Monday, April 7, 2025

ትግራይ አምና እና ዘንድሮ (ሀ) የማይረሳው የከሳቴ ብርሃን ት/ቤት ትዝታ --121 ከጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 4/7/25

 

ትግራይ አምና እና ዘንድሮ

() የማይረሳው የከሳቴ ብርሃን /ቤት ትዝታ --121

ከጌታቸው ረዳ  Ethiopian Semay

4/7/25

ክደራሲው ለዛሬ ወልድ ወጣት አንባቢዎች የተሰጠ ምክር!

ዛሬ ሃገራችን የምትለዋት ኢትዮጰያ ከሰማይ ተጋግራ የተሰጠቻችሁ ሃገር ሳትሆን ብዙ ለፍተን ፤ከጠላት ጋር ተታኩሰን፤ ሞተን፤ ተሰድበን፤ ብዙ ድካምና ደም የፈሰሰባት ምድር ያስረከብናችሁ መሆንዋን ዘንግታችሁ በምድሪቱ ሕልውና ላይ ስታላግጡ በማየቴ የተስማኝን ውስጣዊ ሐዘንና ቅሬታየን እየገለጽኩ ታሪክ ወደ ኋላ ላስቃኛችሁና ሐዘን ተሰምቷችሁ ምናልባት ልብ ብትገዙ ስለ ኢትዮጵያ የተከፈለው መስዋዕት እነሆ ከምጽሐፍይ ላስቃኛችሁ።

ቁስለኛና በሽተኛ የሚቀበለው ብቸኛው የከተማዋ ሆስፒታል ከየቀጠናው የመጡ የቆሰሉ ብዙ ሠራዊቶች በብዛት ስለተቀበለ ከአቅሙ በላይ ሆኖበት፤ በሆስፒታሉ የመተላለፊያ በረንዳዎች ላይ ሳይቀር እንዲተኙ በመደረጉ፤ ብቸኛው ሆስፒታል በቁስለኛ ስለተጨናነቀ፤ አማራጭ ሆኖ የተገኘው ከተማዎቹ ወደ እሚገኙ ትምሕርት ቤቶችና ህንጻዎች እንደመታከሚያና ማረፊያ ሆነው እንዲያገለግሉ ቅጽበታዊ ውሳኔ ተደረገ።ከነዚህ ውስጥክሳቴ ብርሃን/ቤት ነበር።፡ ህንጻው ብዙ ክፍሎች ስለነበሩት የቆሰለው ሠራዊት በብዛት በማስገባት በጊዜአዊ አልጋዮች እና ወለል ላይ እንዲተኛ ተደረገ።ከላይ እንደገለጽኩት ወቅቱ ክረምት በመኖሩ፤ የቆሰሉ ሠራዊቶች ወታደራዊ ቦቴ ጫማቸውና ልብሳቸው በጭቃ እና በደም የተለወሰ ሆኖ ለማየት እጅግ የሚያበሳጭ እና የሚያሳዝን ፈታኝ ወቅት ነበር። ሠራዊቶቹ አልጋ ላይም ሆኑ ወለል ላይ የተኙት አጣዳፊ የማጓጓዝ ስራ ሲሰራ በዛው ላይ ብዛት ስለነበራቸው-ጫማቸው፤ የቦምብ ትጥቃቸውና የጠበቀው ቀበቶአቸው ከነትጥቃቸው ተኝተው ይታያሉ።ይህ አሳዛኝ የሆነ የእርስበርስ ጦርነት ላየ ሰው እውነት ከባዕድ ጋር እንጂ  በአንድ አገር ዜጋ ልጆች የተደረገ ጦርነት አይመስልም።እጅግ የሚያሳዝነው ግን ያኔም ሆነ ዛሬ እስካሁና ደቂቃ ድረስ ወያኔዎች በሚያሰራጩዋቸው የፕሮፓጋንዳ መገናኛዎችውጊያው በጣሊያን እና በኢትዮጵያ ዜጎች መካካል እንደተደረገ  አድርገው በማየትወራሪየሚል ቃል በመጠቀም፤ የጦርነቱ ተከታታይነት  ቀዳማይ ወራር፤ ካልኣይ ወራር ሳልሳይ ወራር..” (1 ወረራ፤ 2 ወረራ፤ 3 ወረራ…) በማለት ኤርትራኖች የሚጠቀሙበትንመሬት ለመንጠቅ የመጣ፤ ኮሎኒያሊስት/ ባዕድለማለት የሚጠቀሙበት አገላለጽ ነው የትግሬ ወያኔዎች ሲጠቀሙበት የነበረው። ደርግተገንጣይ ቡድኖችብሎ ሲገልጻቸው፤ ወያኔዎች ደግሞ በሚገርም አሳፋሪ አገላለጽወራሪ ሃይልበማለት ኢትዮጵያዊነታቸው በግልጽ የጣሉበት አጋላለጽ 

ነበር።በወራሪና በባዕድ የተደረገ ጦርነት ብለው ስለሚያምኑም፤ የዓረቦች አሽከርነት ለማሳየትይመስላልከዓረቦች (ባሕሬን) እና ከሰሜን አፍሪካ (ሞሮኮ) አደባባዮች ዛሬም በሕዝብ መሰብሰቢያ አደባባይ ተተክለው የሚታዩት ከነዚህ ዓረብ አገሮች የተቀዳ ዓረባዊየሐውልትቅርጽ ቀድተውመቀሌ ከተማ ውስጥ ለተሰውት ተዋጊ ሃይላቸውሃውልትአቁመዋል።

ወደ ክሳቴ ብርሃን /ቤት ቁስለኛ ማቆያ ህንጻ ልውሰዳችሁ። ከሳቴ ብርሃን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ/ክርስትያን ትምህርት የሚሰጥበት መንፈሳዊ /ቤት ነው። በሰራዊቱ ብዛት እና ድሕረ ውግያ መደረግ የነበረባቸው ጥናት ባለመደረጉ ቁስለኛ የሚመዘግብ፤ የሚያስተናግድ የሰው ሃይል ስላልነበረ አስቀድሜ እንደገለጽኩት ከነ-ቦምባቸው እና የታጠቁት ሽጉጥ ተጋድመው ያቃስታሉ።  በዛው ብርዳማ ወለል ላይ ያለ ብርድ-ልብስ፤ በትራሳቸው ላይ ጉዝጓዝ በሌለው ወለል ላይ በጀርባቸው ተንጋልለው፤ በጥይት እና በቦምብ የተመታው የቆሰለው ገላቸው፤ ስቃዩ አላስችል ብሎአቸው ፊታቸው በላብ ተጠምቆ፤ ገላቸው በትኩሳት ነድዶ፤ የስቃይ ድምፅ በማሰማት ለተጨማሪ ስቃይ ተጋለጡ።

የሰው ልጅ አንጀት ሰርስሮ በሚገባ ሲቃ እያቃሰቱት የነበረው የስቃይ ጽምፅ እንኳን ለሰው ልጅ አንጀት የአራዊት ጀሮ የሚያሰቆም፤ የሚያባባ ፤የሚያስለቅስ ድምጽ ስለነበር፤ በጆሮው የሰማ የመቀሌ ኗሪ ሕዝብ እንዲህ ያለ ስቃይ ለምን እና እንዴት ተከሰተ ለሚለው ምርምር ለምሁራን ትቶ፤ ባደመጠው የስቃይ ድምፅ  ስለባባ የማልረሳው በዓይነቱ ልዩ የሆነ ተስምቶና ታይቶ የማይታወቅ ኢትዮጵያዊ ሰብአዊነት የተመረኮዘ ያየሁትን የማስታውሰውን ለታሪክ ላስመዝግብ። እንደገለጽኩት የሚያርፍበት መጠለያ ስላልተዘጋጀለት ከሠራዊቱ ብዛት አኳያ ለተቀናጀ እንክብካቤ ስላላመቸና በሃላፊነት የወሰደ የሰራዊት አዛዦችም ከነበሩ እየተካሄደ ወደነበረው የውጊያ ቀጠናዎች ቀልባቸው ስለተጠመደ የተመደበው የሰው ሃይልም በቂ ስላልነበረ፡ የአካባቢው ባለሥልጣኖች፤ አጣዳፊ ዝግጅቶች  ካልወሰዱ እርምጃ (ሞት) ለመውሰድ የሚሽቀዳደም እንጂ በጥናት የታቀደ ሃላፊነቱን የማይሸከም ሥርዐትስለነበረ፤ ከሚመጣባቸውዱብ ዕዳ  እርምጃ ለመሸሽ ሲሉ፤ የከተማው የመንግሥት ተጠሪ ቅርንጫፍ መስርያቤት ሃላፊዎች በመሰብሰብ፤ በየሰዓቱ በሄልኮፕተር  ከጦር ሜዳ የሚመጣው ቁስለኛ የት እና እንዴት ያለ እንክብካቤ መደረግ እንዳለበት፤ እንደየ ጉዳቱ አይነት እየለዩ በየክፈሉ ላመስተኛት ተወያይተው የተቻላቸውን ማድረግ ጀመሩ።

በሰራዊቱ ብዛት እና በመንግሥት ጥናት ባለመደረጉ፤

 እየፈሰሰ ያለው የቁስለኞችን ደም ለማስቆም ለመሸፈን የቁስልሻሽ/ጐዝ መድሃኒት መውጊያም፤ የመርፌ መቀቀያዳርፉር ብረት ድሰት የሕክምና ፕላስተር፤ የመሳሰሉ ጥቃቅን ነገሮች ሕዝቡ ከየቤቱ ካለው እንዲለግስ በተጠየቀበት መሰረት ያለውን ቁሳቁስ ሁሉ ከየቀበሌው እያሰባሰበ ወደ መጠለያ አመጣ። የሰራዊቱ ቁስለኛ ብዛት ስለነበረው፤ በዛው መጠን የሕክምና ባለሞያ ያንን የቁስለኛ ብዛት የሚሸፍን የሰው ሃይል ስለታጣ፤ በዚህ የተነሳ ቁስለኛውን የሚያክም ስላልነበረ፤ እንደየ ቁስሉ ስፋት ጥልቀትና ክብደት ጠረኑ እየለወጠ በመምጣቱ፤ ቁስለኛው ለቀናት አንዳንዱም ለሳምንት ሳይታከሙ በመቆየታቸው፤ ቁስሉቂም’ (ኢንፌክሽን) በመያዙ ምክንያት  በትኩሳትነድሮ በደምና በመግል የተጣበቀው ቁስል በማከም ሂደት ውስጥ ወጣቱና ሕዝቡ፤ ጠረኑ አላስጠጋ ያለውን በደምና መግል የተጣበቀው ቁስል፤ በእጁ እያፈረጠ፤ በጨርቅና በጥጥ ውሃ እየነከረ ጠረኑ የለወጠ ቁስል እየሸተተውም ቢሆን በማጽዳት የማይረሳ ኢትዮጵያዊነቱን ያስመሰከረበት ወቅት ነበር።

እዚህ ላይ ልጠቅሰው የምፈልገው፤ የሕክምና ጥጥ እና ጎዝ/ሻሽ እጥረት ስለነበረ፤ የቁስለኛው ቁስል ስያክም ከየ ያመጣው አንሶላም ሆነ ንጹህ ስስ ጨርቅ በቀጭኑ እየቀደደ ነበር ቁስሉን እያጠበ ለቁስል መሸፈኛ የተጠቀመው እንደዚያ ያለው ትውልድ/ ሕዝብ ዛሬ በክረስቶስ ስም ለምነህ ለማስረጃ እንኳን ለሽታ የሚገኝ አይመስለኝም። ባጭሩድንግል ኢትዮጵያዊነበር! ለቁስለኞቹ የተዘጋጀ የሌሊት (ፕሮን) ልብስ/ ፒጃማ/ የመሳሰሉ ስላልነበሩት፤ ቁስለኛው ሰራዊት፤ በውግያው ወቅት በደምና በጭቃ ተለውሶ፤ ወደ ደረቅ አጐዛነት የተለወጠው ወለል ጋር ተጣብቆ ለብሶት የነበረው ወታደራዊ ደምብ ልብስ ሕዝቡ ከየቤቱ የመጣለትን አንሶላና ነጠላ በማልበስ የቆሸሸው ልብስ በየወንዙና እቤቱ ድረስ ወሰዶ በማጠብ፤ በጭቃ፤ በላብና በደም የደረቀ የወታደሩ ልብስ አጥቦ አልብሶአቸዋል።ለቀናት፤ ለሳምንታት መጀመሪያ ሲመጣ ተንጋሎ በተኛበት ሳይላወስ የቆየውን ቁስለኛ ደግፎ በመስነሳት አከላዊ እንቅስቃሴ እንዲያደረግ፤ ወለል ላይ እና አልጋ ላይ በመተኛት የደነዘዘው አካላቱ እንዲፍታታ አድርጎ ትንፋሽ እንዲያገኝ ረድተዋል።

ከጦር ሜዳ ቆስሎ ሲመጣ በጥብቅ ከርሮ ታስሮ የነበረው ወታደራዊ ጫማቸው ለብዙ ቀናት ከእግራቸው ስላልወለቀ አግራቸው በማበጡ፤ ጫማቸውን አውልቀው የረጋወንና ደማቸውና ያበጠው እግራቸው በዘይትና በደረቁ በማሸት አንገቱን ቀና እንዲል ደግፈው፤ ከየቤታቸው ያመጡት ወተትና ምግብ አልከፈት ያለውን የቆሰለው ጉሮራቸው አለሳልሰው በማጉረስ ያደረጉት ሰብአዊ ርሕራሄ እና ዛሬ ያለው የትግራይ ሁኔታ ሳነጻጽር ሁኔታው እንቆቁልሽ ይሆንብኛል እንዲህ ያለ ጥንታዊ ርሕራሔና ሞራላዊ፤ ዜግነታዊ ግዴታወድዶ ያለ ግዴታበመፈጸም፤ መብራት ባልነበረበትና መብራት በሚቋረጥበት ክፍል ውስጥ ተኝቶ የነበረውን ቁስለኛ ሰራዊት፤ ከቤቱ ያመጣውን ሻማ አብርቶ፤ ቁስለኞቹ ከተኙበት አልጋ እና ወለል ደግፈው አንገታቸውን በማቅናት በስቃይ እና በኡኡታ የደረቀ ጉሮራቸውውሃበማጠጣት፤ የደረቀው ከንፈራቸው፤ በጨርቅና በጥጥ እያራሱ፤ በትኩሳትና በጩኸት የተሰነጣጠቀው የደረቀ ከንፈራቸው እንዲርስ  አድርገዋል።

የመቀሌ ሕዝብ እንደዛሬ ሳይሆን፤ ውርቃማ ከሚባሉ የመጽሐፍ ቅዱስና ቁርአን ሕግጋቶች ከሚጠቀሱ ሰብአዊ "ላንተ እንዲደረግልህ የምትፈልገውን ነገር ለሌላው አድርግ" የሚለውን መርሆ ተነስቶየተደናገጠውን ልብ ያረጋጋሕዝብ ነበር። "ነበር" ብየ የምገልጸው በዛሬው ጊዜ እማሃሉ ውስጥ ከሸገር አውራጃ እና ከወስጡ የበቀሉ አክራሪ ፋሺስታዊ ጎሰኛነት የሚያስተምሩ የተለከፉ ግለሰቦች እማሃሉ ውስጥ በካድሬነትና በከፍተኛ የመንግሥት መዋቅርና በየትምህርት ተቋማቱ እና በኪነት ባለሞያዎችና በየቤተጸሎቶች ተሰማርተው የሕዝቡን ስነ ልቦና በጎሰኛነት ስለበከሉት፤ነውከሚለው ቃል ይልቅነበርየሚለው አማራጭ አድርጌ የገለጽኩት።

ይህ በዚህ እንዳለ፤ ሠራዊቱ የከተማው ኗሪ  ሕዝብ ዜጋዊ

እንክብካቤ ካገኘ በኋላ፤ ትንሽ ሕይወት የዘሩ ሰራዊቶች ከየአልጋቸውም ሆነ ከተኙበት ወለል እየተነሱ፤በምርኩዝም ሆነ በጓዶቻቸው ተደግፈው እያነከሱ በየክፍሉ እየዞሩ፤ የሰርዓቱን መሪዎች በማውገዝ፤ ሠራዊቱን በመቀስቀስ የጦር አለቆች እና ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣኖች ከያሉበት ቦታ እንዲጎበኝዋቸው አስቸኳይ የአድማ ጥሪ ቴሌግራም ይደረግ ብለው ስለተስማሙ፤ በጠየቁት መሠረት፤ ከጥቂት ቀናት ቆይታ፤ እንዲመጡላቸው የጠየቁዋቸው የጦር አለቆች ወደ መቀሌ መምጣት ጀመሩ። አለቆችም፤ በእያንዳንዱ ክፍል በመግባትእንደምን አላችሁ?” እያሉ በመጠየቅ ቁስለኞችን መጎብኘት ጀመሩ።  አለቆቹ ወደ ክፍል ሲገቡ፤ ከአልጋቸው መነሳት ያልቻሉ ኩፉኛ የተጎዱ በተለይ እጆቻቸው ወይንም እግሮቻቸው ያጡ ቁስለኞች፤በእጆቻቸው እያወዛወዙ ወደ አልጋቸው ተጠግተው እንዲያነጋግሯቸው ሲጠሩዋቸው፤ የሠራዊቱ አለቆችም ወደ አልጋው ተጠግተውደህና ናችሁ ጓዶች?” ብለው ሲጠጉ፤ ምራቃቸውን ወደ አለቆቻቸው ሲተፉባቸው፤ አለቆቹም ተደናግጠው ከክፍሉ ሲወጡ፤ በምርኩዝ የሚሄዱ እንዳንዶቹ ቁስለኞችም ኋላ ኋላቸው እየተከተሉ ሲሰድቧቸው ሌሎችም ጥግ ጥግ በረንዳው ላይ የቆሙ እና የተኙ ቁስለኞችበፉጨትእያፏጩ ይቀልዱባቸውና ቁጣቸውን ይገልጹ ነበር።

ልዩ ትዕይንት የነበረው ደግሞ፤ ችግራቸው የአገሪቱ የመገናኛ ማዕከሎች/ ራዲዮ/ ጋዜጣ         እንደማይዘግቡላቸው ስለሚያውቁና በቦታውም የተገኙ ጋዜጠኞች ስላልነበሩ፤ በጣም ቀልጣፋ ተነጋሪዎችና በየክፍሉ በተፈጥሮ ስጦታቸው ቀልድ ነጋሪዎች (ኮመዲያን) የነበሩቀልደኞችበስቃይ የሚያቃስቱትን ጓዶቻቸውን ሲያዝናኑ የነበሩ ከየክፍሉ  የተመዘዙ አባሎች፤ በየክፍሉ በመሄድ፤ አንዱ የመድረክ አስተዋዋቂ ዜና ሰብሳቢ፤ አንዱ ዜና አንባቢ፤ ሆነው በመመደብ፤ የጦር አለቆቹ ሲጎበኙዋቸው በዕለቱ የታየው የጉብኝት ትዕይንት  በዜና መልክ እና በቀልድ አጠናቅረውበሚያስደንቅ አነጋገርና አማርኛ፤ ፖለቲካዊ ቅመም ጨምረውበት፤ ስለ ታየው ሩጫ እና አድማ  ያቀረቡት አቀራረብ እጅግ የማልረሳው ታሪክ ነበር። ከተማ ያደጉ ወጣት ወታደሮች ስለነበሩ አማርኛቸው ሲያንበለብሉት፤ አንዳንዱ ባዲስ አበባዎቹ (አራዳ የምትልዋቸው ይመስለኛል) ልሳን  እየተጠቀሙ ዜናውንና ቀልዱንያለምንም ጽሑፍበቃላቸው ሲያንበለብሉት የሰማ ጀሮ መደነቁን ለመግለጽ ቃላት ፈልጎ የሚያገኝ አይመስለኝም። ዜና አንባቢዎቹ እና ቀልድ ነጋሪዎቹ ባሯርዋጧቸው አለቆቻቸው ላይ ያጠናከሩት በያይነቱ ቀልድና ዜና ሲተነትኑት የሰሙ በከባድ ቁስልና ትኩሳት ተይዘው በሲቃ ሲጮኹ የነበሩ፤ ከተራ ወታደር እስከ መስመራዊ መኮንኖች የነበሩበት የቁስለኞች ክፍል ሳያስቡትፈገግእያሉ ጥርሳቸው ብልጭ እያደረጉ የጭንቀት ፈገግታ ሲያሳዩ ማየት በትዝታ ፈለግ አሁን ሲታየኝ ልቤ ኩፉኛ ይሰበራል።

ሠራዊቱን ለማጽናናት ለመደገፍ በፈቃደኝነት ከተገኙ ኗሪዎች አንዱ እኔ ስለነበርኩ፤ ለእናት አገሩ ለኢትዮጵያ ሲል ሠራዊቱ በሲቃ ተይዞ፤ እንደ ጋለ ብረት የሚያቃጥል ገላው እየተለበለበ፤ ትንፋሽ አጥሮት ሲታገል ባስጨናቂ ትኩሳት እና ላብ ተነክሮ የደረቀው ከንፈሩና ጉሮሮው ደርቆ የትንፋሹ ጠረን ቀይሮ፤የውሃ ያለህእማየ ድረሺሲል ገላውና  ከንፈሩ በቀዝቃዛ ውሃ እያራስኩ ሳጽናናው፤ በዛው ስቃይና የሞራል ጥንካሬና መስዋዕት የከፈለው የመሰለ ሠራዊት ተመን የማይገኝለት መስዋዕት መክፈሉን በዓይኔ ስላየሁት፤ ወያኔ ሥልጣን ከያዘ በኋላ እነዚህን የዋሆች ወደ ለማኝነት ህይወት ወደ በረንዳ ሲጥላቸው፤ ከወያኔ ጋር የማይታረቅ ጸብ የፈጠረብኝ፤ አንዱ ምክንያቴ ይኸኛው ነው። አሁንም ሳስታውሰው እንጀቴ ይረበሻል! ወደ ታሪኩ ልመልሳችሁ። በእንደዛው የመሰለ አስጨናቂ  ክስተት እና ከባድ ቁስል እየተሰቃዩ፤ እርስ በርሳቸው በጠንካራ ሞራል ተደጋግፈው ያየ ሰው፤ የኋላ ኋላ የትም ቀርተው፤ በየበረንዳው እና በስደት ዓለም ተበትነው ማየት፤ እውነትም ኢትዮጵያየሞተልሽ ቀርቶ፤ ያልሞተልሽ በላየሚባለው እውነት ነው።  ይህንን ሳስበው አንድ ግጥም ትዝ አለኝ።

የዘመናችንየኪነት ፈላስፋና የድምጸ መረዋው የቅዱስ ያሬድ ፍሬየሆነው አገር ወዳዱ ዝነኛው ሙዚቀኛው ቴዲ አፍሮሊስትሮበሚል ግጥሙ ውስጥ ያለውን ልጥቀስ።  ጫማ በመጥረግ ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደገ አንድ ሊስትሮ፤ ከዚያ ከድህንት ዓለም ወጥቶ አንድ ቀን ጫማ ለማስጠረግ ሊሰትሮ ጋር ሄዶ ከሊሰትሮዋ/ ከሳጥንዋ /ላይ ቆሞ ጫማውን  እያስጠረገ እንዳለ ውለታ ለዋለችለት የሊስትሮ ዕቃው የገጠመላትን ‘’ቴዲ አፍሮበእንዲህ ይገልጸዋል፦

 

በጣሙን አዝናለሁ ውዷ የሊስትሮ ዕቃዬ፤

ምንም እንኳ ብትሆኚ ባለውለታዬ፤

በጫማ ብረግጥሽ አይክፋሽ ግድየለም፤

 ባታውቂው ነው እንጂ ለዋለላት ሁሉ እንዳዛው ነው ዓለም። 

 ከስሜቴ ልውጣ እና እንቀጥል ወደ ታሪኩ ልውሰዳችሁ። ሁኔታው በሰራዊቱ እና በከፍተኛ አዛዦች እንዲሁም አዛዥ አና አዛዥ መካካል በሁኔታው የተነሳ ያለመጣጣም ስለተነሳ፤ ቁስለኛው ኮለኔል ታሪኩ ላይኔ የተባሉ ከፍተኛ የጦር አዛዥ እንጂ ሌላ እንዳይላክላቸው ስለጠየቁ፤ በጠየቁት መሰረት ኮለኔሉ ወደ መቀሌ መጥተው፤ ቁስለኞች ወደ ተኙበት ክሰቴ ብርሃን /ቤት መጡ። ቁስለኛው የቻለና ያልቻለ በምርኩዝ እና በሰው እየተደገፈ በየበረንዳው እና እመሃል መሰብሰብያው ላይ ተጠራርቶ በመሰብሰብ፤ ለኮለኔሉ ጥያቄ አቀረቡ። ተናጋሪዎቹ አስቀድሜ እንደገለጽኩት እሳት የበሉ ተናጋሪዎች ስለነበርዋቸው፤ ቅሬታቸውን አንበለበሉት። ቆም እያሉ ተናጋሪዎቹ  እምባ ሲተናነቃቸውያዩ አዛዡ በትዝታ ተጭነው በሐዘን ተውጠው ያደምጣሉ። አንዳንዶቹ ቁስለኛ ወታደሮች በዛው ጸጥታ በሰፈነበት አየር ንግግር ሲደረግ፤ ከበረንዳው ላይ ተንጋልለውበሰለለ/ የደከመ/ ድምጽ የታጀበ፤ አንጀት የሚፈታተን የስቃይ ድምጽየሰሙ በረንዳው ጥግ ላይ ካጠገቤ ጎን ቆመው የነበሩ ለእርዳታ የመጡ የከተማው ወጣት ሴቶች፤ ዓይናቸው ውሃ ቋጥሮ  በድንገት ሊፈነዳ የተቃረበዕምባይተናነቃቸዋል።

በኮለኔሉ እና በቁስለኛው ሠራዊት መካከል የመደማመጥ መንፈስ ስለነበር፤ አንዱ የሁኔታቸው ነገር አጠቃላይ ንግግር ካስረዳ በኋላ፤ ሌላ ተናጋሪ፤ በመቀጠል፤ ሲጋራ፤ ወርሃዊ ደሞዝ ልብስ….. ወዘተ.. ወዘተ.. የመሳሰሉ ነገሮች ያስፈልጉናል ብለው ብዙ ዝርዝሮች ካቀረበ በኋላአባታችንይህንን እንደምታደርግልን ባለ ሙሉ ተስፋ አለን፡ እናከብርሃለን! ኑርልን! ብሎ ሲጨርስ፡ ኮለኔሉ በሰሜትና በሃዘን ተውጠው ከውስጥ የያዙት ንዴት እንዳለ መገመት በሚያስችል ንግግር ተናግረውየጠየቃችሁትን በሙሉ ባጭር ጊዜ ይመጣል። ካልመጣ ወዲያውኑ መልእክት ላኩልኝ፤ካሉዋቸው በኋላ የጠየቃችኋቸው ወደ ከፍተኛ ሕክምና የመዛወር ጥያቄም አስቸኳይ ጉዳይ በመሆኑ የምችለውን አደርጋለሁ፤ ጥያቄአችሁ ወደ እሚመለከታቸው ክፍሎች ባስቸኳይ አቀርብላችኋለሁ። ተስፋ አትቁረጡ! እናሸንፋለን! ኢትዮጵያ ወይም ሞት! ብለው ተሰናብተዋቸው ሔዱ። ከሰንት ጊዜ ቆይታ አንደሆነ ባለስታውሰውም ከባድ ቁስለኞች ወደ አዲስ አበባ እና የመሳሰሉ የሕክምና ተቋማትበአይሮፕላን እየተጫኑ ለሕክምና ይወሰዱ እንደነበር አስታውሳለሁ። ሆኖም አገሪቱ የነበርዋት የሕክምና ተቋሞች ከየቦታው በመጡ ቁስለኞች ስለተሞሉ፤ ብዙዎቹ እዛው ክሳቴ ብርሃን እና ሌሎች /ቤት ህንጻዎች ውሰጥ ተጠልለው፤ በቂ የሕክምና እና መድሃኒት ባለመኖሩ፤ድሬሰር/አድቫንስ ድሬሰሮችተብለው በሚጠሩ ዝቅተኛ የሕክምና ባለሞያዎች እየታገዙ ከፍተኛ ስቃይ ለነበራቸው፤ ጦር ሜዳ ላይ ያሉ እየመሰላቸው ትኩሳቱ ሲበረታቸው በቅዠትፉከራ እና ኡኡታ ጩኸትየሚያቀልጡ ቁስለኞች ስለነበሩ፤ ከስቃያቸው እና ከቅዠታቸው ለማስታገስ ተብሎ በድሬሰሮች አማካይነት ያለ ምንም የመድሃኒት መጠን አሰጣጥ ቁጥጥርናርኮቲክ” (አስካሪ አደንዛዥ የስቃይ አስታጋሽ መድሃኒቶች) ‘ቡታዘሊዶን፤ ፌኖባርቢቶል፤ ሞርፊን…..እና የመሳሰሉ እንቅልፍ  የሚያስተኙ፤ የሚያሰክሩ፤ መርፌዎች፤ ማታ፤ ማታ እንዲተኙ በሚል በብዛት እየተወጉ፤ ሱስ ውስጥ የገቡ ብዙ ነበሩ።አሳዛኙ ሁኔታ እዛው ላይ አላቆመም። የሕክምና ባለሞያ እና የሚንከባከባቸው ቋሚ ሠራተኛ እጥረት ስለነበረ፤ ቁስለኞቹ ከተኙበት አልጋ ወይንም ወለል የሚያገላብጣቸው የተመደበ ቋሚ ስላልነበረ፤ኒሞኒያእናቤድ ሶር” (ሳይገለበጡ ባንድ ጎን ለብዙ ወር/ሳምንታት በመተኛት የሚፈጠር ጥልቀት ያለው ጎድጓዳ ቁስል) እየተሰቃዩ ብዙ ጊዜ ቆይተዋል። ጦርነቱ ቀጣይ ስለነበረ፤ ተመሳሳይ ውግያ ሲደረግ፤ የዛሬው ትግራይ ሕዝብና ወጣት በወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ከመበከሉ በፊት (እንደዛሬ አያድርገውና) የያኔው የትግራይ ሕዝብ ሠራዊቱ በያለፈበት ገጠርም ሆነ ከተማ ተጎድቶ ሲያልፍ  የማይረሳ ዜጋዊ እንክብካቤ አድርጎለታል።  ይህ ዜጋዊ እና ርህራሄ የተሞላበት እንክንካቤ ወያነ ትግራይ ብዙም ሳይቆይ በሕዝብ ደም ስር ገብቶ ሕሊናው ሳያበላሸውየኢትዮጵያ ሰንደቃለማ እንጂ እንደ ዛሬ ቄሱም መነኩሴውም ሴቱም ፤ ልጁም፤ ምሀሩም ፤ቤተክረሰትያኒቱምየወያኔባለ ኮከቡ የቻይና ኮሚነሰት ባንዴራ ሳያውለበልብ በነበረበት እንዲህ ያለ የዜግነት ሥራ መስራቱን ለመጀመርያ ጊዜ ለታሪክ ተመራማሪዎች የመዘገበ የመጀመሪያ የትግራይ ሰው መሆኔ ኩራትና ደስታ ይሰማኛል

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ (ከየትግራይ ብሔረተኞች በአማራ ላይ ያላቸው ጥላቻ ከምን የመነጨ ነው?) ከሚል ከታተ 2010 . ከገጽ 121 መጽሐፌ የተቀነጨበ) Ethiopian Semay