋብት መቆየቱ ማስረጃ ነው” ሲሊ ነበር እንደ ማሰረጃ ሲያቀርቡልን የነበሩት።

በተለይ ደግሞ አበርሃ በላይ የተባለው ኢትዮ ሚዲያ ጋዜጠኛ የግብጹ ሙባረክን ለመጣል የተደረገውን ሕዝባዊ አመጽ ለሳምንታት ሲደረግ ታሕሪር እስኩየር (የነጻነት አደባባይ) በተባለው ቦታ ሕዝቡ ለሳምንት ሲመሽግ ‘ምግብና ሻይ’ በየቀኑ ከሕዝቡ ሲቀርብ የምጣኔ ሃብት ያለው ሕዝብ ስለሆነ ትግራይ/ኢትዮጵያ ግን ካንድ ቀን በላይ ማድረግ አይቻለውም ሲል ንጽጽር ሲያሰርግ ሰምቻለሁ። አብርሃ ያላወቀው ግብጸች የመጨረሻ ድሆች ናቸው። ዜጎቿ አባይ ወንዝ ላይ ከበርካታ ልጆቻቸው ጋር ዝናብና ቁር በላያቸው ላይ እየወረደ ስብርባሪ ጀልባ ሃይቁ ውስጥ እየተንሳፈፉ የሚኖሩ የምድር ድሆች ያሏት አገር ነች።፡ ያም ይሁን እና ፤ አብርሃ የዘነጋው ያለፉት የተካሄዱ ኢትዮጵያ አብዮቶች ከማአከላዊ ከተሞች ሳይሆን ድሃ ከሚባሉት ኢትዮጵያ ከተሞችና ገጠሮች ሥርዓቱን ለመቋቋም ለበርካታ ወራት እንዴት ሥርዓቱን አስጨንቆ ብዙ ለውጦች እንዳመጣ ረስቶታል። 

በዚህ ሁለት ሳምንት አጭር ጦርነት 4 ሚኪዮን የትግራይ ሕዝብ ለርሃብ የተጋለጠው ወያኔ አደህይቶት ስለነበር ተሎ ለርሃብ ተጋልጧል የሚለው የነ አብርሃ ሆነ የነዚያ ምሁራን እምነት የማልስማማበት ምክንያት 1ኛ- ወያኔ ሲኖር 4 ሚሊዮን ሕዝብ ለርሃብ አልተጋለጠም፡ አሁን የተጋለጠበት ምክንያት ብዙ ምክንያቶች አሉት “መዋቅሩ ፈራርሷል” በወያኔና በጦርነቱ ሰበብ ማለት ነው። ስለዚህም እንደ ሶሪያ እና ሊቢያ ሁሉ ጦርነት ባለበት አገር ሁሉ ርሃብ እውን ሆነ።

 ኢንፍራስትራክተሮችና ሲፈራርሱ በጣም ሃብታም ከሚባሉት ኢራቅ፤ሶሪያ እና ሊቢያ ጦርነት በተነሳ በሳምንት ውስጥ የውሃ፤የመብራት፤የስልክ ፤ የምግብ እና የባንክ አገልግሎት ተቋርጠዋል።

 

በነዚያ አገሮች እንደተከሰተው ትግራይም ውስጥም ‘ርሃብ፤ ሞት ፣ ወሲባዊ ዓመፅ ፣ የምግብ እጥረት ፣ ፣ ህመም እና መድሃኒት ዕጥረት እንዲሁም የአካል ጉዳተኝነት ተከስቷል። በነዚህ አገሮች ከጦርነቱ በሗላም ድብርት እና ጭንቀት (PTSD) የታዩ የጦርነት ውጤቶች ታይተዋል ፡፡ ስለዚህ ትግራይ ውስጥ ባጭር ወራት የጦርነት ውጤት የሆነው ርሃብ የመከሰቱ ክስተት ድሃ ስለነበር የሚለው ቁንጽል ሙግት ስሕተት ነው።

ያውም አብሮ መዘከር ያለበት “የትግራይ ሕዝብ በዘመነ ወያኔ ልዩ ጠቀሜታ ኖሮት (በመላ አገሪቷ ባለ ሃብት ሆኖ) አልፎም ያልተገራ “የሕሊና ኩራት” ፤ እንዲሁም “የበላይነት ስሜት” (ሱፕረማሲ) አያንጸባርቅም ነበር ማለት “አድራበይነት ወይንም ጅልነት” ከመሆን አያልፍም።

ሕዝብ ስንል በማንኛውም ታሪክ አጋጣሚ “ሙሉ ሕዝብ እያንዳንዱ ሰው” ማለት ንደሆነ የሚሰጠው ትርጉም እውነታውን ለመሸፈን ካልሆነ በስተቀር በታሪክ ሙሉ የሚባል ሕዝብ አይራብም፤ ጦርነት አይሳተፍም፤ ሃብት አያካብትም። ሕዝብ የሚባል በትግራይ ውስጥ ብዙውን ታይቶ በማይታወቅ ብዛት የትግራይ ነገድ/ዘውግ በተለይ “ትግርኛ ተናጋሪው” በሃብትና በሥልጣን ተጋሪነት የበላይነት ይዞ ለ27 አመታት ተጠቃሚ ነበር። ይህ ደግሞ ምሁራኖቹ የሚገልጹት ቀለል አድርገው ክብደቱን ለመሸሸግ ሲሉ የሚገልጹት “ጥቂት የወያኔ ጀሌዎች ተጠቅመዋል” በሚል ሲገልጹት እሰማለሁ።  ይህ በጣም የተሳሰተ ያሰለቸን እና ያንድ ብሔረተኛ የመነሻ ፖሊሲው ትርጉም አለማወቅ ነው።

አንድ ብሔርተኛ የሚነሳው ቆሜለታለሁ ለሚለው ነገዱ ፤መጥቀም እና ለመከላከል እንዲሁም ሥልጣን ይዞ ምጣኔ ሃብቱን ለነገዱ ለማስረከብ መሆኑን ከወያኔ ዘመን አገዛዝ ሌላ ማስረጃ ማቅርብ አይቻልም። በተግባር ያየነውም ይኸው ነው።

ዳኝነቱ፤ከላከያው፤የሚኒሰትሮች፤የመገናኛዎች፤ኢንቨየስተሮች/የንግዶች. ወዘተ…ወዘተ ባንድ ነገድ (በትግርኛ ተናጋሪው ትግሬ) ተይዞ ነበር። ዛሬም በሌሎች ባለ ተራ ዘውጌዎች ተሸጋግሮ አያየን ነው። ሃቁ ይህ ነው። የዛሬዎቹ ባለተራ ኦሮሞዎች ደግሞ ማንን እየጠቀሙት እንዳሉት በግሃድ እየታየ ነው። እነዚህ ይህንን ማድረጉን ካመናችሁ፤ እነኚህ ከማን እንደተማሩ ማወቅ አይቸግራችሁም።

በጣም የገረምኝ ደግሞ እዛው ምንልክ በተባለ ሚዲያ አንድ የሕግ ምሁር የተባለለት እንግዳ “በረሃብ የተጠቃውን የትግራይ ሕዝብ የአማራ ማሕበረሰብ ለመከላከያው በሬ እና በግ ገዝቶ ከማገዝ አልፎ ትግሬውን ከዚያ በዘለለ ማገዝ ይጠበቅበታል ሲል አስገርሞኛል። ሃሳቡ የሚከፋ ባይሆንም፡ እኔ የምለው “አማራው” ከትግሬው በምን ተሽሎት ነው ይህ ሁሉ ሃላፊነት ሊጠየቅ የበቃው። እኔ የምለው የትግራይ ሕዝብ 27 አመት እነሱ ባነገሱት የፋሺሰት ቡድን ሲቀጠቀጥ፤ሲታረድ ሲታረዝ፤ ሲባረር “ምሁራኖች” ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርባችሁላቸው ነበር? ካላቀረባችሁላቸውስ ለምን አልጠየቃችሗቸውም? ወይንስ እራሳችሁም 27 አመት አማራ ሲንገላታ “ዝምታ ውስጥ ነበራችሁ” ።

ለመሆኑ ትግሬው ቪክተማይዝድ ተደርጎ እየቀረበ ያለው ተጠያቂው ማን ነው? ትግሬው በኢትዮጵያዊያን አልተበደለም። ሃቁ ይህ ነው። ያውም ከማንኛውም ክፍለሃገር የከፋ የብቀላ ብትር አልተሰነዘረበትም። ለዚህም ኢትዮጵያዊያን መምስገን አለባቸው። እንደ እውነታው ቢሆን ኖሮ አስቀድሜ ከላይ እንደጠቀስኩት “የጀነሳይድ ተመራማሪው “ስንታንተን” የተናገሩት መርሳት አይገባም። እሳቸው ያሉት “እኔ የምሰጋው ወያኔ ከሥልጣን ሲወገድ የማዝነው ለትግራይ ሕዝብ ነው” ነበር ያሉት። የተፈራው ባይደርስም (በሕዝብችን ደግነትና አስተዋይነት የተሰጋው ቆሟል) ፤

የሚገርመው ደግሞ “ጦሱ” ከሌላ የተቀሰቀሰ ሳይሆን ግን ባራሳቸው አካባባቢ ተለኩሶ እነሱን ራሳቸውን ተመልሶ እየለበለባቸው ነው። ይህ እንዳይደርስ ለብዙ አመታት “ወያኔ” የሚባለው ቡድን እና ፖለቲካ እንዳትቀበሉ “መጨረሻ ራሳችሁን ይበላል” እያልን ስንጮሕ ከሕዝቡ የሰማነው ምላሽ ምን እንደነበር ታውቃላችሁ።  አሁን ይህ ሁሉ መከራ ሲደርስበት ተጠያቂው ማን ነው? ተጣያቂ 1ኛ፤የትግራይ ምሁርን እና ሕዝቡ እራሱ ነው፤ 2ኛው ተጠያቂ የኦሮመዎቹ መንግሥት የሆነው አብይ አሕመድ የሚመራው ሥርዓት ነው። የተቀረው የውጭ ጦሰኛ ካለ መጀመሪያ ልጅህን ማስታገስና መስመር ማስያዝ በተገባ ነበር። ያ ሳይሆን እንደኳስ ጨዋታ “አየኹም ናይና” (የኛዎቹ አይዟችሁ) እየተባለ በየ አደባባዩ ሽማግሌና አሮጊት እናቶች ሳይቀሩ የወያኔ ባንዴራ ታጥቀው ሲዘሉና እስከስታና ፉከራ ከማየት ምን የከፋ ትዕይንት አለ?

የትግራይ ሕዝብ ከማንም በላይ ጦርነት አይቷል፤ ጉዳቱንም ያወቀዋል ተብሎ ሲነገር ነበር። አይደለም እንዴ? የጦርነት ምንነት ያወቀ ሕዝብ እንዴት በአንድ ሓላፊነት በማይሰማው፤ አገር ገንጣይ ትምሕርት ተከትሎ በጊዜው ጦርነቱን መግታት ተሳነው?

 

2ኛው ርዕስ

 የወያኔ ታጋዮች ለዲሞክራሲ ትግል ነበር በረሃ የወጡት የሚለው የተሳሳተ ትርክት በሚመለከት፡

 

የትግራይ ሕዝብ ወዶም ተገድዶም ጸረ አማራ ፖሊሲ መከተሉ ከኔ በላይ አብልጦ ወያኔን የሚያውቅ እና በምስረታው ሃ ብሎ ሲጀመር ደደቢት በረሃ የወረደው መስራች አባል የነበረው አንዱ አስገደ ግበረስላሴ የነገረንን እውነታ ይድረስ ለጎጠኛው መምህር ከሚለው ከመጽሐፌ ቀንጭቤ የሰጠውን ጥቅስ ላቅርብ፡<<ህዝባዊ ሓርነት ትግራይ አማራዎች ከድሮ፤ከጥንት ጀምሮ የትግራይ ሕዝብ ጠላቶች ናቸው። እነኚህ አህዮች ከአገራችን ይውጡ፤ትግራይ የራሳችን ነፃ አገር ነች፤ እነኚህ አማራዎች ሲፈልጉ ወደ አገራቸው ሄደው ይታገሉ!!”>> ስትል ህወሓት ኢሕአፓዎችን በትግራይ ውስጥ የመንቀሳቀስ ኢትዮጵያዊ ዜግነታቸውና መብታቸውን ገፈፈች።>> (አስገደ ገ/ስላሴ ህወሓትን ከመሰረቱ የመጀመርያው የህወሓት ታጋይ-ጋህዲ ቁጥር 2 ትግርኛው ቅጅ -ገጽ 162) 

<<ህወሓት ነፃ የሆነች የትግራይ ሪፑብሊክ ለመመስረት ነው ዋናው የትግላችን ዓላማ>> ስትል… ኢሕአፓ ደግሞ <<ትግራይ የኢትዮጵያ ሕዝብ አካል ነው ስለሆነም ትግላችሁ የኢትዮጵያን አንድነትን የሚበትን ነው።>> ሲሉ ነበር። (አስገደ ገ/ስላሴ- ጋህዲ ቁ/2 የትግርኛው ቅጅ 2001 ዓ.ም)

<<ኢህአፓ በአጋሜ አውራጃ ውስጥ በአሰፈ ሰበያ እና በወረዳ ጉሎ ሞዀዳ በወያነ ትግራይ የጠባብነት ጨረታ አሸናፊነት ተበልጦ ከትግሉ ከወጣ በሗላ።ከዚያ በሗላ የጠባብ ብሔረተኝነት በሽታ በመላዋ ትግራይ እንደ ተላላፊ በሽታ ተስፋፍቶ ወደ ሕዝቡ በመተላለፉ አብዛኛው የትግራይ ሕዝብ ፀረ አማራ ተንቀሳቀሰ።”>>

(አስገደ ገ/ስላሴ የወያኔ የመጀመሪያ መስራች አንዱ፦ ጋህዲ ቁ/2 ገጽ 155 የትግርኛው ቅጂ 2001 ዓ.ም.} ።

ልብ ልትልሉኝ የምፈልገው አስገደ ገብረስላሴ የትግራይን ሕዝብ የገለጸውን “…ከዚያ በሗላ የጠባብ ብሔረተኝነት በሽታ በመላዋ ትግራይ እንደ ተላላፊ በሽታ ተስፋፍቶ ወደ ሕዝቡ በመተላለፉ አብዛኛው የትግራይ ሕዝብ ፀረ አማራ ተንቀሳቀሰ።” የሚለውን የሚያሳይን ታጋዩም ሆነ ሕዝቡ ስለ ዲሞክራሲ ሳይሆን የታገለው አስገደ አስቀድሞ እንደነገረን ጸረ ኢትዮጵያ እና ጸረ አማራ ትግል ነበር ያካሄደው። ሕዝቡ ልጁን እየሸኘ እየመረቀ ለጦርነቱ እሳት አንዲሆን ልኬአለሁ ሲሉ በርካታ ወላጆች በቃለ መጠይቅ ሲናገሩ በጆረየ ሰምቻለሁ። ስለሆነም የወያኔ ታጋዮችና የትግራይ ሕዝብ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ፖሊሲው በቀጥታም በተዘዋዋሪም የማይነጣጠሉ ትስስሮች አድርገዋል የምለውም ለዚህ ነው።

ጦርነቱ እና የዘር ማጥፋት ፖሊሲው የማይነጣጠሉ ትስስሮች ነበሩ የምለው የጎንደርና የወሎ መስተዳድር የነበሩ ሕዝብና ለም መሬቶች ተነጥቀው ለትግሬዎች ሲሰጥ በዕልልታ ተቀብለው እዛው የነበረው ጥንታዊ ሕዝብ በመጤ ታጋዮች እየተገፋ “ኩንታል ለመሸከምና ዳቦ መግዣ የምትሆን የቀን ሥራ” አንኳ ለመስራት “አማራ ስለሆነንክ” አይፈቀድልህም እንባል ነበር ሲል ወልቃይት ነፃ ሲወጣ ከጉዳተኞች አንደበት ባለፈው ወር ሰምተናል።  ስለሆንም ከርዕስ መስተዳደር እስከ ሁሉም የቀገጥርና የከተማ ቅርንጫፎች ኢትዮጵያን አሁን ወዳለው አደጋ ለማስገባት በመጨረሻም በራሱ ልጆች ለችጋር መዳረጉ እራሱ የራሱን ችግር በመፍጠር ጉዳይ ሃላፊነቱ የራሱ መሆኑንም መዘንጋት የለበትም እላለሁ። ትግሬነቴን ለምትክዱም ሆነ እውነታውን በመናገሬ ለምትጠሉኝ ምሁራን ሁሉ ዛሬም እንደ ወትሮው ጠምለው ነገር ቢኖር አውነታውን ከመናገር አማራጭ የለም። በመጨረሻም ለትግራይ ሕዝብ የምለው ቢኖር፤ ወያኔንና ችግሩን ላንዴና ለመጨረሻ ለማስወገድ ከዘመተው ኢትዮጵያ መከላከያ አብሮ መበዝምት ዕድሉ ክፍት ስለሆነ፤ ያንን ትግራይ ሪፑብሊክ ቅዠት አሁን ላንዴና ለመጨረሻ የማስቆም አቅሙ ስላላችሁ፤ ያንን በወቅቱ ማከናወን ነው። ካልሆነ፤ ችግሩ ይብስ እንጂ አይሻሻልም። ፋሺዝምና ብሀየረተኛነት መቸውንም የልማትና የፍትሕ አምጪ ሆኖ ኣያውቅም። ሰላማችሁን ካስከበራችሁ በሗላ ግን አብይ የተባለው ፋሺሰት ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ኢትዮጵያዊነታችሁን አክብራችሁ ከሥልጣን እንዲወርድ ማድረግ የግድ ነው። አብይ በሰለማዊ ሰልፍ ማውረድና ማስጨነቅ ይቻላል፤ ጦር መሰበቅም አያስፈልግም።

 አመሰግናሉ።

ጌታቸው ረዳ

Tuesday, January 19, 2021

“በዙ ወጪና ጊዜ የሚሻማ ቢሆንም የኢትዮጵያ ምሁራን ኢትዮጵያን እንዲያውቋት “ሃ” ብለው እንዲማሩ አዲስ ት/ምህርት ቤት ካልተመሰረተ አለን እያሉ አገሪትዋንም እየናዱ እነሱም በቁም የመፍረሳቸው ክስተት ቀጣይ ነው!” (የኢትዮጵያ ወርቅ ጋሻው) 1/19/2021 ትንተና በጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ) Ethopian Semay

 

 

በዙ ጪና ጊዜ የሚሻማ ቢሆንም የኢትዮጵያ ምሁራን ኢትዮጵያን እንዲያውቋት “ ብለው እንዲማሩ አዲስ ት/ምህር ቤት ካልተመሰረተ አለን እያሉ አገሪትዋንም እየናዱ እነሱም በቁም የመፍረሳቸው ክስተት ቀጣይ ነው!”

(የኢትዮጵያ ወርቅ ጋሻው)  1/19/2021

ትንተና በጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ) Ethopian Semay

 


ጥቅስ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ፤ ተወናይና የመጀመሪያ ኢትዮጵያዊት ዓለም አቀፍ ሞዴሊሰት የሐረር ወርቅ ጋሻው (የኢትዮጵያ ወርቅ ጋሻው)

በርዕሱ የተመለከተው ጥቅስ የተናገረቺው ከላይ የተጠቀሰው የሐረር ወርቅ ናት።እንደምናውቀው ከ1966 ዓ፣ም ጀምሮ ወደ ፖለቲካው መድረክ የተከሰቱ የኢትዮጵያ ምሁራን ራሳቸውን ሲያዩበት የነበረው መስተዋት የትምህርት ቤታቸው ዘመናዊው መስተዋት እንጂ ያደጉበት ማሕበረሰብ መስተዋት አራሳቸውን አዋህደው ለመመልከት ሰላልጣሩ በኢስያ፤ በምስራቁና በምዕራቡ አገር የቀሰሙትን ትምህርት ብቻ በመመራት ሕዝባችን እርስ በርስ እንዲገዳደልና እንዲለያይ አድርገዋል።

አስረጅ የተባለ ሎስ አንጀለስ ሲታተም የነበረ የቆየ መጽሔት የኢትዮጵያ ምሁራን ምን እንደሚመስሉ የተነጋገሩትን ጠቅሼ ላስጨብጣችሁ፡

ጥቅሱ እንዲህ ይላል፤

የሰሞኑ የሎስ አንጀለስ አካባቢ የኢትዮጵያውያን ውይይት ከኢሕአዴግ እንዴት ዲሞክራሲ ይገኛል የሚለውን ጉዳይ አስመልክቶ ነው። አንዱ የተሟጋች አይነት ‘ከወያኔ ዲሞክራሲ ይገኛል ብሎ ማሰብ ‘ቀበሮ የበሬ ቆለጥ ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል ዋለች እንደደተባለው፤ ነው፡” ብሎ ትችቱን ሊቀጥል ሲያዛጋ አንዱ የኢሕአዴግ ደጋፊ የስብሰባውን ሰብሳቢ ፈቃድ ሳይጠይቅ ከመቅጽበት ብድግ ብሎ “ወንድሜ ንግግርህ ልፊ ያላት ውርንጫ እናትዋን ተከትላ ገበያ ትወጣለች እንደተባለው አይነት ነው፡ ‘ቆለጥ’ አዲስ አበባ ላይ ወደቆ ይገኛልና ሞኝ አትሁን” ብሎ አደናገረው” ይላል መጽሔቱ ከስብሰባው የዘገበው ንግግር፡

 እነሆ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ ባለ የእርስበርስ ልፊያ እየገቡ የሕዝቡን መከራ ለ30 አመት አስፍተው አባባሱት።ያኔ ‘ቆለጥ’ አዲስ አበባ ላይ ወደቆ ይገኛልና ሞኝ አትሁን” ያሉት እነሆ ዛሬ ከ30 አመት በሗላ ዝንጀሮ ዋሻ ውስጥ ገብተው በመጫኛና በቃሬዛ እየተጎተቱ ፍጻሜአቸው በእንሰሳት አለም የሚታይ ትራጀዲያዊ ፍጻሜ ሆነው ኢትዮጵያንም በሚያስጨንቅ የገደል ጫፍ አስቀምጠዋት እነሆ ለማመን በሚከብድ “አልጋ ቢሉዋቸው አፈር ተመኝተው” በአስገራሚ ስንብት ተሰናበትዋት።

አገራችን እንዲህ ባሉ የምሁራን እንሰሳዎች እየታወከች እስከመቸ እንዲቀጥሉ በቸልተኛነት እንፈቅዳለን? በጣም ጥቂት ሰዎች አገራችን እየተናጋች ነች እያልን ጥቂቶቻችን ስንገልጽ ነበር። የጥቂቶች ድምጽ በማፈን ከፈተኛ ሚና የነበራቸው የዘመናዮቹ ባለሥልጣኖች ብቻ ሳይሆኑ በሚገርም ሁኔታ ከጠላት ጋር እየተሞዳሞዱ አሁን ላለነው አስቸጋሪ ሁኔታ የዳረጉን መሪ ተዋናዮቹ የነበሩት በተቃዋሚው በኩል የተሰለፉ ውጭ አገር የሚኖሩ የፖለቲካ መሪዎችና ብዙዎቹ የተቃዋሚ የዜና ማእከሎች/ሚዲያዎች ናቸው።

በወቅቱ እኔም ሆንኩ የሐረር ወርቅ በተደጋጋሚ ያሰሰብነው ነገር ቢኖር “ለውጥ ከመጣ እኛን የሚታገሉን ዛሬ ከኦነግና ከመሳሰሉ የነ ጃዋር አምላኪ አክረሪ እስላሞች ጋር እየተሞዳሞዱ በየ አዳራሹ ስለ አክራሪዎቹና አገር አፍራሾቹ “ስለ አፍቅሮተ ኢትዮጵያዊነታቸውን” እየሰበኩና እየመሰከሩ የነበሩ ፖለቲከኞችና የድረገጸና የራዲዮን ጋዜጠኞች የዲያስፖራውን ማሕበረስብ እያጃጃሉት ያሉ ክፍሎች ናቸው” ብለን ነበር! ያኔ ገና ይህ ለውጥ ከመታየቱ በፊት ዱሮ! ገና ድሮ!። እነሆ አንዳንዶቹ ወደ ትክክለኛው መንገድ ሲገቡ አንዳንዶቹ ግን አገር  ቤት ካለው “ኢ ቲ ቪ”  ብሰው የተረኞቹ የውጭ አገር” ኢቲቪ” ቱለቱላዎች ሆነው አረፉት። ይሆናሉ ብለን የተነበይነው ቃል እ ያልነው እውን ሆኖ አየናቸው!   

እነሆ ልክ እንዳልነው “አንዳንዶቹ የጭባሪዎቹን መጫሚያ ጫማ ሰር ወድቀው ሥልጣን ላይ እስካሉ እስከመጨረሻ ሕይወቴ አገለግለዎታለሁ ብለው ቃል ገብተው ሲሳለሙ፤ዛሬ ያ ሁሉ ግፍ እየወረደም ቢሆን ፈራ ተባ እያሉ ድፍረት አጥተው ድምጻቸውን ላለማሰማት ድምጽ አልባ “አሽከርነትን” የመረጡ “ሁለቴ የታዩ” ማፈሪያዎች እና እንዲሁም ፤ ከነዚህ ማፈሪያዎች ጋር አብረው በየአገሩ አዳራሾች እየዞሩ ‘ኢትዮጵያ በኮሎኒ ይዛናለች’ ብለው ሲሉ የነበሩት ኦነጎች ሮጠው አገር በመግባት አሁን ላለው የኦሮሙማው መሪ አጋርነታቸው በመግለጽ ተረኛነታቸውን ለማጠናከር የፋሺሰቱ መሪ “የግል አማካሪ” ሆነው፤ እነሆ እኛን ሲያፍኑና የሕዝቡን ኢትዮጵያ ሰንደቃላማ ወደ ጭቃ እየረገጡ፤ የክርስትያን ማተብ በፖሊሶቻው እየበጠሱ እነሆ ሕዝቡ በተረኛው የጅማው አገር በቀል ቅኝ ግዛት መሪ ሥር ወድቆ እነሆ ለሁለተኛ ዙር ለዋይታና ለእሪታ ዳረግዋት።

እነሆ ጥቂት የቁርጥ ቀን ልጆች ወደ ወህኒ በተረኞቹ ታፍነው ታስረዋል።  አብዛኛዎቸ ምሁራን ተብየዎች ግን ዛሬም ይህ ሁሉ የአገር ውርደት የባሰ ገፍና ልቅሶ እያዩ ጀሮ ዳባ ያሉ ብዙ በሚሊዮኖች ናቸው። ምሁራኖቹ በሕዝባቸው በነገዳቸው እንኳ ልዩ የዘር ጭፍጨፋ ግፍ ሲደርስበት ጭጭ ብለው ለ27 አመት ቃል ያለመተንፈሳቸው ሲገርምን፤ ዛሬም ሕዝቡን በማንቃትና ለዘመናት ሲሰበኩ የነበሩ የጠላቶች የውሸት ፕሮፓጋንዳ በሚያስደንቅ ብስለትና ምርምር ጠላቶቹን በሰላ ብዕሩ ያሸማቀቃቸው አቻምየለህ ታምሩ ከፌስ ቡኩ በተደጋጋሚ በሴራ እንዲታገድ ሲደረግ ምሁራኖች እና የሕግ ጠበቆች ተሰባስበው ይልተማረውን ማሕበረሰብ በመጥራት ፌስ ቡክ ዋና መ/ቤት በመምጣት ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ማድረግ አልቻሉም። እኛ ከምሁራን የምንጠብቀው የነሱ ወደ ግምባር መምጣትና እኛም በጥሪው መሰረት ድምጽ እንድናሰማ እና ሁኔታውም በሕግ እንዲታይ ያደርጉ ይሆናል ብለን ሰንጠባበቅ ዝምታን ለምን እንደመረጡ አስገርሞኛል።

 የትግራይ ሕዝብ ማፈሪያ የሆኑ የወያኔ የነ አሉላ ሰለሞን የሩዋንዳ መሳይ ጥሪ በፌስ ቡክ ሲተላለፍ አንድ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ በሕግ እንድንጋፈጠው ጥሪ አቅርቦ አንድም ምሁር መልስ ሳይሰጥ በመቅረቱ ስመለከት እውነትም የዚህ አገር ምሁራን የኢትዮጵያ ወርቅ ጋሻው እንዳለቺው በዙ ጪና ጊዜ የሚሻማ ቢሆንም የኢትዮጵያ ምሁራን ኢትዮጵያን እንዲያውቋት “ ብለው እንዲማሩ አዲስ ት/ምህር ቤት ካልተመሰረተ አለን እያሉ አገሪትዋንም እየናዱ እነሱም በቁም የመፍረሳቸው ክስተት ቀጣይ ነው!”

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ) Ethopian Semay

 

Thursday, January 14, 2021

 


የፋሽዝም ማጠንጠኛ የሆነው የትግራይ  ብሄረተኛነት በትግራይ ተወላጆች መሃል ጉልህ የሆነ የስነልቦና ለውጥ አስከትሏል!

በዚህ ሰነድ ትግሬዎች በወልቃይት ጎንደሬዎች ላይ ምን ሲሉ ነበር? መልሱን ከታች ታዩታላችሁ።

ጌታቸው ረዳ

(Ethiopian Semay ኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ)

4/20/2020 እንደገና 1/14/2021 ታትሞ የቀረበ

ይህ ጽሑፍ በመጽሐፌ ላይ የታተመ ሲሆን፤ ይህ ጥቅስ ከመጽሐፌ ጠቅሼ ለናንተው ላቀርብ የፈለግኩበት ምክንያት፤ በጣም ቅርብ የሆነ እና እንደ ወንድሜ ስቆጥረው የነበረው፤ አብሮኝ ወደ ስደትና ወደ አሜሪካም አብሮኝ የተሰደደው፤ብዙ ያሳለፍን የድሮ ወዳጄ እንኳን ለፋሲካው በዓል አደረሰህ ለማለት ደውሎልኝ ከዚያ ወደ ማይቀረው የወያኔና የአገራችን አሁን ያለው ሁኔታ አንስተን ስንወያይ ለበርካታ አመታት ስጠረጥረው የነበረውን አቋሙን በተጋጋለው ውይይታችን ላይ በድንገት ገንፍሎ ያወጣውን ጋሀድ የሆነውን  የወያኔ ፖሊሲ ድጋፉን እና ጸረ አጼ ምኒልክ መስመሩንከምላሱ ሳደምጥ፤ (ምንም እንኳ የተማረ ሰው ቢሆንም) የግንዛቤ እጥረት ሊኖረው የችል ይሆናል በሚል እሳቤበአገራችን የተጻፉ መጽሐፍቶችን እንደ ዋቢ ማስረጃ ላቀርብለት ስሞክር አማራዎች የጻፉትን ማንበብ ፍልጎት የለኝም!” በሚል  ከምላሱ አምልጦት ሳይሆን በተጋጋለው ውይይታችን በግሃድ የገለጸልኝ የብዙዎቹ ትግራይ ብሔረተኞችንነጸብራቃዊ ተመሳሳይነትዛሬም እንደገና ባልጠበቅኩት የቅርብ ወዳጄአብይ አሕመድ ለትግራይ በጀት ስለከለከለ እኔም የትግራይን መገንጠል እደግፋለሁ፤ ለትግራይ የማትሆን ኢትዮጵያ አመድ ሆና ትበታንሲለኝ፤ ይህንን የቆየውን ጽሑፌ ለማቅረብ ፈለግኩ።

 እኔም በንግግሩ በድንጋጤ ተሰምጬ እንዲህ ያለ የጫጨ አቋሙን በማድመጤ እኔም ግራይ ስትገነጠል፤ ባጀት ከኢትዮጵያ በማትፈልገዋ የበለጸገች በሪፓብሊኪትዋ ትግራይ መስራታችሁ ሰላም እስክትለኝ ድረስ ደህና ሰንብትተባብለን የበርካታ አመት ወዳጅነታችን በዚህ በመቋጨቱ፤ ብሐረተኛነት ምን ያህል አደገኛ በሽታ እንደሆነ ለመግለጽ ካሳተምኩት መጽሐፍ ልጥቀስና እናነተም ተማሩበት ይኼው።

የትግሬዎች ፖለቲካፋሺዝም እንደሆነ አምስተርዳም ኗሪ በሆነው በምሁሩ ዶክተር አሰፋ ነጋሽ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያዊ ምሁር ስለ የትግራይ ፋሺዝም እና ኦሮሞ ፖለቲከኞች ፋሺዝም መሆኑን በብቸኛው በወዳጄ ዶከተር አሰፋ ብቻ የቀረበ ሰነድ እና ከዚያም ብዙዎቹ እየተቀባበሉ የነቁበት የዶክተሩ ሰነድ እየተቀባበሉ ኢትዮጵያዊያን ምሁራኖች ተምረውበታል።

ብሔረተኛነት ማለት ደግሞ ሰብኣዊነትህን የሚነጥቅ ክፉ የመንፈስ በሽታ ነው።ፋሽዝም የተጋነነ የጀግንነትን ስሜት ያጠናክራልይላል ዶክተር አሰፋ ነጋሽ። የወያኔ ትግሬዎች ዘፈኖች የትግራውያንን ታላቅነት፤ ጀግንነት፤ የልዩ ታሪክ ባለቤትነት፤ የሴቶቻቸውን ማህጸን ቅድስናና የጀግና ልጆች ፈጣሪነት እንደዚሁም የታጋይ ገብሩ አስራት ሚስት የውብማር አስፋው በጻፈቺውእስፈንክስዋም ሞታ ትነሳለችበሚል መጽሐፍዋ እንዳለችው የትግራዉያን የወያኔ የጽናት ተምሳሌትነት በኩራት ያዜማሉ። 

ፋሽዝም በትግራይ ማህበረሰብ ውስጥ ባስከተለው የስነምግባር፤ የአመለካከት ለውጥ ምክንያት ስትመለከቱ፤ ለምሳሌ ያህል ከሰባት መቶ ሺህ በላይ (ይላል አንዳንድ ጥናት) የትግራይ ተወላጆች በኃይል ተከዜን ተሻግረው የወልቃይትን፤ የጸገዴን፤ የጠለምትን ወዘተ መሬት ሲነጥቁ በፋሽስት አመለካካት የተቀረጸው የዛሬው የትግራይ ትውልድ(ለምሳሌ የዓረናው እንደ እነአብርሃ ደስታእና የአክራሪው ወያኔ እንቁላል የሆነው የባይቶና በፋሺሰታዊ ስነ ልቦና የተቀረጸው ዓባይ ትግራይ መሪ ወጣት የሆነውክብሮም በርሀበማን አለብኝነት የሌላውን መሬት ነጥቆ በስግብግብነት ለትግሬነት ብቻ በማጠቃለል የመውሰዱን ድርጊት እንደ ሕገ ወጥና -ሞራላዊ ድርጊት አልይቆጥሩትም። እንዲያውም ይህንን ሕገወጥና ነውረኛ ድርጊት እንደ ጀግንነት ስራ ቆጥሮውት ይፎክርበታል። ለምሳሌ ወልቃይት ውስጥ ወያኔዎች ሕዝብ ሰብስበው ያስጨፈሩትን ይህንን ዘረኛ ሙዚቃ በዩቱብ አድምጡ የኔን ጽሑፍ ካነበቡ በሗላ ግን ትምክህተኛው ሙዚቃቸው ስላጋለጥኩባቸ ይህ ከታች ያለው የቪዲዮ አድራሻ ሆን ብለው ከዩቱብ አስነስተውታል።

https://www.youtube.com/watch?v=hScfnfaqLOY

  በዚህ ቪዴዩ ሙዚቃ ወልቃይት ውስጥ በብዙ ሺሕ ሕዝብ ሰብስበው የጨፈሩበት ይህ ቪዲዮከትግርኛ ወደ አማርኛልተርጉምላችሁ፡ ሁለቱ ዘፋኞች እየተቀባበሉ ያዜሙትን ፍሬ ነገር እንዲህ ይላል።ዛሬ እና ከጥቂት ወራት በፊት የነበረውን የወያኔዎች ተምክሕት እና ዛሬ በጦርነቱ ተሸንፈው በሚያሳፍርና በሚያሳዝን ሁኔታ እንዴት እንደተንበረከኩ ታይቷል። ለውርደታቸው መነሻ የሚከተለው ትምክሕት ነበር። እነሆ!

ጠላቶቻችን በቅናትምራቃቸው እንደ ራበው ውሻ   ያንጠባጥባሉ

እኛ አልፎልናል፤

ድል አድርገናል፤

ተደስተናል፤

እኛ  ያሰብነውን  ፈጽመናል፤

 ጠላቶቻችን ግን ፈዝዘው  ቀርተዋል/ይፍዘዙ!!  እያሉ ይዘፍናሉ፤ ይፎክራሉ።ሕዝቡም አብሮ በሙዚቃው ተውጦ ጦዟል፡

ደጋግሞም እንዲህ እያሉ ይዘፍናሉ--

ወልቃይት አገሬ እሷን ነበር የምመኛት፤

ዛሬ በጉልበቴ አገኘሗት

ትግራይ አገሬ

ውቢትዋ አገሬ

ጠላቶችሽ ፈዝዘው ይቅሩ፤

አንቺ ነሽ ሞራሌ፤

አንቺ ነሽ ወኔዬ፤ አንቺ ነሽ ክብሬ

የትግራይ ልጅ፤

የወያኔ ልጅ”’

በማንነቱ የማይደራደር፤

በማንነቱ የማይሳሳት….

በጥፍሩ ጥሮ ግሮ ሃብት የሚያፈራ

በጥፍሩ ጥረቱን አሳይቶ ባሸናፊነት የወጣ

የትግራይ ልጅ! ዘራፍ አለ በወልቃይት!

በደጀና በቃብቲያእሰይ ይበል የትግሬ ልጅ!

ባለ ድርብ ዋልታ።

እሷ ነበር ወልቃይት

በትግል  ወቅት የነበረች ስመኛት

አሁን አገኘሗት!

የምንመኛትን የኛዋ ወልቃይትን

ከቶ አንለቃትም

! በል የወያኔ ጎበዝ፤ እና የወያኔ ተከታይ ተረከዝ፤

ቦታ የለንም በላቸው ለትምክሕተኞች።

እሷን ለትምክሕተኞች አንለቅም።

ጣፋጭ ፍሬ የተሸከመውን

ያረገዘውን ዛፍ አንሰጥም።

 የወልቃይትን ለም መሬት ለትምክሕተኞች (ለአማራ) አንለቅም። አራስ ላማችንን፤

ፍሬ ያላት ዛፋችን

 ለትምክሕት አማራዎች አንለቅም።

 ለትምክህተኛ ኃይል አንሰጥም

 የሚለው ስንኝና ሙዚቃ የሚያመለክተን በአክራሪ ብሄረተኞች እየተገለጸ ያለው ፋሺስታዊ ልሳን ከላይ የጠየቀስኩትን በጸያፍ ቃላቶች የታጀበ የትግራውያን ፉከራ እንዲህ ይደመጥ ነበር።

የወልቃይት የጎንደር ተወላጆች ወልቃይትን ለማስመለስ ብዙ መስዋዕት ከፍለው ነበር። ፋሲስቱ አብይ አሕመድ ዛሬ የራሱን ፓርቲ ልኮ ወልቃይትና የራያ አካባቢ የትግራይ ነው ብሎ የአማራዎች ጽዋ አቆሽሾታል። የወልቃይት በጠቅላላ የጎንደሬዎች ተጋድሎ ከመንግሥት ታጣቂዎች እና ከወያኔ ታጣቂዎች እየተፋለሙ ያስመዘገቡት የቆየ ቪዲዮ እጋብዛችሗለሁ። መልካም ቆይታ።

ሰላም እንሰንብት

ጌታቸው ረዳ!!