Wednesday, March 19, 2025

በዋሃቢያው ጂሃዲስት ቡድን ባለበት ተፈልጎ እንዲታረድ መስጊድ ላይ እና መስቀል አደባባይ የታወጀበት እፎይ የተባለው ልጅ ጉዳይ! ጌታቸው 3/19/25


በዋሃቢያው ጂሃዲስት ቡድን ባለበት ተፈልጎ እንዲታረድ መስጊድ ላይ እና መስቀል አደባባይ የታወጀበት እፎይ የተባለው ልጅ ጉዳይ!

ጌታቸው

3/19/25

            The scary development of extreme wahhabism in Ethiopia!

ወደ ጉዳዩ ከመግባቴ በፊት ዋሃቢ የሚለው ቃል ልግለጽ። ውሃቢ/ሰለፊ/ መነሻው ሳዑዲ ዓረቢያ ነው። በዛው ምድር (ሥርዓተ መንግሥት) ሁለት ግንዶች አሉት። ፖለቲካዊው እና ሃይማኖታዊ

የሳዑድ ቤተሰቦች ፖለቲካዊው/መንግሥታዊው ዘርፍ ሲቆጣጠሩ የአብደል ወሃብ ቤተሰብ ደግሞ “አውልያው” (ቤተ ክሕነቱን/ሲኖዶስ እንደምንለው) በበላይነት ይቆጣጠሩታል።

ዋሃቢው Mutaween /መጠዊን/ የተባለ የራሱ ፖሊስ አለው። (መጠዊን) እስልምናውን ለማራመድ እና ማንም ሰው ከዛው ዕምነት እንዳይወጣ የሚቆጣጠር በክርስትያን አማኞችም ሆነ በሴቶች ላይ ምሕረት-የለሽ አውሬነት የተላበሰ ተቆጣጣሪ ፖሊስ ነው

 በነዳጅ ገቢ የሚገኝ ዶላር/ፔትሮ ዶላር/ የሚውለው በውጭ አገር የሚገኝ እስላም እና ክርስትያን ወደ ውሃቢ/ሰለፊ እምነት ለመለወጥ እና ለማስፋፈት ያውሉታል።

በዋሃቢስቶች ትንታኔ ሁለት የሰው ልጆች አሉ ይላሉ። አንደኛው «ትክክለኛ የእስልምና አምልኮ ያላቸው፣ የተመረጡ፣ ያሸነፉ» የሚሏቸው ሲሆኑ ሁለተኞቹ ደግሞ «ቃሪፎችና/ቃፊሮች/ እና ሙሽራኮች» የሚሏቸው እንደ ክርስቲያኖች፣ አይሁዶች እንዲሁም ዋሃቢስቶች የማይደገፉትን እንደ መውሊድን ማክበር የመሳሰሉ ስርዓቶች የሚከተሉ ሌሎች ሙስሊሞችን ያካተተ ነው። ባጭሩ የሌሎችን እምነት አክብሮ፣ ተስማምቶ የመኖር ነገር በነርሱ ዘንድ በፍጹም የማይታሰብ ነው።

ከታች በፎቶግራፉ ላይ የምታዩት አክራሪው ዋሃቢያው <<ኦርቶዶክስን እናጠፋለን>> የሚለው እና <<ፋኖና ማሕበረቅዱሳን ካልፈረሱ ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን>> የሚለው ማስረጃ ክርሰትያንን በማረድ የተደራጀ የዋሃቢው ክፍል ነው።

ይህ ቡድን የተፈጠረበት ምድር ሳዑዲ ዓረብ እና ፓኪሰታን የኢትዮጵያን ነባራዊውን እስልምና ወደ ዋሃቢና ሰለፊ እምነት እንዲከተል “ነባሩን የእስላም ማሕበረሰብ” “እጅግ አክራሪ እንዲሆን” ሰይጣናዊ ተልዕኮአቸውን በመበከል ላይ ናቸው።ከነዚህ እንደምሳሌ ሊጠቀሱ የሚገቡት

ሳድቅ መሐመድ (ኡስታዝ አቡ ሓይደር)

የተባለው አጅግ ዓለም አቀፍ ሽብርተኛነት ሊሰት መመደብ የሚገባው አክራሪና <<የኢትዮጵያን ቤተክረስትያናት ባያችሁበት ሁሉ በእሳት አጋይዋቸው>> ፤ <<ክርሰትያኑን እረዱ./…>> <<ከግርማቸውና ከሐጎስ ወይንም ወልደስላሴ የሚለው የኩፋሮች ስም የያዙት ጋር ወዳጅነት አትፍጠሩ>> እያለ ዩቱብ ላይ ምንም የማያውቁ የዋህ ወጣት እስላሞቹን (በተለይ ምስኪን ወጣት ሴቶችን) እየሰበከ የሚገኘው ውሃቢዎቹ በሚሰጡት ስንቅ እየተመገበ  በጥገኝነት ሱዑዲ ዓረብ የሚኖር “ኢትዮጵያዊው “አይሲስ”

እንዲሁም አቡበከር አሕመድ የተባለው ሌላው አስመሳይ

<<ዓለም እስላሞች ሲያስተዳድሯት ሰላም ነበረች፤ ኩፋሮች ከያዝዋት በሗላ ግን ተበጠበጠች>> እያለ እስላማዊ ቅኝ-ግዛት (እስላማዊ ኢምፔሪያሊዝምን) የሚሰብክና የሚመኝ አስመሳይና “ቅዠታም”

አክራሪው ያልተወላገደ ጥሩ አማርኛ የሚናገር በትውልዱ የዓፋር ተወላጅ የሆነው ወሎ ያደገው “አቡበከር መሐመድ” እና

በዋሃቢነቱ መንትያ የሆነው ሌላው  ጓደኛው ጸረ ክርስትያኑን ‘’ግራኝ አሕመድን’’ <<የነፃነቴ ምልክትና የነጻነታችን አርበኛ>> እያለ መጽሐፍትን የጻፈ አክራሪው አሕመዲን ጀበል ነው።

አሕመዲን ጀበል ማለት በተመራማሪው ሊቅ አቻምየለህ ታምሩ አገላለጽ

<<የኦነግ የፖለቲካ ታሪክ ደራቹ የአሕመዲን ጀበል ተልዕኮ በሃይማኖት ስም የኦነግን የፈጠራ ታሪክ እየደገመ ኢትዮጵያውያንን በተለይም ኢትዮጵያውያን-ሙስሊሞችን በኢትዮጵያዊነታቸው እና በኢትዮጵያ ላይ እንዲያምጹ ማነሳሳት ነው። በደረታቸው የፖለቲካ ድርሰቶቹ ሁሉ ለማጉደፍ ያልሞከረው የኢትዮጵያ መልካም ታሪክ የለም። በሃይማኖቱ ሙስሊሞ ሆኖ ሳለ የኢትዮጵያን እድሜ 100 ዓመት አድርጎ ኦነጋዊነቱን ለማጽናት ሲል ብቻ በሰው ሃይማኖት በክርስቲያኖች መጽሐፍ በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ገብቶ የተጠቀሰችዋ አገር ኢትዮጵያ እንዳልሆነች አድርጎ ለማቅረብ የክርስቶስ ሐዋርያትን ሳይቀር አላዋቂ አድር ለማቅረብ የሚቃጣው ካድሬ ነው ።>> ባጭሩ

 ኦነጋዊው አሕመዲን ጀበል>> ስንመለከት፤ እስላሙን ለማነሳሳት እንዲመቸው

<<«የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሳይሆን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሙስሊሞች» እንባል ነበር ብሎ «ሦስቱ አጼዎችና ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች» በሚለው ድርሰቱ ውስጥ ያቀረበው ትርክቱ የሚገርም ነው። «ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሙስሊሞች» የሚለውን አገላለጽ የራሱን ትርጉም ሰጥቶ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እንደ ኢትዮጵያዊ አይቆጠሩም ነበር ያለን ሰውዬ እሱ ራሱ ግን LTV ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ «ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሙስሊሞች» ሲል ይደመጣል!>> ሲል አቻም ስለ ሰውየው ዓይን-ዓውጣ ውሸት አጋልጦታል።

በተጠቀሱ እስላማዊና ዓረባዊ አገሮች ሄደው በሥራም ሆነ በኑሮ የኖሩም ሆኑ እው እየሄዱ ቁርኣኑን የተማሩ ወጣት እስላም ኢትዮጵያዊያን ሴቶችና ወንዶች ብዙዎቹ አክራሪ እስላም ሆነው በመምጣት “አነጋገራቸው ጺማቸውባሕሪያቸውባሕላቸውአለባበሳቸው፤ “ዓረባዊ” በመሆን ሃገርን በማበጣበጥ ሳይመቻቸው በማድፈጥሲመቻቸው “በግሃድ” ብጥብጥንና ግድያን ያጎለብታሉ።  ስለ አክራሪው ውሃቢያ መጠነኛ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ይህ ካልኩኝ ወደ ርዕሱ ልግባ።

ባለፈው ሰሞን “እፎይ” የተባለ ኢትዮጵያዊ  እስላሞች የሚያመልኩት “በቁርኣንና ሃዲስ” መጽሐፋቸው ውስጥ <<መሐመድ የሕጻን ልጅ የወንድ --- ሞጭሙጯል>> ብሎ በማለቱ  የመሐመድን ስም በጸያፍ ቃል ሰደብኸዋል ብለው ባለበት እንዲታረድ አክራሪ ውሃቢዎቹ  በመሰጊድም በዩቱብም “ጂሃድ” አውጀውበታል።

በሌላ በኩል ልጁ “ሞጨሞጨ/መጠመጠ” ከማለት ይለቅ “ሳመ” የሚለው ለማለት ስለነበር ስለ ቃላቱ አቃቀሜ ስሕተት  ይቅርታ እየጠየቅኩ ደርጊቱ ግን የተጻፈና እኔን ለመሞገት የሚፈልግ “ኡስታዝ” ለመከራከር ዝግጁ ነኝ”  ብሏል እፎይ የተባለው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ወጣት።

በሌላ ወገን ደግሞ “ሕጋዊ መጅሊስ አይደለም” ሲባል በብዙዎቹ ወሃቢያዎች ግን የተደገፈ “ሕጋዊ መጅሊስ ነው” ተብሎ በኦነጉ አብይ አሕመድ የተሾመውና <<ስለሾምኩዎት እኔን ይወዱኛል? አዎ! ወይም አልወድህም! የሚለው አንዱን ይምረጡ>> እያለ አስቂኝ የህጻን ባሕሪው ደጋግሞ አዳራሽ ውስጥ በሕዝብ ፊት ዓለም እየሰማው የተጠየቀው አዲሱ ተሿሚው “ኦሮሙማዊው የመጅሊስ ተጠሪ” እፎይ በተባለው የቁርዓንና ሃዲስ ጥቅሶችን እየጠቀሰ የሚከራከራቸው ወጣት “ሕጋዊ ክስ እንደመሰረተበት ብቻ ሳይሆን (ታስሮ የተፈታ ይመስለኛል፤ ካልተሳሳትኩኝ) እኝህ መሪ “ዩቱብ ላይ” ያስተላለፉት መልዕክት እንደ ወጣቶቹ አስጸያፊ ቃል እየተጠቀሙ ልጁን ሲሰድቡና ንትርክ ውስጥ ገብተው አድምጬአቸው እፎይም <<እንደ እርስዎ የመሰለ ትልቅ አዛውንት እና መሪ ጸያፍ ስድቡን ትተው መከራከር ከቻሉ በጨዋ ይምጡና ይከራከሩኝ>> በማለት መልስ ሲሰጣቸው አድምጬ ገርሞኛል። እሳቸውም ከመከራከር ይልቅ ወደ ክስ መሄድ መርጠዋል።

ሌላው አስገራሚ የታዘብኩት ጉዳይ መስቀል አደባባይ በሺዎቹ የሚቆጠሩ እስላሞች <<እፎይ ይገደል>> እያሉ በማቸው ዕለት ተሰልፈው አዲስ አባባን ቀውጢ ሲያደርጓት እና “የአላህ ቤት ነው” ብለው እስላሞች የሚጸልዩበት መስጊድ ውስጥ በሥርዓት የእስልምና መዝሙር እየተዘመረ <<እፎይ የተባለ መልኩ እንደዚህ አከላተ ቅርጹ እንደዚህ ..የመሰለ በቅርቡ ይገደላል>> እያሉ ጂሃዲስቶቹ ያወጁትን አስደንጋጭ የግድያ አዋጅ ለመሸፋፈን እንዲመቻቸው <<ይገደል>> የሚሉት እስላሞች Tekbir Media - ተክቢር! በሚል ፌስቡክ የሚታወቀው  ሥራዩ ብየ የምከታተለው ታላቅዋንና ሰፊዋን ሃገር ያስታቀፉት ነገሥታቶቻችንን ስም በማጠልሸት የተጠመደው ይህ ዋሃቢስት "ዩ ቱበር“ እና "ቲክ ቶከር”“በቁጥር እዚህ ግባ የማይባል የጥቂት ሰዎች የተናገሩት ነው” በሚል <<ክብደት እንደሌለው>> ለማሳየት ሲያጣጥል ሰምቻለሁ።

እንዲህ ከሚሉት ቀንደኛው እጅግ “ሞለጭላጫና የተካነ አሰመሳይ” ፤ ‘ዕብሪቱ” መጠን ያለፈ፤ የነ አሕመዲን ጀበል ጋሻ ጃግሬ የሆነው ፎቶው ላይ የምታዩት ልጅ  ነው።

ይህ ደግሞ የውሃቢዎቹና የሰለፎቹ የቆየና የለመድነው “ቀንደኛ” መገለጫ ባሕሪያቸው ነው።

ይህ የሚያስታውሰኝ “ኦሮሚያ በሚባለው የሞት ምድር “የሚታረደው ሁሉም አምሐራ አይደለም ብዙ አምሐራዎች በሰላም እየኖሩ ነው ብለው እንደሚያጣጥሉት የሽፋን ስልት” ተመሳሳይ ነው።

ከዚህ በታች ያለው ፎቶግራፍ << ሠፊዋን ሃገር ለፍተው ያስረከቡን ኢትዮጵያን ነገሥታቶችን ስም በማጥፋት የተጠመቁ “በጣሊያን ወረራ ወላጆቻቸው ለጣሊያን አድረው ሃገር የወጉ ጸረ አምሐራ “የአስካሪ (ባንዳዊ) እስላም” ልጆች እና የጂሃዳዊው ዋሃቢያው እስላሞች መፈክር ነው። ሃገራዊ ቋንቋ ሳይሆን ዓረብኛ የተጻፈበትን ባንዴራቸውን እዩት።

ሰለፊ ጂሃዲሰቶቹ ቁርአናቸው ገልጠው ከመከራከር ይልቅ “መግደል፤ ማረድ” የለመዱበት ባሕሪያቸው መቸ እንደሚያቆሙት ይገርመኛል (አመጽ ለምን እንደመመሪያቸው እንደሚያደርጉት አልገባኝም። ምባት ከታች በተለጠፈው የተለያዩ የቁርዓን/ሃዲስ አንቀጾች እውነት ይሆን?

እፎይ በተባለው ልጅ ላይ ጥቂት ሰዎችም ይሁኑ መቶና ሺሕ ሰዎችም ይሁኑ “የይገደል” አዋጅ የሚያሳየው “መሟገት የማይችል አቅመቢስነት ወይስ በሚያምንበት መጽሐፍ ዕውቀት የሌለው የተጻፈውን ማንበብና መረዳት የማይችል አማኝ በመሆኑ?” ችግሩ ምንድነው? አንድ ሰው ስለ ክርስቶስ ወይንም ስለ መሃመድ መጥፎ ቃል ስለተናገረ ዓለም ምድሩ የሚገለበጥበት ምክንያት የለም። መፍትሔው መከራከር ነው! አለቀ!

እውነት ለመናገር ልጁ እንዳደመጥኩት <<ቁርአናቸውን እያነበበና እየጠቀሰ>> በሚገርም ሁኔታ ሲከራከራቸው እና የሚሰብኩት ስብከት እውነታ እንዳልሆነ ከቁርኣናቸው እየጠቀሰ ሲከራከራቸው ሰምቼው  ‘እየተንደፋደፉ ወደ ክርክሩ መድረክ በመምጣት ሲከራከሩት የነበሩት እስላሞች (ሸኮች ሁሉ ሳይቀሩ)” እያፈሩ መልስ ሲያጡ ሰምቻለሁ።

 እሱ ብቻ ሳይሆን እስልምና ሲከተሉ የነበሩ ወደ ክርስትና የተጠመቁ እፎይ የተባለው ወጣት የሚደግፉ “ዓረብኛውን ጽሑፍ የሚያውቁ” ወጣት ተከራካሪዎች እስላሞቹን በሚገርም ሁኔታ ሲወጥርዋቸውና መልስ ሲያንሳቸው አድምጬ ገርሞኛል።

ሆኖም ዋሃቢያዎቹ የተጠቀሙት እርምጃ ልጁን ተከራክሮ ካማሳመን ይልቅ “ይገደልን” ምን አመጣው? እኔን የሰደቡ ግደልዋቸው ብሎ “ነብስ ማጥፋት” መሐመድ ፈቅዶ ከሆነ እኔ አልገባኝም።

በክርስትያን እምነት ላይ 10 ቃላት መመሪያ ግን አትግደልየሚለው ብቻ ሳይሆን <<አያውምና ይቅር በላቸው>> ነው የሚለው።እኔን የሰደቡ ሁሉ ይቅር በቸው/በላቸው/ ነው የሚለው እንጂ ስለሰደቡኝ ግደላቸው አላለም። እንዲያ ብሎ ከሆነ ደግሞ ስሕተት ነው።

እስልምና በጣም ብዙ የተለያዩ እምነቶችና ጥቅሶች አሉት፡ ማንን እንመን?

73 የእስልምና ክፍሎች አሉ። እነዚህ ሁሉ “ቁርኣን” እንቀበላለን ይበሉ እንጂ እርስ በርስ ቁርኣኑን በመተርጎም ላይ አይጣጣሙም። ባለመጣጣማቸውም ይገዳደላሉ። እንዲህ ባለበት ሁኔታ “እፎይ” የተባለው ልጅ ቁርኣናቸውን እየጠቀሰ ሲከራከራቸው (የተጠቀመውን ቃል አጠያያቂ እንዳለ ሆኖ) እስላሞቹ ጋር ያደረገው ክርክር ሳደምጥ እስላሞቹ መጽሐፋቸውን የሚያውቁ ሆኖ አላገኘሁዋቸውም (እስካሁን ድረስ ያየሁዋቸው መረጃዎች ከሆነ ፤ ሌላ ያላየሁት ከሌለ በቀር )።

ሆኖም መስጊድ  ላይ አሰላም አለይኩም ወራሕመቱላህ” እና “አላሁ ወአክበር” እያለ ግድያን (ያውም መስጊድ ውስጥ) የሚያውጅ ጂሃዲስቱ ውሃቢያወ ቡድን (የተለጠፈው ቪዲዮን አድምጡት) እውን ቁርዓናቸው ግድያን ያበረታታል?

የኢትዮጵያ አክራሪ እስላም በፖለቲካውም በመንግሥት ውስጥም በሽምጥ ተዋጊው ክፍል ውስጥም በስፋት ተንሰራፍቶ “ክርስትያኑን” በማረድ ለበርካታ አመታት ምንም ሳይሆን አሁን የቀጠለ መሆኑን ታውቃለችሁ። ክርስትያኑ ደግሞ “ል ብሎ” በዝምታ ግድያው እንዲቀጥል አድርጓል። ኦርቶዶክስ እንወክላልን የሚለው ዋናው “ሲኖዶስ” እንኳን ግድያን እና የግድያ አዋጅ በሕግ ከስሶ ሊያስቆም  “ተገንጥሎ የትግራይ አባ ሰላማ ሲኖዶስ እያለ  ጳጳሳት የሾመ <<የወያኔ አባ ሰላማ>> ላይም ምንም እርምጃ አልወሰደም። ማፈሪያ ሲኖዶስ ነውና ኢትዮጵያ ተዋርዳለች! ይገርማል።

ታስታውሳላችሁ ካሁን በፊት <<ያንቀላፋ የሚመስለው ጽንፈኛው የውሃቢው ቡድንሰበብ የማሽተት ሱሱ ተነስቶበት ፋኖ ይውደምፋኖ ሌባ ማለት ጀምሯልጌታቸው ረዳ ETHIOPIAN SEMAY 4/28/22 የሚለው ጽሑፌ?

ትችቴ ያተኮረው “አክራሪው ዋሃቢያው” ቡድን አዲስ አበባ ዋናው መስጊዳቸው ውስጥ ሐጢያታቸው እንዲሰረዝላቸው በጎ እንዲያስቡ ከመጸለይ ይልቅ <<ፋኖን ሌባ>> <<ፋኖ ይገደል>> በሚል የአማሐራን ሕዝብ ጭፍጨፋ ለማስቆም <<ጀነሳይድ” የታወጀበትን ማሕበረሰብ መከታ ለመሆን ጫካ የወጣን ፋኖ  <<ባለበት ሁሉ እንዲታረድ>> ጂሃዳዊ ጥሪ ሲያደርጉ ምንም አልተኮነነም

በዛው ጽሑፌ ዋሃቢያው ጫካ ውስጥ አምሐራን በማረድ ብቻ ሳይወሰን አዲስ አበባም ውስጥ ሁለተኛ ምሽጉ እንደሆነች ለማሳየት የጻፍኩት ነበር።እስከዛሬ ድረስ ችለን እንጂ ተቻችለን አልኖርም የምትለዋ ውሃቢዎቹ የሚወድዋት 30 አመት ሙሉ መፈክራቸው ከጥቂት ወራት በፊት ባሳዩት አዲስ አበባ የመስጊድ ሰልፋቸው ላይ በጽሑፍ ዘርግተዋት ሲያስነንብዋት የነበረቺው ይህች የብዙዎቹ ጽንፈኛ ዋሃቢዎች ተወዳጅ መፈክራቸው ዛሬም እፎይ” በተባለው ልጅ ላይ እየተጠቀሙባት ነው።

ዋሃቢያው በሚጸልይበት መስጊድ  ውስጥም “እፎይ የሚገደት ሰዓት እየመጣ ነው” እያሉ ሲቀድሱ መስማት የሚገርም አገር ሀኗል።እና ወዴት እያመራን እንደሆንን አመላካች አዋጅ ነው።

ዋሃቢያው ያንቀላፋ ቢመስልም ዛሬም ትንሽ ከሸተተቺው ያችን የሚፈልጋትን ምክንያት አድርጎ <<ግደለው፤ እረደው፤ አፈናቅለው>> የምትለዋ የማረድ ሱሱ እየተጠቀመባት ነው።

ሌላ አጀንዳ ካልመጣ በክል 2 እስልምናው ለጎሰኛነት መገልገያ እየሆነ ከመጣ መቆየቱን እንመለከታለን።

ሳንታረድ በሰላም እንሰንብት!!

ጌታቸው ረዳ