ከአዲሰ ደምጽ አዘጋጅ ከወንድሜ አበበ በለው የተጠየቅኩት ጥያቄ የሰጠሁት አስተያየት፡
ከጌታቸው ረዳ
(Ethio
Semay ድረገጽ አዘጋጅ)
4/4/25
የተለጠፈው ፎቶ ከዘመነ
ፋኖ ሌላ መንቀሳቀስ የለበትም በሚል ዕብሪተኛ ባሕሪ ‘አምና ሳይወዱ
ተከብበው’ ከሌላ የፋኖ ተዋጊ ሃይል ወደ ዘመነ ካሴ ፋኖ እንዲቀላቀሉ የተገደዱ በዘመነ ምክትል “አስረስ ማረ” ጀብደኛነት ሳይወዱ
‘ዘመነ መሪያችን ነው የሚል ምሃላ ሲያሰፈጽማቸው ነው።
ሰላም አቤ፡
በስልክ እንዳናግርህ
ስለ ጠየቅከኝ፤ ዛሬም በስልክ ላናግርህ ባለመቻሌ ዛሬም ከፍተኛ ይቅርታ እየጠየቅኩህ፤ ስለ አምሐራ (ፋኖ እንቅስቃሴ) ፤ ስለ ትግራይ
ሁኔታ እና ስለ አብይ ያለኝን ሃሳብ እንዳካፍልህ ስለጠየቅከኝ እያመሰገንኩ ባጭሩ ሃሳቤ እንደሚከተለው ነው፡
1) ስለ
ፋኖ
2) ስለ
ፋኖ እና ትግራይ ግንኙነት እንዲሁም ስለ ትግራይ ሁኔታና ኤርትራ ጉዳይ…. በዚህ ልጀምር፡-
የፋኖ አነሳስ ግልጽ ነው። <<ለ50
አመት ሕልውናው ጥያቄ ውስጥ ስለገባ ብቻ ሳይሆን፤ የዘር ማጥፋት ወንጀል <<እንደ ሰው ፤ እንደ ዜጋ፤ በክብሩ፤ በሕይወቱና በኑሮው>> ሆን ተብሎ በመንግሥት (በኦሮሞ/በትግራይ)
አክራሪ ፖልቲክኞች በታቀደ መንገድ ጥቃት ተፈጽሞበታልና ያንን ልማሰቆም በስንት
ቅስቀሳ ቀስቅሰን ወጣት አምሐራና ምሁር <<ተነስ ራስክን ተከላከል፤ ሕዝብሕንም ከአደጋ ተከላከል> ብለን ወጣቱና ምሁሩ እንዲሁም ሚዲያው ስንቀሰቅሰው “እምቢ ብሎን” በመጨረሻ ጽዋው ከሞላ
ቢቆይም “ጽዋው ሞልቶ መሰለኝ”
ወደ ጫካ ጠመንጃ ትግል ገባ። ይህ በኔ በኩል ስመኘውና ስቀሰቅሰው የነበረ ምኞቴ ስለነበር በዚህ ረክቻለሁ።
ፋኖ ጫካ ከገባ ወዲህ ግን የተስፋየንበት ተስፋ ሳይሆን ቀርቶ <<በብሐረተኛነት ርዕዮት የተመራ >> “ለስም ገናናነት” “በትንንሽ ጭንቅላቶች” እየተመራ፤ እርስ በርስ በክ/ሃገርና በአብሮ አደጌነት ተቧድኖ መዘላለፍ፤ መተራመስና መገዳደል ጀመረ። ተነሳ ሲባል ዘጭ አለ! ተዳከመ!
እስካሁን ድረስ መላውን
“ክልል” ቀርቶ አዲስ አበባን ክብቦ ማስጭነቅ ይችል የነበረው ዕደ’ል ሳይጠቀምበት ቀርቶ በሚገርም
ሁነታ ጠላት ካዳከመው ይልቅ
እራሱ በተከተለው ባሕሪ ትግሉ እንዲረዝም ምክንያት ሆነ (በተለይ የጎጃም “ዘመነ
ፋኖ” በተባለው የመንደር አጉራ ዘለል የሚመራ ታጣቂ ምከንያት)።
በጣም የሚገርም አዲስ ክስተት ያየሁት ደግሞ “የጎጃም የዘመነ
ካሴ ፋኖ” <<ዘመድኩን በቀለ>> በሚባል ዕብድ መመራቱ ‘ፈረንጆች” Odd/strange/ የሚሉት በኢትዮጵያም ሆን በየትም ዓለም የሽምቅ ተዋጊዎች
ታሪክ ተሰምቶ፤ ታይቶና ተደርጎ የማያወቅ ከመሬቱ በብዙ ሺህ ኪ/ሜ ርቀት ሌላ አህጉር ውስጥ (አውሮፓ/ጀርመን) የሚኖር
አንድ <<ናርሲስት>> ግለሰብ
ድርጅቱን እንዲያሽከረክረው “ክፍት” እንዲሆን መፍቀዱ ሌላው አስገራሚውና
ለድክመቱ ሁለተኛው ምክንያት ሆነ።
አሁንም ከጎጃም ፋኖ ሳልወጣ “ቀዳሚው ለድክመቱ ተጠያቂ ግን ድርጅቱንና የሕልውና ጥያቄ ጠልፎ በራሱ የዝና አጥር ውስጥ እንዲቀረጽ
ምክንያት የሆነው ግለሰብ አስቀድሜ የጠቀስኩት <<ዘመነ
ካሴ>> የተባለውና ምክትሉ (አስረስ ማረ) ናቸው።
እነዚህ ግለሰቦች አምሐራን ለማዳን ጠመንጃ ታጥቀው ቢወጡም “ያሳዩት ባሕሪ ግን” የትግሉን ፈር የሳተ “ስነ ምግብር” መከተላቸው
በትግሉ ሕይወት ላይ አደጋ የሚጥል ፤ ንጹሃን መምህራንና አዛውንቶች
እያፈነ መግደሉን ምክትሉ በቃሉ ሲናገር
ሰምተናል።
ከግለሰቡ (ከዘመነ ካሴ) የጎጃም ጫካ መንግሥትነት (አጉራዘለልነት) ውጭ የሆኑ “ገጠሮችም” ሆኑ “በሥሩ ያልሆኑ የፋኖ ታጣቂዎችን”
እና በአካሄዱ የተለዩት “ግለሰቦች”ነ “ጋዜጠኞች” “ምሀራን” እያፈነ
ማሰር፤ ማሰቃየት፤ ሽማግሌዎችና ቀሳውስት እንዲሁም እናቶች በእምብርክክ እያስኬደ አንዳንዱንም መረሸኑን በፎቶ የተደገፉ ማስረጃዎችም አሉ።
ከዚያ አልፎ ለብዙዎቻችን ያስደነገጠ “የዘመነ ካሴ አጉራዘለል ባሕሪ” በምርጫ መሸነፉን ሲያወቅ ፤ ለአንደነት የተሰበሰቡትን የፋኖ
አመራሮች ሁሉ እንዲበተኑ ምክንያት በመሆን ምንም ያልበደለውን ምስኪኑ “እስክንድር ነጋ” ላይ ከ አሳንስ
የስድብ ውርጅብኝ አልፎ <<የመግደል ዛቻ>> መሰንዘሩ ትግሉ <<በዚህ ይጫካ በጋሚዶ ውጣት አምራር መክንያት>> ትግሉ መጠለፉን ማመንና ትግሉ “አንድ እርምጃ ወደፊት ሊሄድ የሚገባው ትግል ሦስት እርምጃ ወደ ሗላ ጎትቶታል”። ይህንን ማመን አለብን።
ወንድሜ አበበ ሆይ!
ቅር ሊልህ የሚችል ከሆነ ይቅርታ አድርግልኛና “ዘመነ ካሴ ማለት” የፋኖ ታጋይ
ሳይሆን <<ከተራ ወረበላ ታጣቂ ባሕሪ ያልተሻለ ለትግሉ እንቅፋት ነው ብየ ደምድሜአለሁ>>። ልጁ በምክር የሚስተካከል
አይደለም።
ዕብሪተኛነቱ መጠን ያለፈ ስለሆነ በቀላሉ የሚስተካከል አይደለም። እኔ እንደ ትግራይ ተወላጅነቴ
የትግራይ ፋሺስት መሪዎች ባሕሪ ከውልደታቸው እስከ ሞታቸው ድረስ ያለው ባሕሪያቸው ሳይሰልቸኝ አጥንቻቸዋልሁ። ብጎጃሙ ዘመነና ምክትሉ
ትመሳሳይ ባሕሪ አይቻልሁ። ዘመነ ኢሳያስ አፈወርቅ
የሚመሳስል “የከረረ ናርሲዝም” ያንጸባርቃል። ይህ ወጣት “የፋሺዝም
ባሕሪ ያጠቃው የትግሉን
ምንነት ብቃላት እንጂ ሥራ ላይ እንዴት እንደሚተገበር የልተረዳው እጅግ
ዕብሪተኛ ነው” ብየ ደምድሜአለሁ።
ይህ ያልተገራ ባሕሪው የ70 ዎቹ ባሕሪ
ይመስላል። እሰክንድር ላይም ሆነ በሌሎቹ ሰዎች የማፈን ፤ የመግደልና የማስፈራራት ባሕሪ
የልጁ ንጋሪ ባሕሪ ነው። በዚህ አልተወሰነም።
ይህ ሰው ትዕቢት የወጠረው <<አምሐራዊ ብሔረተኛ ፋሺሰት>> ነው።
ብዙ ጽሑፎች ይህንን በሚመለከት ስለጻፍኩ ያንን በድረገጼ ብታየው ጥሩ ነው።
አክራሪ ብሔረተኛነቱ አጅግ ስለበረታበት <<ሥልጣንና መሪነት የሚተረጉመው “ሲወለድ
ከናቱ ማሕጸን እና ከዘሩ በሕልምም በውንም የመጣ ነው ብሎ ደምድሟል። ይህ ዓይንተኛ የፋሺዝም ምግልጫ ዋናው ምልክት ነው። የፋኖ
መሪነት በራሱ ሥር ብቻ የሚንቀሳቀስ ታጣቂ ካልሆነ ሌላ ታጣቂ አካባቢው ላይ እንዲኖር እንደማይፈቅድና እንደማይራራለት “በእሳት
ሁሉ እያቃጠለ እንደሚፈጃቸው ጭምር ተናግሯል”። ይህ አባባል ከአብይ አሕመድ ንጉሥ የመሆን
ምኞትና ጭካኔ የተለየ አይደለም።
የዚህኛው እንዳውም “መሪነትንና ንግሥና በሕልም ትንግርት የሚነገር ፤ ከማህጸን
እና ከዘር (ከDNA) የሚገኝ ነው ብሎ የሚያምን Typical የናዚዎች” ባሕሪ በመሆኑ የጎጃሙ የዘመነ ካሴ ፋኖ
ለቃላቴ ቅር ካላለህ <<የአምሐራ ፋኖ እንቅስቃሴ የፋሺስት ብሔረተኛ>> ትግል ወደ መሆን ቡቃያው እየበቀለ ነው የሚል እምነት
አለኝ።
ልጁ ላደረገው
ጥፋት (ወንጀል) እና አካሄዱ አምኖ እርማት ካልወሰደ (በጨዋ መልክ ስለ ትግሉ ብሎ ሸብረክ ይላል የሚል እምነት የለኝም) እሱ
የሚመራው አመራር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ሊያመዝን ነው። ብግልጽ ለመናገር ፤ ድርጅቱ በዕብሪት የተወጠሩ “የልዕለ ጎጃሜነት ስሜት” ያሰከራቸው ግለሰቦች ስለሚመሩት ፤ ድርጅቱ
እንዴት እንደሚስተካከል ሳስበው ለኔም ያስጨንቀኛል። ስብራቱ ሰፊ ነው ጽናቱን ይስጣችሁ ስል እያዘንኩ ነው!
ስለ
ወሎ ፋኖ አንድ ነገር ልብል፡
የወሎ ፋኖ የሚዘወረውና የተጠለፈው አሁንም በዘመነ ካሴ ስለሆነ የወሎ ፋኖ
ጤንነት ሊሻል የሚችለው ድርጅቱ ከዘመነ ካሴ አላቅቆ እስክንድር ነጋ ጋር
“የትግል - ዕርቅ” ካልፈጸመ ይባስኑ ከጎጃም ፋኖ አመራር በባሰ መልኩ በአውራጃዊነትና በሃይማኖት
ውጥረት ውሎ ውስጥ መግባቱ አይቀሬ
ነው፤ (ኦል ረዲ ምልክቶች እያየሁ ነው)።
ወሎ ውስጥ በፋኖ “ምሕረቱ ወዳጄ” (ምሬ ወዳጄ) የሚመራው “ፋኖ” ሳጥናው፤ ሰውየው “የፖለቲካ
ሀ ሁ” ስለማያውቅ እስክንድር ላይ እጅግ የከረረ ጥላቻና ስም በማጠልሸት ዘመቻየ ተጠመደ ማሃይም ግለሰብ ስለሆነ የዘመነ ቅርንጫፍ ወሎ ላይ በቅሎ ታያልህ። የተግረምኩበትና
የደነገጥኩበት አንድ የቅርብ ክስተት ደግሞ ይሚከተለው ነገር ነው። መአዛ መሐመድ ትባላለች (ጋዜጠኛ) የምሬ ወዳጆ ያገሩ ልጅ ነች። ታዲያ ልጅቷ እዚህ አሜሪካ ትኖራለች « እንዲህ ስትል በፌስ-ቡክዋ ጽፋለች፡
«ሌላ የፋኖ ድርጅት ወሎ ውስጥ መኖር የለበትም “መጨፍጨፍ አለበት” ብላ የጻፈች “አዲሲትዋ ዩዲት ጉዲት” “መአዛ መሐመድ” ነች። ልጅቱ የሮሃ ሚዲያ ባለቤት ነች። ምሬ ውዳጆ ማሃይም በመሆኑ ይህች ጋኔል ሴት የምትሰብከውን ሁሉ ስለሚሰማ
በሌሎቹ ፋኖዎች ላይ ቶክስ በመክፈት ትግሉ
ፈሩን ለቆ ወደ እርስበርስ መጠፋፋት እንዳይገባ
እሰጋለሁ።
ምሬ ወዳጆ <በደመነብስ>
የሚጓዝ ስለሆነ ሚዲያዎች እንዲህ ያሉ “በደመነብስ” የሚጓዙ ፋኖዎች
ለምሳሌ እንደ የጎንደሬው <<ሽማግሌው መሳፍንት>> እና ወሎየው <<ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞ>>
የመሳሰሉት ሰዎች ሚዲያዎች እነዚህን ማራቅ አለባቸው (ስለ ውግያ ማብራሪያ እንዲሰጡ በሚመለከት ካልሆነ በስተቀር ስለ ድርጅታቸው
ያለው ሁኔታና ፖለቲካ እንዲናገሩ መፍቀድ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል)
ስለ
ሸዋ ፋኖ በሚመለከት፤
ሸዋ ወስጥ ሁለት ፋኖ ያለ ይመስለኛል። አንዱ እስክንድር ውስጥ ያለው ሲሆን
ሌላው ማን እንደሚመራው አላውቅም (ግን ያው ልክ እንደ ወሎው በዘመነ ካሴ የተጠለፈ ድርጅት ነው የሚል ግምት አለኝ። እና ስለዚህ
ድርጅት ብዙም የምለው የለኝም)።
ስለ እስክንድር ግን እንደምታውቀኝ ሁሌም እኔ እስክንድር ማለት በጨለመቺው ሃገር የሃገሪቱ መብራት ሆኖ ለሌለው እያበራ ለራሱ እየተቃጠለና እንደ ሻማ እየቀለጠ ያለ አስገራሚ
የዘመናችን አርበኛ ነው ከማለት ብዙ አልሄድበትም። በዚህ ሰው ላይ እየደረሰ ያለ የስም ማጥፋት ዘመቻ
በትግል ዘመኔ እንደ እስክንድር
ያለ <<የተከዳ የሰው እየሱስ>> አይቼ አለውቅም።
ባጭሩ እግዜር ከክፉ ይጠብቀው ብየ ስደመድም።
ወደ ሌላው ርዕስ ከመግባቴ በፊት ስለ ፋኖ አጠቃላይ አንድ ነገር ልብልና ልደምድም።
ፋኖ አሁን ካለበት ችግር ለመውጣት እያቆጠቆጠ ያለው <<ከአምሐራዊ
አክራሪ ብሔረተኛነትና አውራጃዊ/ክሃገራዊነት>> ስሜት እራሱን ማላቀቅ አለበት። ይህ ክስተት እየታየ መሆኑን ማመን ለእርማቱ
አንድ መንገድ ጠራጊ ነው። አድበስብሶ ከታለፈ ብሔረተኛነት አደጋ ስላለው በጥንቃቄ ቢታይ።
ብሔረተኛ መጀመሪያ የሚበላው እራሱ ነው። ለዚህ ነው <<የአምሓራ
ብሔረተኛነት>> <<ብሔረተኛ
ነኝ>> ብሎ ራሱን ስላሳመነና ስለሚከተል <<ንጹሕ አምሐራና የአምሐራ ጭምብል ያጠለቀ አምሐራ መሳይ>>
እያለ እርስበርስ እየተናቆረ ያለው።የብሔረተኛነት መጨረሻው
ማረፊያው የት ነው ብትለኝ፤ ልክ የወያኔዎች ዕድል ይገጥመዋል።
አመሐራው ለሕልውና ቢታገልም ወያኔ በቀደደለት የብሔረተኛነት ስሜት መግባትና
መቀስቀስ የለበትም። ሥርዓቱ ፋሺስት ስለሆነ ትግሉ የሕልውና ትግል ሆኖ ሃገር በቀል ጸረ ፋሺዝም ትግል ነው ፋኖ ራሱን መምራት
ያለበት (ድርብ ጭቆና እና ድርብ ትግል)። እኔ አምሐራ ብሔረተኛ ነኝ ካልክ ጨዋታው እና ምቱ ይቀየራል ማለት ነው። ብሐረተኛ ውጫዊውን
(አካባቢውን) እንደ ራሱ አይመለከትም። ቀስ እያለ እየጠበበ ወደ ውስጥ ብቻ ነው እንደ Snail ወይንም እንደ ኤሊ ወደ ውስጥ የሚሸመረረው።
ሌላው ነገር ፤ ፋኖ መሬት ላይ ባሉት በሳል አመራሮች እንዲመራና እንደ ዘመድኩን
በቀለ የመሳሰሉ “ጨርቃቸው የጣሉ ናርሲስቶች”
መራቅ አለባቸው። ችግር እየፈጠረ ስላለው ዘመነ ካሴ እንዴት ይሰተካከላል የሚለው በኔ አስተያየት ልጁ ባንድ አጋጣሚ ራሱ ክትግሉ ካላገለለ (የማየታስበ
ቢሆንም) በጦርነት ወይንም መገመት
በማልችለው አጋጣሚ ሕይወቱን አጥቶ ከትግሉ ካልተላቀቀ፤ ልጁ ትዕቢተኛና
ደም የጠማው “ችግር ፈጣሪ” ነውና <<ጽናቱን ይስጣችሁ>>።
ሌለው ሜዳ ላይ የሚታገሉ የፋኖ ተመራቂዎችና ጠቅላላ ለሕዝብ ስብሰባ ንግግር
የሚያደርጉ ብዙዎቹ ያደመጥኳቸው በሙያቸው “ወታደሮች/ ኮማንዶዎች/
የነበሩ በአምሐራነት “ዕብሪት” የተወጠሩ ትምክሕት ከምላሳቸው እንደ ውሃ የሚፈስ ጠባብ ብሔረተኛነትን
የሚሰብኩ “የፖለቲካ ዕውቀት” የሌላቸው “ምሊታንት” ብቻ ሆነው አይቻቸዋለሁ። ብዙዎቹም
በድምጽ የተናገሩትን የቀዳሁዋቸው ብትሰማ ትሸማቀቃለህ። ስለዚህ እነዚህ
በወታደራዊ ስልጠና ብቻ እንዲያሰለጥኑ እንጂ በሕዝብ ፊት ወይንም ለታጣቂዎች የፖለቲካ ትምሕርት እንዲሰጡ ባይደረግ ጥሩ ነው።
እያልኩ ስለ ፋኖ እና ትግሬዎች (ወያኔዎች) ግንኙነት ስለጠየቅከኝ አንድ ነገር
ልብል፡
ፋኖዎች ማዶ ካለው ሕዝብም ይሁን ድርጅት ከማተኮር መጀመርያ ራሳቸውን አጥርተው
ወደ ማዶ ክመመልከቱ ትቆጥበው ቅድምያ በራሳችወ ዙርያ ቢሰጡ
ጥሩ ነው። እርስበርስህ አንድ ሳትሆን ከሌላው ጋር አንድ ልሁን ብሎ መቃዠት ከቅዠት አያልፍም (ጨቅላነትም ነው)::
ወያኔዎችም ሆኑ ትግሬዎች ስለ ፋኖ ያላቸው አመለካከት ስለጠየቅከኝ ጉዳይ፤-
ትግሬዎች/ወያኔዎች/ (ትግሬዎች ስል ሕዝቡ የሚመራውና የሚያመልከው ወያኔ ስለሆነ
አንድም ሁለትም መሆናቸው ስናገር የማይጥማቸው ሰዎች አሉ- ያ ግን ብዙ ጊዜ ከተነተንኩት ትንታኔ ውጭ ያፈረሰው ሌላ ማስረጃ የለም። ይህንንም ላብራራልህ ከፈልግክ ሌላ ቀን በሰፊው ልልክልህ
እችላለሁ)፤
ትግሬዎች ፋኖን የሚመለከቱት እንደ <<ሌባ፤ማይካድራ ላይ ትግሬን
የጨፈጨፈ የወንጀለኞች ስብስብ፤ የጠላት ድርጅት…» እያሉ
ነው የሚመለከቱት እንጂ እንደ የወዳጅ ድርጅት አያዩትም።
ለዚህም ምክንያታቸው፤ አንደኛ “ፋኖ” የአምሐራ ድርጅት ነው። ስለሆነም አምሐራ
ማለት የትግሬ ጠላት ነው ብለው ለዘመናት የተሰበኩበት ርዕዮት ስለሆነ ድርጅቱ (ፋኖን) እንደ ተቀናቃኝ ያዩታል። አምሐራ አንዲደራጅና ታጥቆ እንዲያዩት አይሹም፤ ምክንያቱም ለመገንጠል
አጀንዳቸውም ሆነ “አገር ሲሆኑ” ወደ ሱዳን በር መውጫ ሊጠቀሙበት የወረሩት የወልቃይት መሬትና አካባቢው አምሐራዎች ከታጠቁ እንቅፋት
ይሆንብናል የሚል ጠንካራ እምነት አለቸው።
አምሐራዎቸ ይዋሕንታቸው ይገርምኛል። ወያንይዎች ፤ ሻዕቢያና ቡችላዎቻቸው አምሐራዎች እንኳን
መታጠቅ ቀርቶ ጭራስ <<አብይ አሕመድ>> ፋኖን እንዲያጠፋላቸው ከፍተኛ ምኞታቸው ነው። ልብ ብለህ ከተከታተልካቸው
“የልብ” <<ግንኙነታቸው>> ከኦብነግ ፤ ከኦነግ
እና ከአገው ሸንጎና ከመሳሰሉት ጸረ አምሐራ ድርጅቶች ጋር ነው። እነዚህም የሚፈልጓቸው “ፋኖን” ለማዳከም ተጨማሪ ሃይል ነው ብለው
ስለሚያምኑ ነው።
ለምሳሌ “መኮንን” የተባለው ድሮ ኢትዮጵያዊ ነኝ እያለ
እስከ አሜሪካ ድረስ መጥቶ ጭምብሉን ሳያወለቅ ኢትዮጵያውያንን ሲያሞኝ የነበረ የሰቆጣ ተወላጅ ነኝ የሚል የአገውኛ ዘፈን ዘፋኝ (በነገራችን ላይ እኔ
አገዎች የሚያቀነቅኑትን ዘፈንና እስክስታቸው አምሓራዊ እንጂ የአገው አይደለም የሚል እምነት
አለኝ። ምክንያቱም የአገዎች እስክስታ የሚወዛወዙት <<ጃንጥላ
ይዘው በቂጣቸውና ከሽንጣቸው በታች ነው>> የሚወዛወዙት እንጂ በትክሻቸው የሚመቱት እስክስታም ሆነ ቋንቋ አምሐራዊ ነው።
ይህንን ካሁን በፊት አንድ ጽሑፍ አቅርቤአለሁ)፤
የሆኖ ሆኖ ይህ ዘፋኝ ከመጀመርያ ጀምሮ በድብቅ <<ከወያኔዎች ጋር>>
ግንኙነት እንደነበረውና የወያኔ በዓል ያከብርና ይዘፍንላቸው እንደነበር አንድ ሰነድ ሰርቼበት ነበር (ታስታውስ እንደሆን)፤ ከዚያም
በ2010 ጦርነቱ ከተጀመረ በሗላ ጭምብሉን አውልቆ <<የተምቤን አገው ነኝ እያለ ከተምቤን አገዎች ጋር ሸርኮ አገውኛ
እየዘፈነ ትግሬዎችን እያስጨፈረ <<እኔ ወያኔ ነኝ>> እያለ <<አምሐራን ሲዘልፍ>> ነበር።
ከዚያም አገው ተዋጊዎች ጋር ሆኖ በጦርነቱ ወቅት ወያኔን
ወግኖ በፕሮፓጋንዳው ሲፋለም ነበር። ይህ ሁሉ የሚያሳይህ ትግሬዎች አገው የሚባል እና ቅማንት የሚባል ሰው ሁሉ ጸረ አምሐራ እንዲደራጅ ትግሬዎች ክልብ እየጣሩ ነው (አንተም ይህንን
የምታውቀው ነገር ነው)።
ስለዚህ ፋኖ መደራጀትና መታጠቅ ማለት <<የትግሬዎች
ሃገርነት>> እንቅፋት ነው ብለው ስለሚያምኑና እንደልባቸው የአምሓራን ሕዝብ ወደ ድምበሩ እየገቡ እንደዘወትሩ መዝረፍም
ሆነ ለማሸማቀቅ፤ እንደማይችሉ ስለሚያውቁ፤ በተቻላቸው ሁሉ <<ፋኖን>> እንዲኮላሽ ምኞታቸው ነው።
ትግሬዎች አምሕራንና ፋኖን የሚያዩት
<<የነዚያ የማረክናቸው ልጆች>>
የነፍጠኛ ልጆች ከማለት አልፈው አዲስ ስም ሰጥተው <<ፎጣ ለባሽ>> <ጨፍጫፊ>>
<<ዘራፊ>> እየሉ ስም በማጥፋት እንደ ነፃ አውጪ
ሳይሆን እንደ ዘራፊ እንዲታይ የአብይ አሕመድ ፕሮፓጋንዳ ህያው እንዲሆን ይሰራሉ።
እናንተ አትሰምዋቸው እንደሆነ አለውቅም እንጂ ምሁራኖቹ
ሁሉ በዚህ ተጠምደዋል (ጥቂቶቹ አብይ አሕመድን ለማዳከም ፋኖ አንፈልገዋለን ብለው በታክቲክ እዚህም እዚያም ሊኖሩ ይችሉ ይሆናል፤ ብዙዎቹ ግን ጸረ ፋኖ ናቸው)።
የሚያሳዝነው ግን ምንጩ ባላውቀውም የወያኔ ዘፈኖች ወደ ፋኖ ለውጠው ሲዘፍኑና የፋኖ መሪዎች ፎቶ
ሲለጥፉ አይቻለሁ። ያ በጣም የወረደ የበታችነት ስሜት የሚያሳይ የብሔረተኛ ባሕሪ አሳያ ነው።
ባጭሩ ትግሬዎች ስለ ፋኖ ያላቸው አመለካከት ፋኖን (አምሓራን) የሚያዩት እንደ
ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያን ለማቆየትና ለማጠናከር
የቆመ ድርጅት ነው ብለው ስለሚያምኑ የሚጠልዋትን ኢትዮጵያ ሳይወዱ ፋኖን የሚወዱበት ምክንያት አይታየኝም። ኢትዮጵያ
የሚባል ክርና ማግ ሁሉ እንዲበጣጠስ ይፈልጋሉ። ለዚህ ነው ኦነጎችን፤ አገዎችና ቅማንቶችን እያባባሉ ለ50 አመት የቆዩት።
ጌታቸው ረዳ ከትናንት በስትያ በትግርኛ ለተሰብሳቢ ሕረዝብና ለደጋፊዎቹ የሰጠው
ቃለ መጠይቅ ልተርጉምልህና የኤርትራም የትግራይም ሁኔታ አንድ ነገር ይነግርሃል። በተለይ ስለወ ወልቃይት (ፋኖን አብረህ እየው)፡
ጌታቸው
ረዳ እንዲህ ይልላል።
<<ዓለም በኛ ጉዳይ ላይ እኛ እንደምንፈልገውና
የኛን ዓላማ ደግፋ እኛን የምታስታውስበት ሁኔታ የለም። ምክንያቱም ትላልቅ ዝሆኖች አሉ በዚህ ጉዳይ ውስጥ የገቡ።
የቀይ ባሕር ምዕራባዊ ወሰኖች ማለት ከዚያ ጀምሮ እኛ እስከ
ምንገኝበት (ትግራይ ጭምር) እነዚህ ዝሆኖች እኛን ለመቆጣጠር ባላቸው ሃይል ሁሉ እየተሽቀዳደሙበት ነው።
ምዕራባውያንም ዓረቦችም… ሃይል ያለው ሁሉ ያንን አካባቢ
ለመቆጣጠር እየተሽቀዳደሙ ናቸው።እኛ በዚህ ውስጥ እመሃል ላይ ተቀርቅረናል።በነዚህ ዝሆኖች ሳንደፈጠጥ ወይንም የነሱ ጠላቶች ሳንሆን
የዚያም ወይንም የዚህ ጠላትን ወዳጅ ሳንሆን ሳንደፈጠጥ ለመውጣት እንዴት መውጣት እንችላልን የሚለው ማሰብ ይገባናል።
የሁሉም ወገን ወዳጅ ብንሆን ጥሩ መንገድ ነበር፤ ሆኖም
የግድ አማራጭ እንድንወስድ ለምን እንገደዳለን?
እኔ የሚያሳስበኝ የትግራይ ሕዝብ ባላመነበት ጦርነት ተመልሶ
እንደገና ግዳጅ (ተጠቂ) እንዳይሆን ስጋት አለኝ።
የኤርትራ መንግሥት ራሱን ለመከላከል የትግራይ “ግማሽ መሬት”
እይዛለሁ በሚልበት ወቅት እኛ ምን አሰብን? የፌደራል መንግሥት የኢትዮጵያ ድምበር ማስከበር አለብኝ ሊል ይችላል። እነዚህ ሃይሎች
ይህንን የየግል ዓላማቸው ለማስከበር ሲንቀሳቀሱ በእኛ ዘንድ የሚከሰተው ክሰተት ምን ይሆን? የሚለው ለኔ በአያሌው ያሳስበኛል።
“ኤክሰትሪም ቾይዝስ” ቅርቃር ውስጥ በምንገባበት አስገዳጅ
ምርጫ ላለመግባት እንዴት ብለን ከዚህ ቅርቃር ወጥተን ራሳችንን እንዴት ማዳን እንደምንችል መስራት ይኖርብናል።
እኔ የማውቀውና ሁሌም በውጭ ሃይሎች የሚጠይቁኝ ጥያቄ አለ።
በሱዳን ፖለቲካ ሳይቀር “ተራ” አለብን። ስደተኞቻችን እዛው ይኖራሉ። እነዚህ ስደተኞቼ እንዴት ወደ ቦታቸው ላስመልሳቸው የሚል
ቁጣና ፍላጎት አለው። ትላልቅ ሃገሮች ሳይቀሩ ማንን ነው የምትደግፉት (ሱዳን ውስጥ ያለው የርስ በርስ ውግያ ማለቱ ነው) እያሉ
ይጠይቁናል።
ስለዚህ እኛ የትግራይ መሪዎች እንደ መሪዎች act ብናረግ
ኖሮ አሁን የተፈጠሩት ቀውሶችና አሳሳቢ ሁኔታዎች የምንወጣባቸው ዕድሎች ከመድረሳቸው በፊት ልንወጣቸው እንችል የነበሩ ዕድሎች እያመለጡን
ነው።
ሌሎች (ከትግራይ ውጭ ፌደራል መንግሥቱንም ማለቱ ነው)
በሚወስኑት ውሳኔ የትግራይ ሕዝብ ቅርቃር ውስጥ እንዲገባ ፍላጎት የለኝም ብቻ ሳይሆን አቅሜ በሚፈቅደው መጠን ይህንን ቅርቃር
(Avoid) ላመስወገድ እሰራለሁ።
እኔ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ያለኝ ግንኙነት ሌላ ግንኙነት
ሳይሆን <<የፕሪቶሪያ ስምምነት>> በማስፈጸም ላይ ያተኮረ ሰላማዊ ግንኙነት እንጂ <<ዓሰብ የማስመለስ፤የሱዳን
መሬት የመዋጥና የመጋፋት፤ ወይንም የመንን ለመቆጣጠር የሚባል ግንኙነትም ይሁን ንግግር የለኝም።
ስለዚህ 1.5 ሚሊዮን የትግራይ ተወላጅ የሚናርባት ኢትዮጵያ
፤የኢትዮጵያ አካል መሆናችን ብቻ አይደለም፤ የኢትዮጵያ አካል ባንሆንም ቁጥር Matter (ሚዛን አለው) 1.5 ሚሊዮን የሚኖርበት
አካባቢ የሚደርስበት መጪ አደጋ እሱን ለመከላከል በቂ ዝግጅት ሳናደርግለት እንዲበጠበጥ አልፈልግም።ለምነስ ይበጥበጥ?
ስለሆነም ከሁሉም ጋር ሰላም መፍጠር አለብን። የዓለም መሪዎች
እኛ ዘንድ እየመጡ አሜሪካ የሚጠይቁን አውሮጳኖች እየመጡ የሚጠይቁን ለምንድ ነው እንደ መንግሥት ተደራጅታችሁ የማትንቀሳቀሱት እያሉ
ነው የሚጠይቁን።
የተወሰነ ቡድን TPLF leadership ውስጥ እኔ እንደማውቀው በጣም ጥቂት
ግለሰቦች አመራር ውስጥም ሊኖሩ ይችላሉ፡ አድማና ብጥብጥ የሚሹ አሉ። እኔ እስከማውቀው እና ስንቀሳቀስ በነበርኩበት ሁሉ አሳውቅ
ነበር። መንግሥትም ከጀርባ እንመታሃለን የሚል አልነበረውም። እንዳውም
የመጀመሪያ (initiative) (ገፊ አስነሳሽ ሆኖ) ለምን አታገኛቸውምና አታነጋግራቸውም የሚል ግፊት የመጣው ከጠ/ሚ አብይ አሕመድ
ነው።
አንዱ በዚያ አንዱ ከዚያ ጋር ዝብርቅርቅ ባለ የተለያየ
ግንኙነት በመከሰቱ ምክንያት ባለመደራጀታችን ሳናስበው ሳንደራጀበት ለአደጋ የምንጋለጥበት ዕድል ግን ሰፊ ነው። አሜሪካኖች አውሮጳኖች
የሚጠይቁን ለምንድነው አንድ ሆናችሁ የማትሰሩ እያሉ ሲጠይቁኝ “እኔም ችግሩ እያወቅኩትም ቢሆን” “አንድ ነን እያልኩ እከላከላለሁ”።
እየሆነ ያለው ግን ያ አይደለም።
ባልተደራጀ አደረጃጀት እየተጓዝን ግማሹ ከፋኖ ግማሹ ከአዲስ
አበባ ፌደራል መንግሥትጋር እኔ የማላውቀው ግንኙነት የሚያደርጉ ቡድኖች አሉ።
እኔ እሻልሃለሁ የሚሉ ከአዲስ አበባም ይሁን ከአስመራ ከመቀዲሾ
፤ ከካርቱም ፤ ከምስር (ግብፅ) ጋር ያልተደራጀ ቅንቅስቃሴ ማድረግ በመጨረሻው እኛን “ያጠፋል”።
አንዳንዱም <<ወርቅ>> ለመሸጥ ሲል
በትግራይ ሕዝብ ስም ከሌሎች ሃገሮች ጋር ግንኙነት የሚያደርጉ አሉ። ይህ በትግራይ ሕዝብ ስም እየተንቀሳቀሰ ያለ ይህ ቡድን ችግር
እንደሚፈጥርብን አውቀን “በትግራይ ሕዝብ ስም ሊንቀሳቀስ የሚችል ሕጋዊ አካል <<የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ብቻ ነው>>።
ይህ በየማዕዝናቱ 2 ጀኔራል፤ 2 2 ኮለኔሎች፤ 2 ከንቲባ፤
2 ፖሊስ 2 አስተዳር 2 ፕረዚዳንት፤ 2 ፖሊት ቢሮ 2 ማዕከላዊ ኮሚቲ. ወዘተ… እየተሞከረ ያለ የአስተዳደር ሽሚያ የትግራይ ሕዝብ
አደጋ ላይ የሚጥል ዕድል እየሰፋ እየመጣ ነው።
እዚህ አካባቢያችን እየተንቀሳቀሱ እና እየተጋበዙ ያሉ
Acters <<ተዋናያን>> ከኛ ዕውቅና እና ቁጥጥር ውጭ ናቸው። ስለዚህ ከዚህ <<እየመጣ ያለው አውሎ
ነፋስ>> እንዴት እናመልጣለን ብለን የማይቀር አደጋ መምጠቱም አይቀሬ ነውና እንዴት እንከላከለው የሚል የማምለጫ መንገድ
እንኳ ምንም የሃሳብ ውይይት ሲነሳ አላይም።
አሁን እየተረባረብንበት ያለው አስገራሚ ነገር ወረዳዎችና
ጣቢያዎች ላይ ነው። እርግጥ እነዚህ ለሰላምም ለልማትም፤ ለአንድነትም ለማነቀቃቃት “ማገር” ናቸው፤ ሆኖም አሁን እየተከሄደበት
ያለው በወረዳና ጣቢያዎች ላይ ሕዝቡን ለመከፋፈልና ለመበተን እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ግን ሕዝባችን ይበልጥ ለአደጋ የሚያጋልጥ
እንጂ ከአደጋ የሚከላከልለት እንቅስቃሴ አይደለም እየተከሄደ ያለው እንቅስቃሴ።>>
ሲል ጌታቸው ረዳ ለተሰብሳቢ ሕዝብና ለጋዜጠኞች በሰጠው
ቃለ መጠይቅ።
ስለ
ኤርትራ ጉዳይ፤
እንደምታውቀው ኢሳያስ ሃገራችን ሳያፈርስ የሚተኛ “የጠላቶቻችን ተላላኪ የሆነ የገዛ
የወላጆቹን አገር ኢትዮጵያ የካደ ይሁዳ” ስለሆነ፤ ማንኛውም ክፉ ነገር ከመሞከር አይቆጠብም።
ጦርነት ይነሳል የሚል
ግን እምነት የለኝም። ሁለቱም የየራሳቸው ችግር አለባቸውና ለጉራ እንጂ በተግባር አያደርጉቱም ። ሆኖም አንደ ልማዱ “ኢሳያስ መተንኮስ
ከጀመረ “አሁን እኛ እጃችን አናስገባም” የሚሉ
የወያኔ አዛዦችና ወታደሮች ሳይወዱ ጦርነቱን ይሳተፉበታል (ምናልባትም አንዳንድ የፋኖ ድርጅቶችም እንዲሁ- አብይም ፋኖን ለመከፋፋል
ይጠቅመዋል)። ምክንያቱም ጦርነቱ ከተጀመረ በባድመና ዛላምበሳ አዲግራት ኢሮብ ከሆነ እዛ ያለው ሕዝብ እየተደበደብን ዝም ብላችሁ
ልታዩን ነው እንዴ ብሎ ወያኔዎችን ስለሚቃወም፤ ወያኔዎች ሳይወዱ ጦርነቱ (ድንገት ከተከሰተ) ይቀላቀላሉ።
ሆኖም፤ አብይ ወደ ትግራይም በዓፋርም ለመንቀሳቀስ ትልቅ የፋኖ አደጋ ስለሚገጥመው ከኤርትራም ሆነ ከትግሬዎች
ጋር “ጦርነት” አይሞክረውም
(Self suicidal ነው) ።
ስለ የትግራይ ሕዝብ ሁኔታ ግን ጌታቸው ረዳ የሰጠው ስዕል
በማየት ትግራይ ማዕበል እያዋከባት ያለች
ጀልባ ስለሆነች ከዚያ መረዳት ትችላልህ። ለወደፊቱ ግን ትግሬዎች ከወያኔ አመለካካት ይርቃሉ ወይ የሚለው ጥያቄ
ስመልስ “አይላቀቁም””
“ሌላ ትውልድ” መወለድ ይጠበቃል የሚል እምነት ስላለኝ ያንን ሰነድ በሌላ ቀን አልክልሃለሁ።
አመሰግናለሁ
ወንድምህ
ጌታቸው ረዳ Ethio Semay 408 561 4836