Thursday, October 8, 2020

የባሕርዳር አማራ አክራሪዎች ትግሬ የሚባል ሁሉ እስከ ጥቅምት 4 ቀን አገራችንን ለቃችሁ ውጡ የሚል ወረቀት በትነዋል፡ መስከረም 28/2013ከጌታቸው ረዳ(Ethiopian Semay ድረገጽ ዋና አዘጋጅ)

 

የባሕርዳር አማራ አክራሪዎች ትግሬ የሚባል ሁሉ እስከ ጥቅምት 4 ቀን አገራችንን ለቃችሁ ውጡ የሚል ወረቀት በትነዋል፡

መስከረም 28/2013ከጌታቸው ረዳ(Ethiopian Semay ድረገጽ ዋና አዘጋጅ)

የኢትዮጵያን ሰማይ ድረገፅ ተከታታዮቼ ሆይ፡ ይህ መልዕክት ስጽፍ በሃያል ንዴት ውስጥ ሆኔ ስለጻፍኩት ምን ብየ እንደምጽፍን ስለማላውቅ መልዕክቱን ብቻ ተረዱልኝ። “ሼር” እንድታደርጉትና  አክራሪዎቹ እንዲያነብቡትም እጠይቃችሗለሁ።

 ይድረስ ባሕርዳር ለምትኖሩ አማራ አክራሪ ወጣቶች ሆይ! ይህንን መልዕክቴ ይድረሳችሁ!

ዜናው የደረሰኝ ባሕርዳር ውስጥ ከሚኖር ታናሽ ወንድሜ  ነው። አሁኢን ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ሥልክ ደውሎ ከአማራ አክራሪ ሃይሎች የተበተነ ወረቀት ትግሬዎች እስከ ጥቅምት 4/2013 ቀን ከአገራችን ውጡ የሚል የጭፍጨፋ ማስጠንቀቂያ ደርሶናል በማለት የግድያ ደወል የያዘ ወረቀት መበተኑን ወንድሜ ከባሕርዳር ከተማ አሁን ሥልክ ደውሎ ነግሮኛል።

ትግሬዎች ከአማራ ምድር ውጡ፤ለሚደርሳችሁ ግድያም ሆነ የንብረት ቃጠሎና ዘረፋ ሃላፊነቱ የናንተ ነው ፤ የትግሬ ንብረትና ቤትም ማንም ሰው እንዳይገዛቸው የሚል ወረቀት በምንኖርበት አካባቢዎች ወረቀት ተብትኗል።  መንግሥትም የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ለነገ ስብሰባ እንድትመጡ ብሎ ጠርቶናል፡ ስማችንም አስመዝግበናል፤ ምን እንደሚያደርጉን አናውቅም፤ ብሎ አሁን በስልክ ደውሎ ስጋቱን ነግሮኛል።

ባሕርዳር ውስጥ የቀረነው ጥቂት ትግሬዎች ብቻ ነን። ብዙዎቹ ትግሬዎች ብዙ ዛቻ ሲደርሳቸው ንብረታቸው የእንዳትገዙ እየተባለ ስለተነገረ ንብረታቸው እየጣሉ ባሕርዳርን ለቅቀው ከወጡ ከወጡ አመት ሆኗቸዋል።

ዛሬ ወደ ትግራይ የሚወስድ የጎንደር መስመር መንገዱ ተዘግቷል፤ ወደ አዲስ አባባ የሚወስድ መንገዶችም ቄሮ የሚባሉ ዘግተውታል፡አስተማማኝ መንገድም አይደለም፤ በሁለቱም አቅጣጫ መውጫ የለንም። እንዳንገደል ስጋት አለን፤ ብሎ ስጋቱን  በስልክ ነግሮኛል።

አንባቢዎች ይህንን መልዕክት “ባሕርዳር ውስጥ ለሚገኙ የአማራ አክራሪ ወጣቶች” እንዲያነብቡትና እንዲደርሳቸው “በፌስቡክ “ሼር” እንድታደርጉልኝ እጠይቃለሁ። ለኔ ውለታ ብትውሉ ይህንን መድረግ ብቻ ነው የምጠይቀው!! አክራሪው አማራዎች የማስተላልፈው መልዕክት እነሆ ከዚህ በታች ይድረሳችሁ!

የሴቶችና የህጻናት ህይወት ለመዝመት እየፎከራችሁ ላላችሁ ቦቅቧቃዎቹ የአማራ አክራሪዎች ሆይ!

እኔ ጌታቸው ረዳ እብላለሁ፤ የኢትዮጵያን ሰማይ (Ethiopian Semay) ድረገጽ ዋና አዘጋጅ እና ስለ አማራ ጭቆና 6 መጽሐፍትን ጽፌአለሁ። 29 አመት እራሳችሁን መከላከል እቅቷችሁ፤ ‘ሃሞታችሁ ፈስሶ፤ ወኔአችሁ ‘ተሸማቅቆ’ በየቦታው እንደ ጅግራ የሚያሳድዷችሁን ጠላቶቻችሁን መቋቋም አቅቷችሁ፤ 29 አመት ሙሉ እስካሁን ድረስ እኔው አንድ ትግሬ ኢትዮጵአዊ ስለ እናንተው “ደህንነትና መብት” ስጮህና ስከላከልላችሁ እድሜየን ሙሉ “ስሰደብና ከትግሬ ዘመዶቼ” ስገለል፤ ብዙ ችግር ሲገጥመኝ ዛሬ አማራን የሚጨፈጭፉትን መቋቋም ሲያቅታችሁ ባሕርዳር ውስጥ ዕድሜአቸው ሙሉ የኖሩ ፤ ሰላማዊ እናቶች፤ወጣቶችና ህጻናት ትግሬዎች ስለሆኑ “ከባሕርዳር አማራ መሬት ውጡ፤ እንገድላችሗለን የምትሉትን “ወኔና ሱሪ” ዛሬ ከየት ተገኘ? በሰላማዊ ዜጎች ላይ የምታስፈራሩት ዛቻ እና የዘር ማጥፋት ዘመቻችሁ እስከምን ርቀት ድረስ ሊወስዳችሁ ይችላል?

እናንተ በምታደርጉት የዘር ማጽዳት ዘመቻ ለፋሺሰቶቹ ወያኔዎች ተጨማሪ ተዋጊና ደጋፊ ሃይል እየገነባችሁላቸው መሆኑን እንድታውቁት ብቻ ልነግራችሁ እፈልጋለሁ።

አገሪቷ ወደ ጦርነት ማቅ እንደምትገባም አስቀድሜ ብዙ አመታት አስጠንቅቄ ነበር፤ ይኸየው ዛሬ “የአማራ ናዚዎች” ወኔአቸው በህጻናትና ፤ በሴቶች፤ እና በአዛዉንት ትግሬዎች ላይ የግድያ ደወል ደውላችሗል። ለማንኛወም ትግሬዎችን ከባሕረዳር አስወጥታችሁና ገድላችሁ እናንተ ባሕርዳር ውስጥ በሰላም ተንደላቅቃችሁ የምትኖሩባት ከተማ ሆና የምናይ ከሆነ ጊዜው ሲደርስ እናያለን። ለምስክርነትም ያብቃን!

የሚያሳዝነው ስጋት ግን በመልሶ የማጥቃት ግጭቱ የሚጠቁት ምስኪን ዜጎች እንጂ እናንተማ “ቦቅባቃው የናዚ እና የፋሺቶች ታሪክ የሚያሳየን” “ከፉካራና ቀረርቶ ወኔ አልፎ” ጦርነት ቢጀመር እዛው እሳት ውስጥ እንማትገኙ የታወቀ ነው። የአማራና የኦሮሞ ናዚዎች እስካሁን ድረስ ያየነው ጉልበታቸው በሴቶችና ህጻናት ላይ ሲዝቱና ሲዘምቱ ብቻ ነው፡ እናንተም እንዲሁ። ለሁም ጊዜ መስተዋቱ ሁሉም በጊዜ ያሳየናል!

ውለታ የምትውሉልኝ ሰዎች ካላችሁ ይህንን መልዕክት አክራሪዎቹ እንዲደርሳቸው “ሼር” እንድታደርጉት ታሪክ ይጠይቃችል።

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ድረገጽ ዋና አዘጋጅ)