

ስለ ፕሮፌሰር አለሜ እሸቴ ከዚህ ዓለም በሞት መየት የተሰማኝ ሐዘን ጌታቸው ረዳ getachre@aol.com March 31/2011 ፕሮፌሰር አለሜ እሸቴ በፈረንጆች አቆጠጠር March 28, 2011ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል የሚለው ዜና ethiopia.org ከተባለ የህዋ ሰለዳ ተለጥፎ አንብብያለሁ።ቀጥሎም ሳይበር ኢትዩጵያ/ዋርካ በተባለው የሃሳብ መለዋወጫ አምዶች ላይ ተመሳሳይ ዜና አንብብያለሁ። ቀጥየም የቅርብ ጓደኛየ ደውየ ስለ ዜናው እርግጠኛነት ጠይቄው እሱም መሞታቸውን እንደሰማ ነገረኝ። የነበረኝ የቤታቸው ስልክ የት እንዳስቀመጥኩት ለጊዜው ስላጣሁት ፤ዜናው በርግጠኝነት ማወቅ ባልችልም፡ እውት ከሆነ፡ ሐዘኔን በዚህ አጋጣሚ እገልጻለሁ። ፕሮፌሰር አለሜ ጣሊያን አገር ማኒላ ውስጥ ነበር የሚኖሩት። በሚኖሩበት አገር የኢትዩጵያውያን ስደተኞች ማሕበር እና የሰብአዊ ጉዳዩች ዳሬክተር ነበሩ። ፕሮፌሰሩ በጣሊያን ዩኒቨርሲቲ በሙያቸው ሙሉ ፕሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ፕሮፌሰር አለሜ በኩላሊትና በአዝማ በሽታ ሲሰቃዩ ቆይተው በመጨረሻ ተሸንፈው ወደ እዚህ ዓለም ዳግም ላይመለሱ በሞት ተሸንፈው እንደ ሆነ እገምታለሁ። ፕሮፌሰር አለሜ እሸቴ ምሁር ከመሆናቸው ሌላ አምስት ዓለም አቀፍ የውጭ ቋንቋዎች መናገር ይችሉ ነበር። የጥንታዊ እና የዘመናዊ ታሪክ ጥናቶች፤ የፓለቲካና የማሕበራዊ ጉዳይ ስነ ምርምር ሊቅ ነበሩ። ፕሮፌሰር አለሜ ከማውቃቸው የኢትዩጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ግምባር ቀደም በመሰለፍ የተለያዩ የኢትዩጵያ ጠላቶችን ባላቸው እውቀት ስለ ኢትዩጵያ ሞግተዋል።ፕሮፌሰር አለሜ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እያሉ የጻፏዋቸው የአማርኛ መጻሕፍቶች እንደንበሩ አሁን ስማቸው ከዘነጋሁት አንዲት የሴቶች ማሕበራዊ ጉዳይ ተመራማሪት ኢትዩጵያዊት እመቤት ተነግሮኝ እንደ ነበር አስታውሳለሁ። የአማርኛ መጻሕፍቶቹ ስም በውል አላስታውሳቸውም። በእንግሊዚኛ የተጻፉ ጥናቶች በርካታ ሲሆኑ ለምሳሌ Ruralness and rural transformation in Ethiopian history (1976) Cultural Situation in Socialist Ethiopia: Studies and Documents on Cultural Policies (1982) የሚሉና በመጽሐፍ መልክ እንዲታተም እዚህ አሜሪካን አገር ውስጥ የሚገኙ ኢትዩጵያውያን ማተሚያ ቤተቶችን አነጋግረው በርካታዎቹ የማተሚያ ባለቤቶች ድፍረት ስላጡ ዶክዩመንቱ በመጽሐፍ መልክ ሳይታተም ቀርቷል። እሳቸው እንደፈለጉት ያለ ምንም እርማት ወይንም የአታሚው አርትኦ ሳይደረግበት እንዳለ እንዲያትሙላቸው ከተጠየቁት መካከል አንዱ ሎስ አንጀለስ ከተማ ካሊፎርኒያ ውስጥ የሚገኝ ፀሐይ ማተሚያ ቤት አንዱ ነበር። የኢመይሉ ልውውጥ ለታሪክ እንዲሆን ፋይልህ ውስጥ አስቀምጠው ብለው የላኩልኝ ማሕደር አሁንም በእጄ አለ። በእድሜና በበሽታ እየደከምኩ ስላለሁ አዙረህ የምትጠይቀው አስተማሪ እንዳታጣ ብለው ጠቃሚ የታሪክ ማሕደሮችንም ሰጥተውኝ በክብር አሁን በእጄ አሉ። አንዳንዶቹም እሳቸው እያሉ በድረገጽ ምህዋሮች እንድለቃቸው ነግረውኝ ተለቅቀዋል። የተለቀቁ ዶክዩመንቶች የብዙ አገር ወዳድ ኢትዩጵያውያን ዜጎች የማሰብ ችሎታ እንዲዳብር ረድተዋል። እርግጠኛ መሆኑን ባለውቅም፡ የፕሮፌሰሩ ሞት ስሰማ እጅግ ከፍተኛ ድንጋጤና ሐዘን ነበር የተሰማኝ። እኔ ከማውቃቸው የታሪክ ምሁራን የተለያዩ የኢትዩጵያ ጠላቶችን በድፍረት የሚጋፈጥ ኢትዩጵያዊ ምሁር ያየሁት ፕሮፌሰር አለሜ እሸቴ ነበር።የፕሮፌሰሩ ጽሑፍ በጣም ጥልቅ ምርምር ያዘሉ ስለነበሩ ጠላቶች መልስ ለመስጠት ስለሚቸገሩባቸው ሙግታቸው በተራ ስድብ ሲሸኙዋቸው እንደነበር ይታወቃል። የታተመው መጽሐፌ ከመታተሙ በፊት በጠና ታመው እንደነበርና በማጋገም እንዳሉ ነግረውኝ በመጽሐፌ ላይ አስተያየት እንዳላቸው እንዲያክሉበት ልኬላቸው ዜናውን ሲሰሙ በጣም ደስ ብሏቸው እንደሚያነቡትና አስተያየታቸው እንደሚሰጡበት በኢመይል ነግረውኝ ሲያበቁ ድንገት ከግንኙነት ተቋረጥን።ግንኙነታችን ከተቋረጠ በኋላ አገር ወዳድ ኢትዩጵያውያን ስለሁኔታቸው የሚታወቅ ነገር እንዳለ ጠይቄአቸው እነሱም መረጃ እንደሌላቸው ከነገሩኝ በኋላ ለብዙ ጊዜ ሲጠፉብኝ በጠና መታመማቸውንም ጠረጠርኩ። ሰው ነበሩና አምላካችን አዳም ሆይ! አንተ አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ እንዳለው ሁሉ እሳቸውም ቀናቸው ደርሶ ከሆነ ተለይተውናልና ማዘን ይኖብናል። የኢትዩጵያ ልጆች በጠና ማዘን ይኖርባችሗል። ጠላቶች ደስ ብሏቸዋል፡ምክንያቱም በጥልቅ እውቀታቸው አፋቸው የስከድኗቸው እንደነበር ስለሚያውቁ እንደሳቸው ሆኖ ፊት ለፊት የሚገጥም ደፋር የታሪክ ተመራማሪ እንደሌለን ያውቃሉና በዚህ ረክተዋል። ፕሮፌሰሩ “From Baron Prochazka to Benito Mussolini "Legge Organica" the "Charter" for the Tribal Dismemberment of Ethiopia” የሚለው ጽሑፋቸው ለሕዝብ ይፈ ሲሆን ወያኔዎችና ዘረኞች ምን ያህል ራዕድ/ፍርሃት ድንጋጤ እንዳደረባቸው ጽሑፉን ያነበባችሁ ዜጎች የምታስታውሱት ይመሰልኛል። በዓይን መታወክ ምክንያት ከሕዝባዊ መድረክ ድንገት የተሰወረው እውቁ ምሁር የትግራይ ተወላጅ (ዓጋመ አውራጃ) ካናዳ ውስጥ የሚኖር ዶ/ር ሐጎስ ገ/እየሱስ ኢትዩጵያውያን ረስተውት ስንገነዘብ እኔ እና ዶ/ር አለሜ እሸቴ Where's the great Hagos Gebreyesus? Message May 8, 2007 (ጉጉል ብታደርጉት ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ) በማለት ዶ/ር ሐጎስ በሕይወት መኖሩን አወቅን። ደ/ር ሐጎስ የሚታወቀው በብዙ ትግሎችና ጽሑፎቹ ቢሆንም ከነሱ ውስጥ The Two Headed Hydra, National Self Hatred and Nihilism …" የሚለው ኢሕአፓ፤ መኢሶን ወያኔና ሻዕቢያ ያወገዘበት የብሔር ብሐረሰብ ጉዳይ ነበር። ዶ/ር ሐጎስ የፕሮፌሰሩ አውነት ሆኖ በሞት መለየታቸው ሲሰማ እንደሚያዝን እርግጣኛ ነኝ። በዚህ አጋጣሚ በቅርቡ የሚታተመው መጪው መጽሐፌ ለዶ/ር አለሜ እሸቴና ኤርትራ ውስጥ የባሕር በራችንን ላላማስነጠቅ አሰቃቂ ሞት የተጋፈጡ የምፅዋ ጀግኖችን መታሰቢያ እንዲሆን ለግሻለሁ። ፕሮፈሰር በሞት ቢለዩም ስራቸው ህያው ነውና የተቀረነው ትጋለቸውን በድፍረት ኢትዩጵያዊነትን ለማስከበር ትግላችን ይቀጥላል። እየተሰራጨ ያለው ዜና ውሸት እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ፡ ሞተውም ከሆነ ይህ የሐዘን መግለጫ ያነበቡ ቤተሰቦቻቸው እውነቱን እንደሚነግሩን ተስፋ አደርጋለሁ። መረጃ ስላልተገኘ ተብሎ ስጋታችንን ሳንገልጽ ቢታለፍ ይቆጫል። ጌታቸው ረዳ www.ethiopiansemay.blogspot.com getachre@aol.com ነብስ ይማር ፕሮፌሰር አለሜ እሸቴ
;">Obama, Cameron & Sarkozy 28.03.2011 Dear President Obama, President Sarkozy and Prime Minister Cameron, Thank you for caring about the welfare of human beings. Thank you for your concern about the safety of innocent civilians. As you will be aware, the United Nations Organization had planned, this month, to pay homage to Muammar Al-Qathafi for his human rights record, after a carefully researched report was drawn up, praising him for his tremendous humanitarian work not only in his own country but across the African continent, where he is much respected. where he is much respected. Now a question. If a group of carefully trained heavily armed citizens seized power, burnt buildings, massacred civilians and destroyed government property in, say, Texas, Northern Ireland or Corsica, what would the authorities of your countries do? Stand back with their hands over their hearts or meet the challenge with armed security forces? You do know who started the massacres in Benghazi? Another question. Where did all those former Libyan flags come from? Were they lying around somewhere in Libya for the last half-century or were they manufactured overseas, as was the Libyan "Revolution"? Actually, a series of questions. Did you know that Muammar Al-Qathafi inherited the poorest country on Earth and turned it into the best in Africa in human development indices? Are you aware of the tremendous amount of good Muammar Al-Qathafi has done and continues to do across the African continent? Were you aware that Libyans enjoy free housing? Have any of you implemented nationwide free housing policies in your countries? UN Resolution 1970 (2011) forbids the supply of weaponry to the "poor unarmed civilians" (aka armed terrorists) running amuck in Libya. Why are the "rebels" then sporting sophisticated and heavy weaponry? Why are weapons being smuggled to them through the Egyptian frontier, so conveniently secured and from the west across the Tunisian frontier, the first stage of Operation Grab Libya's oil? Who is supplying this weaponry and why is there not an independent investigation, now? UN Resolution 1973 (2011) forbids the deployment of troops in Libya. This includes special forces. What are they doing there, then? Why are they training the terrorists? As you know, a similar uprising in Iraq was put down by your friend, the Prime Minister's troops, who opened fire killing 29 in Baghdad. Why haven't your free and independent media said a word about this? What is your policy on Yemen where the military forces of your friend the President are killing poor unarmed innocent civilians? Where is the No Fly Zone over Yemen, or Bahrain? Why do you keep insisting you are not taking sides, when your air forces are bombing military columns from one side but facilitating the advance of the other? If that is not taking sides, I don't know what is. Why are you lying to your people? What justifies the strafing of civilian facilities, which goes totally against the remit under Resolution 1973? Why are you attempting to murder Muammar Al-Qathafi and his children? How would you feel if someone murdered a member of your family? You do know the origin of these wonderful unarmed civilians running around with heavy weaponry chanting Allahu Akhbar, do you not? You do also know that Muammar Al-Qathafi was one of the first figures to outlaw Al Qaeda? And you will be aware, of course, that Al Qaeda is indeed operational in Libya and has seized some sophisticated weapons systems which no doubt will be used tomorrow in a terrorist attack? And you will be aware of the role played by AQIM in the Libyan uprising of course? Nicolas can ask Chad's President Idris Deby - he speaks French. Do you speak French President Obama? Prime Minister Cameron? You do know that AQIM has links to Al Qaeda and you also realise that in helping the "innocent civilians" you are also helping AQIM and therefore recognise that you are in fact aiding and abetting Al Qaeda? The Americans will need no reminding what happens when you start arming Islamist fanatics, as per Afghanistan - the payback and thank you note was 9/11. You do know that Islamist fundamentalism has been brewing in Benghazi for decades, that many members of the "Revolution" have been trained in Afghanistan, and that Al-Qathafi had caused fury there in Benghazi by daring to declare himself against stoning of women for "adultery" and the death penalty for homosexuals? Of course you also know that he stirred up rage in Benghazi by calling the Islamic veil a "rag" and a "tent"? You will be aware that the sentiment against him in Eastern Libya is because he has been throwing Islamist fundamentalists into jail, and for daring to say Christians and Jews should be allowed to visit Mecca? Why have the Libyan information websites been taken down? Why are your governments practising cyber terrorism alongside the terrorist attacks with military equipment? How comfortable do you feel, and I address myself to Mr. Cameron here in particular, about closing down hospitals in your country while the cost of the operation is, just in flying costs, somewhere like 50.000 pounds per aircraft per hour? To help Al Qaeda set up a base at the gates of Europe? Do any of you know what in fact you are doing? Or are you driven by the desire for a war to bolster flagging support at home? You did realise that Colonel Muammar Al-Qathafi has a higher popularity rating inside Tripoli than you have in your capital cities? Once again, you have jumped the gun inventing some Quixotic cause to justify your own ineptitude and to satisfy the energy and weapons lobbies which in fact run your policies. You three are the most disgusting examples of useless, spineless incompetent wannabe protagonists who have, in Libya, shown an extremely high degree of irresponsibility. That having been said, if you want an exit strategy, here it is (because I have no doubt you are collectively unable to formulate one for yourselves). Accept the Libyan government's ceasefire, stop the campaign NOW and allow the African Union to step in and broker a deal. Stop arming terrorists, stop wasting your taxpayers' money (the bill for the Americans is already in the hundreds of millions; for the British and French many tens of millions already. How many maternity wings, how much school accommodation or medication against cancer would that fund? "Sorry Mr. Jones. We cannot continue with your treatment because the NHS does not have that type of funding. In the six hours you have been waiting to be seen, your Government has spent 300.000 on a single aircraft's sortie over Libya"). Helping Al Qaeda. Sterling job, chaps! Tell you what...you are unfit to be in your positions. If anyone "has to go" it is you three. And this time, if I receive one single death threat in my mails (which usually follow this sort of article) I shall be investigating the source. This time I shall be implacable and shall not simply delete them. Photos: "Unarmed civilians" Timothy Bancroft-Hinchey Pravda.Ru
ከአዘጋጁ፡ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ የሚለው በስሕተት ስለሆነ በስህተቱ ምትክ ዳዊት ዳባ ተብሎ ይነበብ>በዛው ሰሞን “አልጄ” የተባለ የሦስትዩሽ ድርጅት ጥምረት በኢትዩጵያዊነቱ የማያምን ውጪአዊ የሆነ ድርጅት ለአርባ ዓመት ብረት ታጥቆ ኢትዩጵያን ለማጥፋት የተሰለፈ እራሱን “ኦነግ” ብሎ ለሚጠራ ሕዝብን ለመበተን ማንኛውንም አስነዋሪ ድርጊት የፈጸመ ተራ የሽፍቶችና የፋሽስቶች መንጋ ለኢትዩጵያውያን የቀመመው መርዝ ተመልሶ እራሱን ሲበክለው ተከፋፍሎ በየፍርድ ቤቱ ሲጯጯሁና ሲጓተት ከርሞ ለይስሙላ አንድነት ፈጠርን ሲሏችሁ ሞኞቹ አልጄዎችና እነ ዳዊት የመሳሰሉ የተቃዋሚ አባል ቡድኖች ከመቸውም በላይ ደስተኞች ሆነናል በማለት ፕሮፓጋንዳችሁን ለሕዝብ አስነብባችሗል።
እስኪ ዛሬ ደግሞ “ትግሉን እየተካሄደበት በአለው መንፈስ ከመቼውም ጊዜ በላይ ደስተኞች ነን” በሚለው አቡጊዳ በተባለው መሰል ድረገጹ እንድናነብለት የለጠፈልንን የዳዊት ከበደን “ከመቼው በላይ” (ከመቼውም በላይ ሲል ማለት ከ20 ዓመት ሙሉ ከተደረጉት ትንቅንቅ ትግሎች የበለጠ ዛሬ አመርቂ ደስታ እንደተሰማው ነው እየገለጸልን ያለው ) ደስተኛነቱን የገለጸልንን እስኪ አንዳንዶቹን እንመርምራቸውና እውን “ከመቼውም በላይ ያስደሰተው ምን ይሆን?” ብለን አንድ ባንድ እንሂድባቸው።
“ካብ ክልተ ጥንሲ ከይትሕጎሲ” የሚለው የትግርኛ ምሳሌ ከዳዊት የደስታ ስሜት አንድ ሆኖብኝ ነው ምሳሌው ያስታወሰኝ (እንዳትደሰቺ ከሁለት ሰው አንድ ጽንስ አርግዢ። (ላለመሰደሰት ፍላጐት ካደረብሽ ከሁለት ሰው ባንድ ቀን አርግዢና ‘የኔ ነው የኔ ነው’ ብጥብጡ ራስ ምታት ይሆንብሻል ማለት ነው።- ናይት ሜየር የሚሉት ፈረንጆቹ ማለት ነው)ነገሩ ሳስበው፤ ዳዊት በተጠቀሰው ርዕስ ተሞርኩዞ ያስተላለፈው እንድምታ ስለ ኦሮሞ ነፃ አውጪ አንድነት ከመቸውም ቢሆን ተደሰቱ ሲለን፤ባንድ በኩል ደግሞ ትግሉን አቅጣጫ የማስያዝ ድፍረት እንዲኖረው ያስገነዝባል። ስለ ኦኖጎቹ ግልጽ ሲሆን ስለ ትግሉ አቅጣጫ ማስያዝ ሲናገር አዲስትዋን ኢትዩጵያን “ለመውለድ” ይመስለኛል።ብሩህ ተስፋ፤ ሰላም፤ ከዘረኛነት የጸዳች ጠንካራና አንድነት የሰፈነባት ኢትዩጵያ እንድትረገዝ ከተፈለገ << እንዴ?>> እንዴት እንዲህ ሊሆን ይችላል? ኦንግ ነው አዋላጁ ወይስ ኢትዩጵያውያን? የሚል ጥያቄ ያስጭራል። ኦነግ ኢትዩጵያዊ ነኝ ሲል አልተደመጠም፤አልተነበበም ፤አላወጅም። ታዲያ ሁለት ተቃራኒ ሃይላት አንዱ አፍራሽ አንዱ ገምቢ በሆነበት ወቅት “ኦነግ” ና “ኢትዩጵያውያን” ነን የሚሉ ቡድኖች ሲቀላቀሉ አገሪቱ የምታረግዘው ጉድ ምን፡ይሆን? መጪው ዘመን የሚያጠላብንን <<ፍራቻ ወይ እርግጠኛ ያለመሆን ስሜት ያላቸው የድርጅት ሰዎች ባሁኑ ሰዓት ሕዝብን ቢያወያዩ የሚማሩበት ይሆናል።>> ይለናል ወንድሜ አቶ ዳዊት ።
ወንድሜ ዳዊትን ለመጠየቅ ከራሱ ምስክርንት ልነሳ።
(1ኛ) <<የኦሮሞ ነፃ አውጪ ድርጅት አመራሮች የነበረባቸውን ውስጣዊ ችግር ላይ መፍትሄ ሰርተው በአንድ ሆነው ለመታገል ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ችግሮቻቸው ላይ መፍትሄ ሰርተው በአንድ መቆማቸው ብቻ ሳይሆን አቋማቸውን አለዝበው ከሌሎች ኢትዩጵያዊ ድርጅቶች ጋር ትግላቸውን ማቀናበር ጀምረዋል።>> የሚለው ዳዊት ማስረጃው የት አገኘው? “በኦነግና በኢትዩጵያዊ ቡድኖች በአንድ ቆመው ለመታገል ስምምነትና እንቅስቃሴው ኦነግ አቋሙን “ማለዘቡ” የምትጠራጠሩ ሰዎች ፍራቻችሁ እና እርግጠኛ ያልሆናችሁ “ፈሪዎችና ተጠራጣሪዎች” ሕዝቡን ብትጠይቁ ትማሩበታላችሁ ይለናል፡ ታዲያ ሕዘብ የሚለው አድራሻ የት እንደሚገኝ ባላወቅም ወደ ሕዝብ ከመሄዴ በፊት ዳዊት እንዲመልስልኝ የምፈልገው “በየትኛው የኦነጎች መግለጫ ነው አቋሜን አለዝቤአለሁ ያለው?” ለምን እንዋሻለን? እንዳንዋሽ በሕዝብ ስም ማሃላ ገብተናልኮ! እኔ የማውቀው የኔ እህት ጠላና ጠጅ ወይንም ቅራሪ እቤታችን ስትጠምቅ ኰምጠጥ ሲል እናቴ እህቴን ምነው አስኰመጠጥሺው? እንዲለዝብ ማር/ሱካር አስልሺው ወይንም ድፍድፍ ጨምሪበት በማለት የኰመጠጠው ጠጅ/ጠላ/ቅራሪ ለዘብ እንዲል ታደርገው ነበር። ሲለዝብ ግን ለቅምሻ ለዘብ ብሎ በማርነቱ ምላስን ያሞኝ እንጂ ኮምጣጣነቱ መቼም ቢሆን አሁንም አንጀት ውስጥ ሲገባ ኮምጣጤ መሆኑን አይተወውም።ስለዚህ አቶ ዳዊት በየትኛው መንገድና ትርጉም ነው ኦነጎች ለዘብ ብለዋልና እቀፍዋቸው እያለን ያለው? እኔን ካላመናችሁ ሕዘቡን ጠይቁት ከሕዝቡ ትማራላችሁ ይለናል። በድርጅት ውስጥ የግድ አልታቀፍክም ካልተባልኩ በስተቀር “ሕዝብ” ከሰሩት የድምር ቀመር አንዱ’ኮ እኔ ነኝ።ይህ ከሆነ ኦነግ መለወጥ ቀርቶ ለዘብተኛ ሆኛለሁ ሲል አልሰማሁም አላነበብኩም ለዘብተኛ የሚባሉ ምንና ምን አቋማቸው እንደሆኑ ዘርዝሮ አልነገረንም፤አላወጀም። ለዘብተኛ ለመሆኑ ምንድ ነው ትርጉሙ?
ኦነግ በጥሪው ወረቀት ያስነበበን <<ድል ለኦሮሞ ሕዘብ>> እንጂ ለኢትዩጵያ ሕዝብ ሲል አልተደመጠም። ዳዊትም የሚነግረንን የኦነግ ለዘብተኛነት በይበልጥ ቢያብራራልን በተሻለ ነበር። ከዓይን የሚፈጥን ከውሃ የሚቀጥን የለም ይላሉ ትግሬዎች፤ ስለ ኦነግ ለዘብተኛነት ለኢትዩጵያዊነት ምን እርባና እንዳለው ባይገልጽልንም እንዲህ ዓይነት ፈጣን የሆነ ፕሮፓጋንዳ ከምናይበት “ፈጣን ዓይን” የፈጠነ ይመስለኛል። ከምናይበት ዓይን የፈጠነ ነገር ደግሞ ማየት ስለማንችለው ሳይታየን “ይሄውና ቆሞ አይታይችሁም?” ቢለን ዓረቦቹ “ስሒር” ወይንም የእኛኑ ግዕዝ “ምትሐት” የሚባለው ድግምት ሊደገምብን የተከጀለብን ይመስለኛል።
ወንድሜ ዳዊት ስለ አንድነት ፓርቲ አመራሮች ባንድነት መቆም ተስፋ ማድረጉ የራሱ ስሜት በመሆኑ ከመቼውም በላይ ከተደሰተ እንኳን ደስ ያለህ እለዋለሁ።( እናቴ “ሳሪሃ ማሪሃ” የምትለው ዓይነት “ነገር ሳላበዛ” ማለቴ ነው)። ኢሳት ስለሚባለው በተቃወሚ ግለሰዎች የተቋቋመ አዲስ የህዋ/ሳተላይት የቴሌቪዥን ትግሉ ላይ ያበረከተው አስተዋጽኦ ሊኖር የሚችል ቢሆንም “በመለኪያነቱ” መለኪያ እና ተወዳዳሪ እንደሌለው ወንድሜ አቶ ዳዊት ከበደ አስነብቦናል። እኔ በዚህ በኩል “ሳሪሃ ማሪሃ” ሳላበዛ ባጭር ማርኛ የምገልጽበት ቃላት ያለኝ ቢሆንም “በእንተ ሞጐጐ አንጭዋ ትሕለፍ” (ምጣድ ላለመስበር ዱላ ሳልሰነዝርባት አይጧ አንዳሻት መንገዷን በኩራት ትቀጥል ነው) የሚለው የትግርኛው ብሂል ተገንዝቤ በጣቢያውን የተቀላቀሉ አንዳንድ ዜጎችን ላለመንካት ስል ተቆጥቤ “ወዲህ ቢሉት አራት ወዲያ ቢሉት አራት” የሚል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ሳይንሳዊ አነጋገር አለ! የሚሉትን ክቡር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም እኛ ትግሬዎች “ወጮ ተገልበጥካዩ ወጮ” “ወጮ ቢገለብጡት ወጮ” የምንለው ዓይነት ነው “ኢሳት” የሆነብኝ።
ጣቢያው ደግሞ ደጋግሞ የሚጋብዛቸው የክብር እንግዶቹ የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የትግልና የአገር ላገር የኡደት (ዙረት ልበለው?) ጓደኞች የሆኑት የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግምባር አዛውንቶችን ነው። አዛውንቶቹ በተከታታይ ያስተላለፉት መልክት በጣም ነዋራ እና ስድ የሆኑ ያልታረሙ አነጋገሮችን በኢትዩጵያ ታሪክ፤ባሕል፤ ደምብ፤ ትውልዶችና በነገሥታቶቿ ላይ ትንሽ ሳይሸማቀቁ የስድብ ውርጅብኝ ሲያወርዱ ነበር የተደመጡት። ከዕድሜአቸው አኳያ ፈሪሃ እግዚአብሔር ሳይኖራቸው የዘለፋና የውሸት የክሕደት ምላሳቸው በኢትዩጵያ ሕዝብ ትውልድና ታሪክ ውጭ አገር ተጠልለው የሚሰነዝሩት አስነዋሪ ንግግር ጣቢያው ምንም ሳይሰማው ኢትዩጵያንና ታሪኳን እንዲዘረጥጡ ያለ ገደብ በመፍቀድ ወደ ኢትዩጵያ ማስተላለፉ የሚያሳዝን ስራ እንጂ ከመቸውም በበለጠ ተወዳዳሪነቱ የሚሞገስበት ስራው ምን እንደሆነ ለኔ አልታየኝም።
ለ19 ዓመት የተካሄደው ትግል ሳስተውለው በተለያዩ ዋሾች እንድንማረክ የተጠመደብንን ወጥመድ በማወቅ ይሁን ካለማወቅ ቀስ በቀስ ያንኑን የ1983ቱን የዋህንት እየደገምነው እንደሆነ ምልክቶች እየታየኝ ናቸው። እውነት እንድትደበቅ አስተዋጽኦ እያደረግን እኮ ነው። ብዙ ሕይወት ያጠፉትን እንደ መላዕክት እንዲታዩ ሽፋን እየሆንን እኮ ነው። ለምን? ከሰይጣኖች ጋር ፍቅር ይይዘናል? እንዴት እንገላገላቸው እንጂ መልሰው መላልሰው እንዲገድሉን እንዴት እንዘጋጅላቸው ይባላል? ጥርስ ለሌለው የማይናከስ ጯሂ ውሻ እንዴት እንምበርከክለት? ያኦነግ መሪዎች በውሸት ዓለም በዚህ ውጭ አገር ተጠልለው ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው ሲያስተምሩ እንጂ እራሳቸው እንደ መሪ ጫካ ሄደው እንደጡበት ለሚማግዱት የገበሬው የኦሮሞ ልጅ ትግሉን እያሳዩት በግምባር ተሰልፈው ሲሞቱ አላየናቸውም። የሚኖሩት በውሸት ዓለም ለሥጋቸው ተስግብግበው ነው እየኖሩ ያሉት። ሕዝብን በሃሰት እየሰበከ እራሱ እሳት ውስጥ ሳይከት “የ ኦሮሞ ነፃ አውጪ ተወካይ እና መሪ ነኝ ሲለን” ሃሳዊ መሲህን ማክበር እኮ በባህላችንና በሃይማኖታችን ያስነውራል? ለፍቅር የማይገዙ ጥላቻን መመሪያቸው የሚያደርጉ፤አገራችን የዋሾች ደሴት እንደትሆን በፍጥነት እንዲራቡ እያደረግን ነው። አሳዘኝ!
አሁንም ክቡር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ወዳሉት ድንቅ አባባል ልመልሳችሁ። <<…ኢትዩጵያ የእውነት አገር አልሆነችም፤ከሀምሳ ዓመታት በፊት አንድ የሕንድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በዕጣ የንግግር ውድድር ላይ <<በሕንድ አገር ውስጥ በፍቅር መውደቅ>> የሚል የመነጋገሪያ ርዕስ ደረሰው፤ በሕንድ በዚያን ጊዜ ፍቅር የሚባል ነገር አይታወቅም ነበርና የሚናገረው ቢጠፋው “ፍቅር ከያዛችሁ ከሕንድ አገር ጥፉ!>> አለ። እኔ ግን መጥፋት አልሰብክም፤እውነትን እስክታገኙ ድረስ አትረፉ! ቆፍሩ! እውነት ነፃ ያወጣችሗል ተብሏልና>> ይላሉ።
ኦነጎች እስካሁን ድረስ ለኢትዩጵያ ፍቅርም አክብሮትም የላቸውም። ከኢትዩጵያ ጋር ፍቅር የያዛችሁ ከኦሮሞ ምድር ውጡ የሚሉት ለኛ ብቻ ሳይሆን ኦሮሞውቹንም ጭምር ነው። በፍቅር መውደቅ አያውቁምና “ ከኢትዩጵያ ጋር ፍቅር የያዛችሁ ሁሉ ከምድሪቱ ጥፉ” ነው የሚሉን። አይገባችሁም እንዴ!
ኦነጐች “ለዘብ” ያለ አቋም ይዘው መጥተዋል እያለን ያለው ጋዜጠኛው ወንድሜ አቶ ዳዊት ፤ ኦኖጎች ለዘብተኛ ብለው ይዘውት የመጡትና የመፍትሄ አቋም ብለው እርስ በርስ ካናከሳቸው አንደኛው “ለዘብተኛ” የተባለው ያልተውት አቓማቸው እኛኑን (በኦነጎች አባባል እኛ “አማራ አጐዎችና እኛ አጎብ ትግሬዎች (አቢሲኒያን ይሉናል”) ነፃ አንዲያወጡን (ከነጭ መሆን ወደ ጥቁር ኦሮሞነት እነሱ ኩሽ\ የሚሉትን ዜግነት) ለኛ “ለነጮቹ” የሚታገሉልን አንዱ ትግላቸውን ለወንድሜ ለዳዊት ላስነብበው ይሄውና፦ <<Genuine Ethiopian renaissance is the reversing of the negative 3000 years Abyssinization of the Cushites. Liberation of Agew-Amhara and Agew-Tigrai from this negative impact should be accompanied by the re-Cushitization movement; i.e the Oromo liberation movement should include the liberation of these two highly Abyssinized nations and to help them be re-Cushitized.>> ይሉናል ኦኖጎች። እንግዲህ እኛኑን አማራዎችና ትግሬዎች ከአቢሲኒያዊነት (አቢሲኒያ ማለት በኦኖጎች ኢትዩጵያ ላለማለት የሚጠቀሙበት በኛ የማይታወቅ ጌቶቻቸው ያስተማሯቸው የተሰጠን ስም ነው) ወደ “re-Cushitized” ዜግነት ነፃ እንዲያወጡን ነው ብያንስ “ኮሎኒያሊስቶች” ከሚሉን ሌሎቹ የነሱ ቡድኖች በለዘብተኝነት የቀረበው አንደኛው ይህንን ይመስለላል።
ይህ ፋሺስታዊ እና የደነቆረ የወረበሎች ምጥቀት ስናስበው በጣም አስቂኝ ከመሆኑ የተነሳ “ቁቤ” የነደፉላቸው የውጭ ጌቶቻቸውና ተባባሪዎቻቸው ያሰተማሯቸውን “ኢትዩጵያውያን” <<ጥቁሮች>> አይደለንም ነው የሚሉት የሚለው ጊዜው ያለፈበት ውሸት ያስተጋቡበት ለዘብተኛ የተባለው አቋማቸው አንዱ ይሄ ነው። ይሄ ደግሞ በኛ እንደበት ብንናገረው ስለማይመቻቸው በጥቁር አሜሪካኖች መሪ በማልካም ኤክስ ኢትዩጵያ የጥቁር ሕዝቦች ተምሳሌት የተከበረ ሕዝብ መኖርያ መሆኗንና የኦኖጎችና የሻዕቢያ ጌቶች የሚዘላብዱትን በእኛ የተዘረጋው ስም አጥፊ ዘመቻ ውሸት መሆኑን ካንደበቱ ያለውን ላስነብባችሁና ልሰናበታችሁ።።
<< So, I went through Khartoum to Addis Ababa, Ethiopia, which is a wonderful country. It has its problems, and it's still a wonderful country. Some of the most beautiful people I've seen are in Ethiopia and most intelligent and most dignified, right there in Ethiopia. You hear all kinds of propaganda about Ethiopia. But any time a person tries to tell you as they've told you and me, that Ethiopians don't think they're the same as we are, that's some of that man's manufacturing. He made that up ...They are just as friendly towards us as anybody else is." (G. Breitman; By any means Necessary,(London: 1985), p. 142 >> ጌታቸው ረዳ - ሳንሆዘ አሜሪካ። http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/
በአሰንዳቦ የክርስትያኖች ጥቃትና የአሜሪካው ድምፅ
አይደር ከድር በጂማ ዩኒቨርሲቲ የእስልምና ኃይማኖት መምህር ነው። የአሜሪካ ድምፅ ራዲዩ የአማርኛው ክፍል ለቃለ መጠይቅ አቅርቦት ነበር። ጋዜጠኛው አዲሱ አበበ በከፋ ክፍለሃገር (በባንቱስታዎቹ መልካአ ምድር አጠራር “ክልል”) ጅማ አካባቢ አሰንዳቦ በተባለች ትንሽ ከተማ ሰሞኑን ቁጥራቸው “ከአንድ ሺህ በላይ” የሚገመቱ እስላሞች የተካፈሉበት በየገጠሩ ባሉት 28 የክርስትያን መኖሪያ ቤቶችና 59 አብያተ ቤተክርስትያናት ላይ “በጂሃድ” መልክ በማጥቃት ተግባር እንደተሳተፉ በውጭ አገር የዜና ዘጋቢዎች በኩል በርካታ ዘገባዎች የተሰራጩትን ዜናዎች አስመልክቶ የጂማ ዩኒቨርሲቲ የእስልምና መምህር የሆነውን አቶ አይደር ከድር ሁኔታው እንዲገልጽለት ለጥያቄ አቅርቦት ነበር። እኔ የገረመኝ የመምህሩ ክስ ነው። እዚህ አሜሪካን አገር ውስጥ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዩች የተቋቋሙ በየፓልቶኩ በክረስትና እና በኢትዩጵያ ታሪክ የዘላፋ ዘመቻ አለፍ ብሎም ዘረኝነት የተሞላበት ሲያናፍሱና ሲለዛብዱ የሚደመጡ ዋሾች የሚያጉረመርሙት ዓይንት በቪኦኤው በተለይም አዲሱ አበበን የአንድ በተክርስትያን ማህብር ቦርድ አባል መሆኑና ለሃይማኖቱ የሚያዳላ እያሉ የሚዘላብዱት ሙጃሃዲኖችና ጣሊባኖች የሚከስቱን የክስ ዓይነት ቅሬታ መምህሩም አብሮ ያንኑ ቪኦኤ ላይ ቅሬታውን/ክሱን አሰምቷል።
በአዲሱ አበባ የስልክ ጥሪ እንጀምር ፡ በመጀመሪያ አቶ አይደር ከድር በአድማጮች ስም አመሰግናለሁ።የዛው አካባቢ ኗሪ ነዎት፡ ከዚህ በፊትም ሕብረተሰቡን ለማረጋጋት ብዙ እንደሰሩ ሰምቻለሁ፡መምህርም ነዎት ማለትም የእስልምና ትምህርት እያስተማሩ እንደሆነ አቃለሁ፡ባካባቢው ያለው ሁኔታ ቢየስረዱን? አይደር፡ በመጀመሪያ ቪኦኤ ላይ ያለንን Comment ሁኔታ Churchቾቹ መቃጠሉን ብቻ ሳይሆን Churchቹ ለመቃጠሉ ምክንያት የሆነውንም balanace አድርጋችሁ መናገር አልቻላችሁም። Church ተቃጥሏል፤ለመቃጠሉ በዓይናችን አይተናል፡ይኼ ነገር ከተከሰተ ከሰማን ሄድን። እኔ በአይኔ ያየሁት “Church” ተብሎ ያለው የሰበካ ቦታ ተዘጋጅቶ ገዝተው ቦታውን …(?)የሚያደርጉበት ነው። ያው ተከልሎ ብዙ ነገር ተደርጎ ፤ ያን ያክል አይደለም፤ ግቢ ያለው እንደዚያ ዓይነት ነገር አይመስለኝም ። ስንሄድ ተቃጥሏል። አንድ ተቃጥሏል። “አሰንዳቦ” ከተማ ውስጥ ሦስተኛ ደግሞ ተቃጥሏል ግን እኔ በዓይኔ አላየሁም። ይሄ መሆን እንደሌለበትም ለሕዝቡ ተናግረናል ሸሆቹም ኢማሙም ተናግረዋል።…….(?) አቶ አይደር የሚለውን እስተኪ ዘርዘር አድርገን እንመልከት። <<ቪኦኤ ላይ ያለንን Comment ሁኔታ Churchቾቹ መቃጠሉን ብቻ ሳይሆን Churchቹ ለመቃጠሉ ምክንያት የሆነውንም balanace አድርጋችሁ መናገር አልቻላችሁም።>> አብያተ ክርስትያናት እና የክርስትያኖች መኖርያ ቤቶች ከአንድ ሺህ በላይ እስላሞች በጂሃድ መልክ የተካፈሉበት የማጥቃት ዘመቻ መምህር አይደር በአሜሪካ ድምፅ አዘጋጆች ላይ ቅሬታ ማሳደሩ ጥቃቱ የፈጸሙት እስላሞች ወደው ሳይሆን መጀመሪያ ለዚህ ሁሉ ሰበብ ጠብ አንሺዎች ክርስትያኖች ናቸው ለምን ሰበቡን አትዘግቡትም ይላል፡ “ምክንያቶቹ ክርስትያኖች ናቸው” ሲል “በምስክርነት” ጥቃቱ የአጸፋ እርምጃ ስለሆነ ሕጋዊነት እንዳለው ያረጋገጠ ይመስላል። ያውም ፈራ ተባ እያለ <<ከዚያ በሗላ ተናዶ የሰሩት ስራ ትክክል ነው አይደለም እሱ ሌላ ነገር ነው። >> የሚለውን ስትመለከቱ “ትክክል አይደለም” ብሎ ማለት እንኳ መድፈር አቅቶት “ፈራ ተባ ሲል” ክርክር ውስጥ የሚያስገባ “ማኒፒለሽን ቲኦሪ” ውስጥ ይጎተታል። አስገራሚ! አቶ አይደር ከድር በማስከተልም እንዲህ ሲል የራዲዩ ጣቢያው ዘጋቢዎችን ይኰንናቸዋል እንዲህ ይላል።
<<እናንተ ጋር ያለን (ቅሬታ)፤Cause የሆነው 1ኛ ስላልተናገራችሁ ካንድ ወገን ብቻ መቀበላችሁ 2ኛ ያጋነናችሁ ይመስለኛል።>> አዲሱ ጣልቃ ገብቶ “..ተቃጥሏል… (?)፡ የሚል የማይሰማ ድምፅ ሲጠይቅ ይሰማል፡ አቶ አይደር ከድር እንዲ ሲል ይቀጥላል፡
<<መቃጠሉ የሚያጠራጥር አይደለም፤አዎ ተቃጥሏል>> 1ኛ <<መቃጠሉ ግን ይህን ያክል ተቃጥሏል የሚል ግን የተጋነነ ነገር ይመስለኛል።>> 2ኛ <<ሁለተኛ “በክርስትያኑና በሙስሊሙ መካከል ጥላቻ እንዳለ ነው የገለጻችሁት>> ጣልቃ ገብቶ አዲስ አበበ ጥያቄውን እንዲህ ይላል፡
<ጥላቻ እንዳለ ገልጻችሗል ብለዋል፡ ይሄ እንዳለ በሪኮርድ ተቀርጾዋል? አድምጠዋል?>
<<አቶ አይደር ከድር፦አልተቀረጸም፤አልተገለጸም።>>
እንግዲህ አቶ አይደር የእስልምና ሃይማኖት አስተማሪ ነው፤ እስልምና ደግሞ ቁርአኑን ለማንበብ የአረቦች ቋንቋ ማወቅ ስለሚያስፈልግ ስለማላውቅ አንብቤው አላውቅምና “እውነትን” ማስተማር እንደሚገባ የሚያስተምር እንደሆነ ግን እገምታለሁ። ከሆነ መምህር አይደር ከድር ለምን “ባንድ ምላስ ሁለት ራስ” መናገር ፈለገ?
አዲስ አበበ በማከታተል እንዲህ ሲል ይጠይቀዋል፡ ተጋነዋል ያሉትም አድምጫለሁ፡ ምን ያህል ቤተክርስትያኖች እንደተቃጠሉ እርስዎ ሊገልጹልን ይችላሉ?
አቶ አይደር፡ <<ስንት እንደተቃጠለ ገጠርም አካባቢ ስለሆነ ስንት እንደተቃጠለ ማግኘት አልቻልኩም፡ግን እናንተ እንዳለችሁት የተጋነነ አይደለም። ምናልባት 10 ከአስር በላይ..። ከዚህ ውጪ Information ላይኖረኝ ይችላል።>> መረጃ የለኝም ካለ ሌለውን ተመልሶ አጋንናችሁታል ብሎ ሲያሳጣ/ሲከስ/ሲወቅስ ዜናችሁ ተጋኗል ሲል፤ለመጋነኑ መረጃው ይሁ ነው ብሎ መረጃ ካላመጣ “ተጋኗል” ብሎ መክስስ ሁኔታንና ራስን defense mechanism ውስጥ አስገብቶ minimization ጥቃቱን አቃሎ እንዲታይ ሽፋን ፍለጋ መግባት ነው። ባጭሩ “defense mechanism” ማለትም ‘መካድ”/Denial ውስጥ ለመከናነብ ፍለጋ ነው።
ዜናው የሚለው ይህ ጥቃት ሕብረተሰቡን ያካተተ ጥቃት ነው። አቶ ከድር እንዳለው በቤተሰብ ይነት የተነሳ ግጭት አይደልም። የሃይማኖት ግጭት ነው፤ ጥላቻ ነው! ክህደት ማለትም ፈረንጆቹ Denial የሚሉት defense mechanism የክህደት መንገድ Sigmund Freud Ytbalwe የተባለው አውሮጳዊ የስነ ኣእምሮ ሊቅ እንዲህ ያቀርበዋል “ in which a person is faced with a fact that is too uncomfortable to accept and rejects it instead, insisting that it is not true despite what may be overwhelming evidence.” አንድ ሰው ከእውነት ጋር ፊት ለፊት ሲገጥም፤ የማያጠራጥር መረጃ እያየም ቢሆን የፈለገው ይሁን ተቀባዩ ጭብጡ እንደጋሬጣ ስለሚወጋው እውነታውን ላለመቀበል አላምንበትም ሲል ይጋፈጣል።” አቶ አይደር የእስልምና ሃይማኖት መምህር ሆኖም ይህ እውነታ ላለመቀበል ተጋኗል ሲል እንደገና አልተጋነነም ሲል እውነታው እየተጋፈጠውም ቢሆን እንደገና ጥቃቱ ወደ ማሳነስ በመግባት minimization ወደ ሚሉት ክርክር ሲገባ ይደመጣል። minimization - admit the fact but deny its seriousness (a combination of denial and rationallization) ይህ ምን ማለት ነው፡-ድርጊቱን መፈጸሙ (ጸ/ላላ ብሎ ይነበብ) ማመን - የድርጊቱ ከባድነት ግን ማሳነስ” ማለት ነው። በክህደትና በማመን መሃል መዋዠቅ ማለት ነው። ይሄ ደግሞ ለተከሰተው ሁኔታ እጅግ በጣም በሳላ ሚዛን አይደለም። ይህ ምን ለማሳየት ነው? Projection የሚባል ነገር አለ። Projection ከውስጡ የጥፋቱን ከባድነት አምኖ ሃላፊነት ላለመቀበል መሸሽ ነው። ይህ ደግሞ ከላይ እንደተመለከታችሁት - ለጥቃቱ ሰበብ በአቶ አይደር ቃላት “cause”መነሻው ክርስትያኖች መስጊድ ግቢ (?) ሽንት ስለሸኑ ለጥቃቱ “cause”መነሻው ራሳቸው ስለሆኑ እሳለሙ ተናዶ የክርስትያኑን አጥቅቷል ነው የአይደር አባባል። ጭሱ ሳይሆን ሃላፊው እሳቱ ነው። እሳቱ ሳይሆን ሃላፊው ለኳሹ ነው cause ነው፡ causeዙ ደግሞ ክርስትያኑ ነው፡ አናዳጁ ክርስትያኑ ተናዳጁ እስላሙ ስለሆነ “ተከሰተ”። ነው ምመህር አይደር እያለን ያለው።
ሕብረተሰቡ ውስጥ ለ19 ዓመት እየተስፋፋ የመጣው የሃይማኖት እና የጐሳ ግጭት እንደዚህ ዓይነት ዲፌንሲቭ እና ክሕደት በአጠቃላይ በሕብረተሰቡ መንፈስ ውስጥ መኖር እንኳን ለሊቃውንት ለኛ ለተራ ዜጎችም ግጭቱ ቀላል እና ቤተሰባዊ እንዳልሆነ ማረጋገጥ አያቅትም። ፈረንጆቹ እንደሚሉት general existence of denial is fairly easy to verify, even for non-specialists መላት ነው።. ሌላው የገረመኝ የተዋህዶዎቹን ቤተ ጸሎት ልተወውና የፕሮተስታነቶቹ ቤተ ጸሎትም ምምህር አይደር ከድር እንዴት እንዳናናቀው ተመልከቱ ፤ እንዲህ ይላል፡ <<እኔ በአይኔ ያየሁት “Church” ተብሎ ያለው የሰበካ ቦታ ተዘጋጅቶ ገዝተው ቦታውን ጸሎት የሚያደርጉበት ነው። ያው ተከልሎ ብዙ ነገር ተደርጎ ፤ ያን ያክል አይደለም፤ ግቢ ያለው እንደዚያ ዓይነት ነገር አይመስለኝም >> እንዲህ ዓይነት አስበዋሪ ግምገማ ከአንድ የዩኒቨርሲቲ የሃይማኖት ምምህር አንደበት ሊወጣ የሚጠበቅ ነው”? ግቢ ስለሌለው ተቃጣለ የታበለው “Church” ተብሎ ያለ ያን ያክል አይደለም ማለት ምን ማለት ነው”? መስጊዶች ዛፍ የላቸውም፤ ግቢ የሌላቸው መስጊዶችም አሉ፤ ታዲያ ግቢ ስለሌላቸው ያን ያክል አይደለምና ቢቃጠልም “መስጊድ’ መባል የለበትም ማለት ይቻላል? ምንም ይሁን ምንም እነኚ ዜጎች ገዝተውም ይሁን ተከራይተው “ጸሎት የሚያደርሱበት ነው። ሲቃጠል እንደ ቤተክርስትያን አታስቡት ማለት ምን ይሆን ትርጉሙ?
ከዚህ በታች ያለውን የጅማ ዩኒቨርሲቲ የእስልምና ሃይማኖት ምምህር አቶ አይደር ከድር ያለውን ተመልከቱና ፍረዱ፡ እንዲህ ይላል። <<እናንተ! ይሄ ሊከሰት የሚችል ነው አብሮ የሚኖር ሕዝብ በቤተሰብ ጭቅጭቅ ይነሳል፤ በቤተሰብም አባት በልጅ መካከል ቅጭት ሊሆን ይችላል..ይሄ Exeptional እንጂ ሁሌም በሙሰሊሞችና በክርስትያኖች ያለ ልዩነት አይደለም።>> ጂማ ውስጥ በተከታታይ፤ ሐረር ውስጥ በተከታታይ እና ሌሎች ቦታዎች ለ19 ዓመት ሙሉ የተካሄዱ የጎሳ ግጭቶች ዝርዝር እንዘርዝር ቢባል ብዙ ጥራዝ መጽሐፍቶች የሚያስጽፍ ነው። መምህሩ minimization ወደ ሚባለው ጨዋታ ባይገቡ አዋቂነት ነው። በዚህ ድረገጽ ማለትም ኢትዩጵያን ሰማይ ድረ ገጽ ወደ ቀኝ በኩል በመጀመሪያ ረድፍ የተለጠፈው ጅማ ውስጥ በ1998 ዓ.ም በክርስትያኖች ላይ የተከሰተው ጥቃት የተቀረጸው አሰቃቂና አሳፋሪ ቪዲዩ ይመልከቱና (ከዚያ በፊት በርቀት ዘመን የተደረገው አሳፋሪ ስራ ሳናወሳ ማለት ነው፦የቅርቡ እንኳ በወያኔ አስተዳደር የተደረጉት ተከታታይ ጥቃቶችቹ ስንመለከታቸው) ጥቃቶቹ የቤተሰባዊ ግጭት ይመስላሉ? መምህረ ከድር Exeptional እንዳለው እንዲህ በቃላሉ Exeptional ተብሎ የሚገለጽ ነው? አላህ ይማራችሁ! አመሰግናለሁ ጌታቸው ረዳ “የኢትዩጵያን ሰማይ” ድረገጽ አዘጋጅ። ይድረስ ለጐጠኛው መምህር ጥቂት ቅጂዎች አሉ ለማንበብ የፈለጉ በ408 561 4836 ይደውሉ። http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/