Saturday, November 20, 2010
Who is the Terrorist and Extremist?
ይድረስ ለጎጠኛው መምህር(አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ(ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com http://www.ethiopiansemay.blogspot.com
Who is the Terrorist and Extremist?
By Getachew Reda
(Editor Ethiopian seamy)
The following article was posted on Tocola w/Hagos website. The article was by a TPLF puppet. I ask Tocola to post it as a response on his website. He decline saying
“ Hello Getachew Reda:
I thank you for your note and response to the Editorial of Ethiopia Observer on the statements by Dr. Gregory Stanton, President of Genocide Watch. We posted the Editorial for one single purpose: to bring to the attention of our readers that all the support given by most Diaspora outlets for Dr. Stanton might be for the wrong reason. The Editorial is pointing out such alleged error on Stanton's judgment of blaming Tigrayans for the misdeeds of Meles Zenawi. The frightening consequences he painted of genocidal attack on Tigrayans might deteriorate from prediction to endorsement in the minds of unscrupulous individuals. On the other hand, your response is mainly focused on defending the Opposition and showing the atrocities committed by the TPLF. You are stating factual matter, but off topic in the context of Stanton's speech and the Editorial of the Observer. Thus, I decline to post your article. It adds nothing that we do not already know on the atrocities committed by TPLF. Thank you for the response article, nevertheless. Sincerely
Tecola Worq Hagos, Editor
My response to Tecola was also as the following:
Yes, I am stating factual matter, but you decline to post it because you also allowed his lies and distortions of accusing the opposition in general as terrorists so that all your foreigner readers of your website will have the chance to be brainwashed by his false accusation. Whether the center focus is Gregory or not, you also should have edited or tell the person to remove such accusation and insult to as calling us terrorists that included you. Unfortunately and as expected you never learn. You are to soft hearted to the distorters and TPLF cadres. You shouldn't allow any of those Meles/TPLF puppets use Gregory's speech to attack us as terrorists. Can you ask yourself if you are a terrorist? You like or not it will be posted to the public somewhere. But, unfortunately you rout to side with such distorter is unfortunate. You allow this puppet to slander us as terrorists. You think he cares about Tigrayan? Where the hell was he when the people of Tigray were abused by his masters? he is simply using his speech to slander us using that opportunity and you allowed it. If you chose to be called terrorist by Meles cadres, that is your chose, but do not allow them on your site to call us terrorists and to spread their distorted allegation. It only disrespect your talent.
Getachew Reda editor Ethiopian Semay
“Ethiopian observer- wrote the following in its Editorial complaints to Dr. Stanton page title “An Image of Ethiopia: Racism in Santon's dark heart November 18, 2010” Posted on Tecola Hagos website.
I am not here going to deal with what Dr. Gregory H. Stanton persecutor of criminals of genocide (Please also note, that TPLF is on his waiting list to be persecuted in the future) said or not. It is been responded by so many opposition websites and individuals in regard to Sinton’s comment. Here, I am only going to deal with the writer’s slanderous accusation to the opposition in general. That media ( Ethiopian observer) whether supported or owned by Meles TPLF government is hard to tell. But, that media sounds individual owned and respects Meles/TPLF brutal rule based on his analysis. Though, it is editorial, it started with a pronoun “I”. Individual owned or not, it is clear that this website serves the Weyane Tigray Dukes. To my surprise he started saying “I would like to make it clear to my readers that I am writing as much about myself as about anybody else.” No, Mr., anybody else besides the bandit “TPLF” (plenty of evidence to prove for its banditry and abusing Tigrayans and the nation in general) and its puppets who are racists (plenty of evidence to support such claim) calls me/ or to the opposition whom lived abroad around the world referred us indiscriminately as “extremists and terrorists”. It is strange a supporter of repression group to call all of us in general “extremists and terrorists”. It is outrageous accusation and the insults and the character mentioned there belongs and fits to his organization and his leaders perfectly.
The following accusation towards we the “Diaspora “terrorists and extremists” is projected from editor of Ethiopian observer.
“The few self appointed noisy Ethiopian Diaspora opposition, who are bent on violence and terrorism are responsible for thousands of lives lost, deserves nothing less than unconditional condemnation for their continued attempt to wreak havoc and instability succumbing to megalomaniac dreams in the poorest and most fragile region of the world. Defeatist deploys destructive elements to generate desperado results.”
Won’t you feel to laugh when you hear such distortion from the very first group who used violence and banditry acts (carnage, coerce, intimidation, banditry, murder, theft, corruption, torturing victims with fire …) to seize peoples’ power? Aren’t these bandits dream too much out of their ability to dream and be what they can’t be and act what they are not? He is calling us destructive elements and defeatists while his masters as a symbol of peace, democracy and Human Right activists? I truly amazed by their bold lies and distortion and at times laugh at this EPLF’s Gila puppets (slaves/bariya), how silly they are when they think of me and others like me as part of the opposition that way(terrorists and extremists).
Who the hell do they think they defeat? We know they defeat the moral and fabric of the Tigray peasants by violence and fascistic tortures (plenty of records to go around). Where the hell did TPLF’s puppets learn got the word and the background knowledge of “stability and democracy and integrity to a once country” when they never practice it when they claim as liberators of Tigray”? Does TPLF ever know what Democracy means to citizens? I am a Tigrayan, and I knew for fact that TPLF murdered and enslaved our families (my own family) in the village and in towns, harassed those who refused to join them, neglected their right to be Tigrayans and to live in Tigraya as they wish without being harassed by these genocidal bandits (I will afford my time to debate to anyone who disagree with my accusation against TPLF’s crudest crime ever!!) and torturers. Is that not true? No one with his normal mind refute such claim. Let me give you evidence from TPLF victim in his own words so that readers will not be confused by the bandits’ media outlets distortions. ደርግም ኢትዮጵያዊ ነዉ እናንተም ኢትዮጵያዊያን ናችሁ።” ስንል “ከበስተጀርባችሁ የሆነ ነገር አላችሁ!” በማለት ማሰር እና መቅጣት ጀመሩን …(1500 እንሆናለን)።ወላጆቻችን ታሰሩ። የእርሻ ማሳዎቻችንም ተወረሰ። ቀንደኛ አድመኞች ናችሁ በተባልን በተወሰንን ሰዎች ላይ ከባድ ቅጣት ተፈጸመብን። ከ6 ወር አስከ ዓመት በእስራትና በግርፋት ተቀጥተናል። ክንዶቹ ለረዥም ጊዜ በቀጭን ጅማት ነገር በመታሰራቸዉ ምክንያት ጣቶቹ ደም አስከ ማንጠባጠብ የደረሰ ጓደኛችንም ነበረ። በግርፋት አንድ እጁ እና አንድ እግሩ ሽባ የሆነ ጓደኛየ ሃለቃ ሓዲሽ የባላል። ቢዚያን ወቅት ‘ሙሹሮችና ካህናት’ ሳይቀሩ ‘በህማማት ጊዜ ከቤተክርስትያን’ ተወስደዉ ከሽማግሌዎች በቀር ሁሉም ታፍሶ ተወሰደ። ለመሸሽ የሞከረዉን እንደጅግራ እያሯሯጡ በጥይት ያሳድዱት ነበር። ይህ ሁሉ የተፈጸመዉ የካቲት ወር 1981 ዓ.ም ጀምሮ ማለት ነዉ።ትግራይ ነፃ ከወጣች በሗላ ማለት ነዉ:: ከዚያ… ሰዉ እንደ አዉሬ በአካባቢዉ እየተበተነ በአካባቢዉ በቀን ሰዉ የሚባል አይታይም ነበር። እነሱም እንደ ጅግራ እያደኑ ይዉላሉ፤መሬታችንም ለታጋይ ቤተስብ ታድሎ የምንቀምሰዉ የምንልሰዉ አልነበረም።ከቀበሌ ወደ ቀበሌ የሚያስተላልፉ የነሱ ካድሬዎች ካዩን ጥይት ይተኩሱብናል፤..”) ድያቆን ብርሃነ ገብረህይወት The above young fellow posing his wounded abdomen by TPLF terrorists while TPLF terrorizing Tigray peasants, priests and entire society (Read nore on this on Ethiopian Semay).” This is the true picture of TPL’s democracy and stability that these puppets are shamelessly now claiming TPLF as vanguard of DEMOCRACY & STABILITY and an ETHIOPIAN NATIONALIST! How could leaders and its organization who acted like bandits, their hands and feet stained from tortured victims’ blood and who lost love for its peasant society, who solved every conflict by violence and intimidation now speak of love, unity, peace prosperity, stability (crap propaganda?)to Tigrayans and Ethiopians. How so? Where the hell were you when your own peasants from Tigray were tortured and intimidated and hunted like edible animal by TPLF cadres, and Kifli Hizbis and Baytos and kerabit ….numerous groups & of institution of murder and intimidation all over the village of Tigray? Have you ever complaint about it? Where and when?
Here is the other distortion again.
“Ethiopia yearns for just, equal and consistent governance that upholds the individual right, values and uses diversity to ascend to a higher order. The enemies of truth and perpetrators of disinformation and misinformation would love nothing better than this. We suspect, it is yet another example of your organization disregard to any legal, ethical and moral standards when it deals with Africa and in particular Ethiopia.”
Wrote on his protest to Dr.Santon the president of the Genocide watch/court president. TPLF knows why it is puking on its underwear when voice is heard from Human Right and Genocide watch staff members. It is an open secret that TPLF committed genocide by teaching its followers through songs (see the above TPLF most notorius rascist singer playing his kKirara-traditional instrument) and other organization to hate Amahara and caused and participated on the ethnic cleansing of the Amhara society ( read the following hate songs against Amhara , even against some Awaraga in Tigray)
1-(ንዓወሽ በሉ ዙ አድጊ ኣምሓራይ)
2-(ይኺድ ንዓዱ)
3-(ዓድዋ ሽረ ዐሻኽሱም ፁሩያት ተጋሩ
4-ተምቤን ራያ እንደርታ ጎረቤት አምሓሩ)
and recently involved also in the Gambella crisis which Bernabas himself admitted (see translation of Tigringa to Amharic on my weblog). Who is fooling who?
If as he (Ethiopian observer editor) claimed, motive was none other than the best interest of our country and defend our ethnic identity as true Ethiopians, his effort and condemnation also should have gone similar to TPLF leaders who committed so much human crime and atrocity and abuse. If the fellow need evidence or ask for one I will provide him written documents and audio/video (that includes admission of extreme human abuse and participation on national crime from its own founders and members, unless they too are called terrorists and extremists by the fellow who is naively accusing all of us as terrorists.) TPLF worshipers needs to settle down and study carefully how brutal TPLF was and how a brutal master it was to the peasants in Tigray (not to mention its ugly records after it came to rule Ethiopia).
Let me conclude with Gebru Tareke’s latest book “The Ethiopian Revolution” to teach the Ethiopian observer and reminded him how his TPLF used to look like in the Tigrayan villages while guerrilla:-
“ …When political education through the commissars, propaganda, and self-criticism were not sufficient to keep the fighters in line, there was always recourse to the Halewa Weyane (Defense of the revolution), (“whose shadow was everywhere and whose long arms were merciless” according to a former of the front” said Gebru Tareke in his book. Gebru Tareke continued “..The punishment for repeated serious offense was psychological and physical torment, confinement in dark underground bunkers known as hidmo, or even death. Many fell under the front’s axe, especially in the early of the struggle.” (Page 107 The Ethiopian Revolution). Do we need to go further? TPLF cadres need to filter their distortion with different quality of sieve. Particularly, do not lie to us to the Tigrayans, we know TPLF as much as you do, may be some of us even know more details (victims and their families know better detail than the puppets got their distorted information told by their connive leaders in different tune). Let me conclude my rebuttal with the following TPLF hate songs for readers to judge who is the extremist and terrorist. Let us see how TPLF was teaching its young generation and the people of Tigray; - listen to the TPLF song “CHEQONTINA AMHARU” the hate song against the Amhara people.
“ንአብነት ማይ ጨዉ ዓድዋ እንተዘከርና፤ ተምቤን ዓቢይ ዓዲ ሽረ እንዳባጉና፤ ኩይናት ምስ ገበሩ እቶም ወለድና፤ ጸላኢ ደምሲሶም ታሪኽ ሓደጉልና። ;..ጨቆንትና አምሓሩ ምስ ታሪኽ ፀሓፍቶም ንዓና ዓብሊሎም ታሪኽና ጎቢጦም አለዉ ይምክሑ ብደም ወለድና፤ ንቃለስ ተጋሩ ክንመልስ ቅያና “
(ሓቀኛ ታሪክ ተደብቆ አይቀርም ለምሳሌ የማይጨዉን፤ የዓድዋን፤የሽረ እንዳባጉናን ታሪክ ስንመረምር ወራሪዎችን ድባቅ በምመታት አኩሪ ታሪክ ትተዉልን አልፈዋል። ይሁን እንጂ፤አባቶቻችን ብብዙ ዓዉደ ዉግያዎች ደማቸዉን አፍስሰዉ ያስመዘገቡትን ታሪክ “(ጨቆንትና አምሓሩ ምስታሪኽ ፀሓፍቶም”) “ጨቋኞቻችን አማሮች እና ታሪክ ጸሃፊዎቻቸዉ” በአሁኑ ወቅት እየተኮፈሱበት ነዉ። ታሪካችንን ቀብረዉ በአባቶቻችን ደም/ታሪክ እየተመኩበት ናቸዉ እና የትግራይ ተወላጆች የሆንን በሙላ ታሪካችነን ለማሳደስ በፅናት መታገል አለብን) የሚል መልእክት ነዉ ዘፋኙ ያስተላለፈዉ።
እግዲህ እዚህ ላይ የምንመለከተዉ ልብ ብለን ማሰተዋል ያለብን (1-) ጨቆንትና አምሓሩ የሚለዉ ሐረግ ትግራይን የጨቆነዉ አማራ መሆኑን (2-) ይህ አማራ የተባለዉ ጨቋኝ ነገድ፣ ጉብዝና የሌለዉ፤ለኢትዮጵያም ሆነ ለትግራይ ሕዝብ ሲል ደሙ ያላፈሰሰ፤ በመከራ ጊዜ ለትግራይ ሕዝብ ያልደረሰለት፤የጣሊያን ወራሪ መሪዎቹን እነ ራስ መንገሻ ዮሓንስ እያሳደደ አዲግራትን መቀሌን አልፎ እስከ አላጌ ድረስ ሲያስሸሻቸዉ አማራ የሚባል ክፍል ለወገኑ ለትግራይ ሕዝብ የወገን ደራሽ ሆኖ አምባላጌ፤ እንዳየሱስ፤ ሽረ ፤ በእንዳባጉና፤ በሰለክላካ ጦር ሜዳዎች ከጎጃም ከሸዋ ከወሎ ከጎንደር ገስግሶ ዘምቶ ደሙን እንደላፈሰሰ፤በመስበክ የታሪክ ዉሸት በጽሁፍ እየመዘገቡ አዲስዩን ትዉልድ ለማወናበድ ጥረዋል። ዘፈኑም የሚያመለክተዉ ይሄንኑ የዉሸት ጸረ-አማራ ስብከት ነዉ። ያዉም-አርበኝነት የሚባል ወኔ አማራዉ ስለሌለዉ ወይንም የትምክህተኞቹ ወላጆች የሚባሉት “አማራዎች” አርበኛ ስላልበቀለባቸዉ “በትግራይ አርበኞች” እየተመኩ “የትግራይ አርበኝነት የአማራዉ በማስመሰል” እየተኮፈሱበት ነዉና “አማሮች በራሳቸዉ አርበኞች (ካሉዋቸዉ!!) ይኩሩ እንጂ በወላጆቻችን በትግራይ አርበኞች መኩራራት መኮፈስ የለባቸዉም።ይላል ዘፋኙ የወያኔዉ የኪነት ክፍል።
ይሄ ደግሞ እንዲሆን መፍቀድ የለብንም!! ነዉ መልእክቱ።ይሄን ስታነቡ ብለጭ እንደሚልባችሁ ይገባኛል። ያልበሰሉ ትንንሽ ህሊናዎች አደገኞች በመሆናቸዉ ለምን እንዲያ እንደሚሰማችሁ ይገባኛል። ለመሆኑ አንዳባጉና ፤ሰለክለኻ :ማይጨዉ ያልዘመተ አማራ ማን አለ? ትዝታ የሚለዉ የአቶ አዲስ አለማዮህ መጽሃፍ የሚነግረን በአማራ ዘማች እና አዝማች የተካሄደ ጸረ- ጣሊያን ጦርነት ነበር።እነ አዲስ አለማዮህ ፤እነ ራስ እምሩ ትግሬዎች ናቸዉ? ይህ ክህደት የዘለለዉ የክህደት መጠን ስትመለከቱ ጎሰኝነት በዉሸት ሕሊናን አስክሮ ሕዝብ ለሕዝብ እንደሚያባላ ምንኛ ሃይለኛ በሽታ እንደሆነ እንረዳለን።
Dear readers Judge to yourself, “Who is hateful , extremist and terrorist?
//-//
Tuesday, November 9, 2010
የዳመናው አገር By Getachew Reda
የደመናው አገር (ጌታቸው ረዳ)
![]() |
| GETACHEW REDA Editor Ethiopian Semay |
የደመናው አገር (ጌታቸው ረዳ)
ይድረስ ለጎጠኛው መምህር(አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ(ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/
ይህ ግጥም ወያነ ትግራይ ወደ መንበረ ሥልጣን ወጥቶ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ የጎሳ ፖለቲካ ነድፎ እርስ በርሳችን በጥላቻና በቂም በቀል የጎሪጥ እየተያየን የቋንቋ አደረጃጀት በተከተሉና ባልተከተልነው መሃል ሲታይ የነበረ እጅግ አሳዛኝና አስፈሪ የጥላቻና የመሰዳደብ ዓየር ሰፍኖ በነበረበት የመጀመሪያው ዓመት እና በተለይም ከዚያ ተከትሎ ለ7 ዓመታት ወያኔዎች ከኤርትራ ባንዳዎች ጋር በመሻረክ አማራውንና የኢትዮጵያ ሰንደቃላማና ታሪክ ጸሓፊዎችን እንዲሁም በተለይም አፄ ምኒሊክንና አማራውን በጠላትነት እንዲታዩ ወያኔ ትግራይ በረሃ ውስጥ (1) ተጋድሎ ትግራይ በልዎ እቲ ዓሻ ኣምሓራይ (2) ንዓወሽ በሉ ዙ አድጊ ኣምሓራይ (3) ይኺድ ንዓዱ… እና የመሳሰሉ ፀረ አማራ የወያኔ ዘፈኖችን በግልፅ ሲያሰራጫቸው ነበረውን የጥላቻ ቅስቀሳው በተግባር በመተርጎም አጀንዳው አደርጎ የተነሳው ጥላቻውን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ አማራዎች በተለያዩ ጠባብ ብሔረሰቦች በቢላዋ እና በሳንጃ አንገታቸው እየተቆረጠ ከነበሩበት እና ከቄያቸው ወደ ትውልድ መንደራችሁ ሂዱ እየተባሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል። በወቅቱ ትግሬዎች ሆነን የሻዕቢያ ጊላ (ባርያ) የሆነውን ወያኔን ያልደገፍን ትግሬነታችን ተገፎ “የሸዋ ትግሬዎች” (ሽዋውያን ተጋሩ) እያለ ትግሬነታችን ሲነጥቀን፤ በአንፃሩ ከወያኔ ያልተናነሱ አንዳንድ ጠባብ አማራዎችና የኦነግና የመሳሰሉ ጎሰኞች የትግራይን ሕዝብ ሲዘረጥጡ አልፎም ከትግሬ ጋር ጋብቻ እንዳታደርጉ የሚል ቅስቃሳ ሲደረግ እነሱንም በግልፅ ስቃወም ትገሬ በመሆኔ እኔኑም አብረው ትገሬ ትገሬ ነው እያሉ “የወያኔ የሻዕቢያ ዘር” እያሉ በየ ሚዲያው ሲሰድቡኝ በመሃል ለሃቅ በመቆሜ አንተምና አንተም ተው አንተም ተው ባልኩኝ ቁጥር የደረሰብኝ ዘለፋ እጅግ ኣሳዛኝ ስለነበር፤የተሰማኝን ብቸኝነትና ቅሬታ ለታሪክ የዘገብኩት ግጥም ነው። ግጥሙም በትላልቅ መጽሄቶች ታትሞ ነበር። ዛሬ በራሴ መጽሓፍ ለማስረጃ ተካትቷል። ግጥሙም እነሆ። ለጎሳ እና ላጥንት ለሥጋ ዝምድና ላገር ልጅ ለወንዝ ልጅነት ሳይሆን ለሰብአዊነትና ለኢትዮጵያዊነት በመቆሜ ሞት አይቀርምና እኔ በሥጋ ብሞትም ታሪክ ዘግቦታልና የቆምኩላትን አገሬ ኢትዮጵያን ግን ለጊዜው ቢያዳክሟትና ቢዘልፏትም መግደል ግን ከቶ አይቻላቸውም። እሷን ለመግደል ለ18 ኣመት የተለያዩ መርዞች ተቀምመው ሁሉም አልሰራ ሲላቸው ጠላቶቿ ዛሬ የሷን የሺዎቹ ዘመናት ታሪክ ማመመን እየዳዳቸው ነው (ስዩም መስፍን የመቶ ዓመት ታሪክ ሲላት የነበረው ከባድሜ ጦርነት በኋላ የ3000 ዓመት ታሪክ አለን ሲል ያለውን አድምጡ) ወጣቱ “ልደቱ አያሌው” በምርጫው ክርክር ወቅት ወያኔዎችን ያሳፈራቸውና (ድሮ ምኒሊክ ከሃዲ ሰትሏቸው የነበረ ዛሬ ይመስገነው እግዚአብሔርና ታሪክ ለምርጫ መጠቀሚያ ብላችሁም ይሁን … ለግል ምክንያታችሁ “አፄ ምኒልክን ጀግና ነበሩ” ሰትሉ ለመጀመሪያ ጀሮኣችን አድምጠናል;
ለወደፊቱም ሌላ ታሰሙን ይሆናል። ያለውን ታሪክ ምስክርነት አድምጡ።) ኢትዮጵያ የረዢም ሂደት ክንዋኔ እንጂ ወያኔዎች እንደሚሉት በቀላሉ የምትናድ፤ የኮሎኒ፤ የብሔር ስበስብ ፤አርቲፊሺያል”ስላልሆነች “አትሞትም”። ጠላቶቼ እኔንም ሆነ አገሬን ሊገድሉን ከቶ አይቻላቸውም። ሊገድሉት የማይቻላቸውን ወደ ግጥሜ ይዤኣችሁ ልግባ።
የዳመናው አገር (ጌታቸው ረዳ)
አንተም ታገስ አንተም ተው ባልኩኝ ቁጥር፤
ይጠሩኛል በነሱ ጎን ለምስክር።
ለሓቅ ስናገር አያምራቸው፤
ይመድቡኛል“ሸዋዊያን-ተጋሩ” (የሸዋ ትግሬዎች) ከሚሏቸው፤
ሌላኛውም ካልሄድኩ በመንገዱ፤
ያወርድብኛል የስድብ ንዳዱ።
”የወያኔ የሻዕቢያ” ዘር ይለኛል፤
መድረኩ ሁሉ ይዘጋብኛል፤
የቋንቋ ፍራቻም አገር አጥቅቶታል፤
ትግሬና አማራው ሌላዉም ሌላውም በሩቅ ይተያያል
መዞር አልተቻለም፤መንደር በዘር ታጥሯል።
ንቡም ቢሆን ጨንቆት እምባ ቋጥሯል ዓይኑ፤
አይዞህ እንዳልለው ዓይኔ ብሷል ካይኑ።
በዚህ ናፈቅኩኝ፤አገር እንዳለው ሰው አገሬን ናፈቅኩኝ፤
ቀና ስል ወደላይ የጭጋግ ጉም ታየኝ፤
ልቤ አስሬ መታ ማመንም አቃተኝ፤
አየሁኝ ዳመና የጥንት የሚመስል፤
ይዞ ያገር ካርታ አብሮ የሰው ስዕል፤
ባተኮርኩኝ ቁጥር ይጠጋኛል፤
ደብዘዝ ይልና አንዳንዴም ይጎላል፤
ልዝነብ! ልዝነብ! ይላል፤
ዘንቦ ላይዘንብ ጠብ! ጠብ!.... ጠብ!... ጠብ! ይላል፤
ቀዝቃዛም አይደለም ቆዳ ያቃጥላል።
ቆዳየን ለማየት ዞር ብል ላንዳፍታ፤
ተሰወረ ጉሙ ካይኔ በእፍታ።
አሻቅቤ ሰማዩን ብቃኝ በአንክሮ
ሳይታወቀኝ አየሁት መሬት ወርዶ እፊቴ ላይ ተገትሮ፤
የሰዉ እግር በእግረሙቅ ተሸንክሮ።
ብጎነታትለው ልፈታው
እግረሙቁን ልሰብረው
ጮኹብኝ በገደል ማሚቶ ከበቡኝ በግራ ቀኝ መጥተው
አትንካው አሉኝ እኔም መነካካት አልተው።
ነፃ አውጡት ፍቱለት ወይ ልፍታው ብየ በጠየቅኩኝ
ትግሬ ነህ አማራ? አሉኝ ማንን እምስላለሁ? አልኩኝ።
አይመስልም እንዴ ቆዳየ ቆዳችሁ?
ለምን እንዲህ ጠየቃችሁ? ብየ ጥያቄያቸውን በጥያቄ መለስኩኝ
ማመን ሲያቅተኝ የምለውን ሲጨንቀኝ፤
ገርገጭ ሲል እግረሙቁ ተሰማኝ
በግራ ጎተቱት፤በቀኝ አዋከቡት፤አጋር የለው አማኝ።
አለቀሰ! አብሮት ያለው ካርታም ተላቀሰ
አለቀሰ! አለቀሰ! አለቀሰና እኔኑም ጭምር አስለቀሰ።
ተሰናበተኝ እንደታሰረ ”በጉም” ወጣ ታጅቦ ወደ ሰማይ
አብሮት ጭልጥ አለ ካርታውም አይታይ።
በዝግታ ይጓዛል፤
አንዴ ወደፊት አንዴ ወደኃላ ይዋልላል።
ኮበለለ ኦሮማይ! ሄዷል ስል እንደገና ተሰበሰበ
ይዘንብ እና አብሮት ይወርድ ይሆን ስለው አልዘነበ።
”በጉም” ይጎተታል
አየሁት ደብዛውን እንዴ ይከስላል
አንዴ ይጎላል
ወይ አይሟሟ ወይ አይረጋ፤ ጎልቶ ላይጎላ ባየር፤
ይዋልላል በጉም የደመናው አገር።///-///
Tuesday, November 2, 2010
ወሮበላዎች የመቀሌ ኗሪዎችን እያስጨነቁ ነው!
ይድረስ ለጎጠኛው መምህር(አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ (ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/
ወሮበላዎች የመቀሌ ኗሪዎችን እያስጨነቁ ነው!
ከጌታቸው ረዳ www.ethiopiansemay.blogspot.com getachre@aol.com
November 1, 2010 ጥቅምት 2010
ባለፈው ዓመት አቶ ዜናዊ አስረስ (የመለስ ዜናዊ አባት) በ2002 ዓ.ም (ታመው በማጋገም እያሉ ማለትም አንድ ዓመት ከሞሞታቸው በፊት)ድሃይ ትግራይ ለተባለ መቀሌ ከተማ የሚታተም የትግርኛ መጽሄት የሰጡት ቃለ ምልልስ በኢትኦጵያን ሰማይ (በኔው ዌብ ሎግ)ከትግርኛ ወደ አማርኛ ተርጉሜ ላንባቢአን አቅርቤው ነበር። በወያኔ አስተዳደር ፍትሕ የተበላሸ እና የአስተዳደሩ ብልሹነት የድሮ የመሳፍንቶች/ንገሥታት/ጉልተኞች/ፊውዳሎች..ስርዐትን የሚያስታውስ የአቆርቋዦች አስተዳደር መሆኑን ከወያኔው መሪ ወላጅ አባት አንደበት ለማስረጃ ዘግቤላችሁ እንደነበር ይታወሳል። ያን ባጭሩ ትውስታችሁን እንደገና ለማስታወስ በዚህ ልጀምርና ዛሬም የመቀሌ ከተማ ጋንጎችና ሌቦች/ዘራፊዎች/ነብሰ ገዳይ ወንጀለኞች “ፍትሒ”(ፍረድ ቤት)እየተባለ ከሚጠራው “ወያነ-ዊ”የዳኞችና የአቃቤ ሕጎች ስብስብ እያስጨነቁት እንደሆነ በጥቂቱ አንድ ልበላችሁና በሚቀጥሉት ሳምንታት ትግራይ በወረበሎችና በፍትሕ ዙርያ የተኮለኮሉ የፍትሕ ክፍል (ፖሊሶች/አቃቤ ሕጎች/ዳኞች…)ጉበኞች-ምክንያት ኗሪዎችና ጎብኚዎች እየተርበደበዱ(ተሪፋይድ)እንደሆነ አቀርብላችሗላሁ። ጠቅላላ ዘገባ እስካቀርብ ድረስ የወያኔ ፍትሕ ለመመመዘን ያመች ዘንድ ፓልቶክ ውስጥና “ኢቲቪ”ተብሎ ከሚጠራ እና ከወያኔ ከበሮ መቺዎችና ቱልትላ ካድሬዎቹ እንደሚነገረው ሳይሆን እውነታው እነሱ ከሚሉን የተለየ መሆኑ “እርኩስና ከሃዲ”የሆነ ፍጡር ትተውልን ከተሰናበቱት የመለስ ዜናዊ ወላጅ አባት አቶ ዜናዊ አስረስ ምስክርነት እንጀምር።
<….ሰዉ ላይ ታች ሲል አንዳይቸገር ፤ከሚኖርበት አካባቢ ጉዳዩ እየፈጸመ፡ እሥራው ላይ እንዲውል፤ ረሃብ አንዲወገድ ከሚል አኳያ ስልጣን ለወረዳ ተሰጠ። አሁን የወረዳ ባለስለጣኖች ወደመላአክትነት ተለወጡ።ሰው መሆናቸውን ዘንግተውት ወይንም የሕዘቡ አገልጋዮች መሆናቸውን እረስተው፤ ፈጣሪ አድራጊ እኛው ነን፡ዞባ (አውራጃ) አይቆጣጠረንም በማለት ሉጋም እንደሌለዉ ፈረስ ሆነዋል። መጥፎ ሀኔታ ነው ያለው።በተለይም በማዘጋጃ ቤት፤ ፖሊስ፤ወረዳ በኩል ሕዝቡ ሲያማርር ነው የምትሰማው። ምከንያቱም፤ የሚጠይቃቸዉ ተቆጣጣሪ የለም። አጠቃላይ ስልጣን ለነሱ ሰጣቸዉ። መነሻ ሃሰቡ ጥሩ ነው፤ ሰው እንዳይደክም፤ ላይ-ታች እንዳይል፤ በያለበት አቅራቢያ ውሳኔዎች እንዲያገኝ ፤ነዋሪው ጊዜ ሳያባክን ወደየ ሥራው ወደ ንግዱ ፤ወደየ እርሻው እነዲሰማራ ታስቦ ነው። ሃሳቡ ጥሩ ነው። ግን ቁጥጥር የለውም፤ እንዳሻቸው ይሆናሉ። ለዞባው (ለአውራጃዎቹ) አይሰማም/አያከብርም። ለምሳሌ የዓድዋ ወረዳ ያባረረው ሰራተኛ፡የእንትጮ ወረዳ ይቀጥረዋል። እንትጮ ያባረረው፡ ዓዴት ይቀበለዋል። አንድ ሌባ እሌላ በፈለገዉ ቦታ ሄዶ ይቀጠራል፦በሌብነት ተገልሎ አይኖርም። ምን ነበር? ምን ታሪክ ምን ሬከርድ አለዉ? በምን ምክንያትስ ተባረረ? ብለው አያጣሩም። ….. <…..አንድ ሰው አለ፦ በሌብነት አራት ጊዜ በአራቱም ቦታዎች እተባረረ የተቀጠረ።ወደ ስለጣን!ሌላውን እንተው’ና አኔ የማወቀው አንድ ሰው እንኳ ከእንትጮ ተባርሮ ወደ ዓዴት ላኩት፤ከዚያ ተባርሮ አሁን ደግሞ ወደ ዓድዋ መ’ቷል። አንግዲህ ይታይህ፡ አንድ ሰው ጥፋት ከፈጸመ ጥፋተኛ ነው። በተለይ በሕዝብ አስተዳደር። በየቢሮዉ በሕዝብ አያላገጡ መኖር አይቻልም።እግዚአብሔር ለአዳም ሕግ ሲደነግግለት እፀ በለስ እንዳትበላ በሎታል፡ሲበላ ጊዜ ኮነነዉ። ደሃይ፦ ከቡር አባት ዜናዊ አሁን ወደ አዲስ ሚለንየም ገበተናል፤ከዚህ ሚለንየም ምን ይጠብቃሉ፤ምንስ ይመኛሉ? አባት ዜናዊ፡-ወደ 2000 ዓ/ም መድረሱ በራሱ ድል ነው።በቀጣዩ ግን ይህ መንግሥት የገዛ ራሱን ሹማምንቶቹ ቁጥጥር ያድርግ። ተጠየቂነት ይኑር፤ በተለይም በወረዳ አካባቢ። ያጠፋ፤የበደለ፡ ችሎታ የጎደለዉ መገለል አለበት! ያኔ ጥሩ ዘመን ይሆናል። ጥፋተኛውን ሳይቀጡት እነደነገሩ ቸል ብለውት ሲያጓትቱት ይውሉና መጨረሻ ይለቁታል። ከዚያ በሗላ መጥቶ ወቃሾቹን እራስ እረሳቸውን ይኮረኩማቸዋል። እንዲህ ያለው አሰራር ካልተሻሻለ ተስፋ የለውም። ………ህዋሓት ለሁለት ሲከፈል፤ የትግራይ ህዝብ ሊፈጭ (ችግር ውሰጥ ሊወድቅ) ነው ብየ ተጨነቅኩኝ። የኔ ጉዳይ ሳይሆን ያስጨነቀኝ፤ መለስ ፖለቲካው ውስጥ ስላለ አደጋ ቢደርስበት አኔ መቸውንም ዝግጁ ነኝ። ያስጨነቀኝ ግን ትግራይ አደጋ ውስጥ ይወድቃል ብየ እጅግ ተጠበብኩኝ። አሁንም ቢሆን እኔ ህወሓት እንድትኖር የምፈልገዉ ለራሴ ለግል ብየ ሳይሆን፤ የትግራይ ሕዝብ ለህወሓት ሲል ደሙን አፈስሶ፤አጥንቱ ከስክሶ፤ልሊቱን መዉጫ መግብያ መንገዶችን እየመራ ማሳየት፤ በቀን ሲጠማቸዉ ዉሃ ምግብ፤ማረፍያና መጠለያ በመስጠት አሁን ወዳለንበት ደረጃ አደረሳቸዉ። ያገኘዉ የረባ ጠቀመታ ግን የለም። በወረዳ፤በማዘጋጃቤቶች ቢሮክራሲ ተተብትቦ ፍትህ በማጣት አየተበሳጨ፤እያማረረ ነዉ ያለዉ። መሬት ካንደኛዉ ነጥቀዉ ለሌለኛዉ ይሸጡለታል። በዛም አነሱም (እንደዛም እየሆነ) ድርጅቱ እንዲቆይ እፈልገዋለሁ። የትግራይ ሕዝብ እየቸገረውም ቢሆን ችግሩ እየቻለ ይኑር፤ ከነሱ የተሻለ አመራር ሌላ አያገኝም። የበቁ መሪዎች እንዲሆኑ ራሱ እግዚአብሄር ይርዳቸዉ። በተለይመ አሁን ለየወረዳው የተሰጠዉ ስልጣን ተቆጣጣሪ ቢደረግለት መልካም ነዉ። <… ለምሳሌ በማዘጋጃ ቤቶች በኩል እየተደረገ ያለዉ፡ ላንዱ ሰጥተዉት ቤት ለመስራት መሰረት ተጥሎበት በመሰራት ሂደት ላይ የሚገኝን ቤት አስቁመው፤ በስሕተት ነበር የሰጠንህ አና ስራዉን አቁም በማለት ከሱ ነጥቀዉ ለሌላ ሰዉ ይሸጡታል። በዚህ አሰራር ተጠያቂዉ ማን ነዉ? እነደዚህ ላለ አሰራር ለሚሰራ ባለስለጣን ጠያቂ የለዉም። አንደዚህ ያለ አሰራር እየተሰራ እያዩ አንዴት ተኩኖ ነዉ ዜጎች ከዉጭ አገር መጥተዉ የግንባታዉ ተካፋዮች ሊሆኑ የሚችሉት? ላንዳንድ ሰዎች ደግሞ በማለት የቀሙታል። ሰለዚህ በየወረዳዉ፤በፓሊስ አና በማዘጋጃቤት ፈትሕ የሚባል የለም። እገዚአበሔር ያሳይህ፦ ማዘጋጃቤት ለአንድ ፎቶ ኮፒ ሦስት ብር ያስከፈላሉ። እዉጭ ብታደረገዉ ግን ሚፈጅብህ ሃመሳ ሳንቲም ብቻ ነዉ። ስልጣን እንደ ጠመንጃ ተጠቅመዉ ይዘረፉታል፡ ዘረፋ ነዉ! ዓይን የሌለዉ ዘረፋ! ኦ! እበክህን በቃኝ ይበቃኛል፤ ደከመኝ፤ ብትለዉ ብተለዉ ጉዳዩ የሚያለቅ አይሆንም፤ ተዘርዝሮም አያልቅ> ነበር ያሉት።
ዛሬም የፍትሕ ያለሕ እያለ ለ17 ዓመት የሚጮኸው ሕዝብ በሌቦች እና በመንደር ጋንጎች ቁጥጥር ስር ሆኖ የተሻለ መንግሥት እንዲመጣለት እየተማጸነ እንሆነ አንዳንድ ጥቆማዎች ይገልጻሉ። እጅግ ከተማኑ ምንጮች ያውም ለሥርዓቱ ከፍተኛ ቦታ ተመድበው ከሚያገለግሉ ክፍሎች መረጃው እንዳገኘሁት ከሆነ- መቀሌ ከተማ ለብዙ ኣመታት በጫት ሱስ ወጣቶች እንደተበከሉና በእፅ ሱስ ምክንያት የተነሳ ብዙ ትዳር በመፈረስ ላይ እንዳለ ይጠቁማሉ። በቅርቡ የደረሰኝ መረጃ ደግሞ ከተማዋ በሌቦችና በጋንጎች (ወመኔዎች) ቁጥጥር እንደሆነችና ወመኔዎቹ በየቀበሌው የተለያዩ የየራሳቸው ጋንጎች (ዘራፊ ክፍልና መቺ ክፍል/ደብዳቢ) በማሰማራት እንደ ወታደራዊ የዕዝ ሰንሰልት ተሰማርተው ኗሪውና ጎብኚው ክፍል ስጋት ላይ እንደጣሉት ያመለክታል። በትግራይ ርዕሰ ከተማ በመቀሌ ከተማ ውስጥ ባለፉት ስርዓቶች እነኚህ የከተማ ወመኔዎች መኖር ቀርቶ ወፎችና አሞራዎች እንኳ ሲዞሩ ወቅታቸውንና ያየሩን ጠባይ ተሞርክዘው ነበር ተፈጥሮን እያስዋቡ የሚዞሩት። ዛሬ ወያኔ ተግራይ ፍትሕ አሰፈንኩ ሰላም አነገሥኩኝ ባለበት በተመጻደቀበት የውሸት ሥርዓቱ “የመንደር ወመኔዎች”(ጋንጎች)እና ሌቦች ከያኔ የፍትሕ አካላት ጋር በመመሳጠር ድር/ሰንሰለት/ግንኙነት ፈጥረው ከዘረፉት ንብረትና ገንዘብ “ጉቦ”በመሥጠት የተዘረፈውና የተደበደበው ሰላማዊ ኗሪ አቤት ባለ ቁጥር ወረበላዎቹ ለስሙ ተይዘው በሳልስቱ በነፃ እንዲለቀቁ ይደረጋል።
ይህ በታም እገራሚ ሊሆነን አይችልም። ካሁን በፊት በራሴ ዘገባ ከመቶ ዓለቃ አበረ መኮንን በአዲስ አበባ ባንድ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ የምርመራ ክፍል ሃላፊና የጣቢያ አዛዥ በነበሩበት ጊዜ የወያኔ የፖሊስ ኮሚሽነሮች እና ደሕንንት ባለሥልጣናት ጋር እንዲሁም ካንዳንድ ሚኒስቲር ደኤታዎች ጋር በመመሳጠር “በመንግሥት ጠመንጃ/መሳርያና መኪና፤እንዲሁም ደምብ ልብስ፤ሕጋዊ የፀጥታ /ፖሊስ መታወቂያ ሠነዶች” በመያዝ በየነግድ ቤቱ፤ቡና ቤቱ፤ሱቅ እና በመብራት መንገዶች መኪዎችን አስቁመው በመደዳ የተሳፋሪውን ገንዘብና ሰዓት በማስወለቅ እየረፉ ያሰቃዩት እንደነበረና በዚህም ሲያዙ ከላይ አስቸኳይ ማስጠንቀቂአና ማስፈራርያ በስልክ እየተደወለ እንዲፈቱ ይደረግ እንደነበረ የስም ዝርዝራቸዉና ከደርጊቱ ጋር ታሪኩ (የቃለ መጠይቁ ዘገባ)አቅርቤው እንደነበር ይታወሳል።ዛሬም ትግራይ ውስጥ ይሕ ሰንሰለት እንዳዲስ ታድሶ ኗሪዎች በወመኔዎች እየተርበደበዱ እንዳሉ ከሚታመን ምንጭ አረጋግጫለሁ። ዝርዝሩ በቅርቡ የማቀርበው ብሆንም፤ በጣም የሚገርመው የወያኔ አስራር “ፖሊሱ ሌባን ምርመራ ውስጥ ደብድቦ ምስጢሩን እንዲያወጣ እንዲያደርግ አይፈቀድለትም። ወያኔን የሚቃወም የፖለቲካ ሰው ከሆነ ግን ቶርች/ድብደባ ውስጥ በማስገባት ምስጢሮች እንዲወጡ ከውስጥ ለውስጥ ከበላይ በላስልጣኖች ሰንሰለታዊ ምስጢራዊ ግንኙነቶች /ትዕዛዞች ይተላለፋሉ ( በዓረና ትግራይ ደጋፊዎች የተፈጸመው ግድያና ወከባ የታዘብነው ጉዳይ ልብ ይለዋል)። በዚህ ጉዳይ ሌቦችና ወመኔዎች እንደማይደበደቡ ስለሚያውቁ የፈለገውን አድርገው ሲያበቁ ከካዱ ሌላ ቴክኒካዊ ምርመራ አይደረግም፡፤ ሌባው/ወመኔው በቂ ማስረጃ ቢቀርብለትም -ፖሊሱ መብት ስለሌለው ዳኞችና አቃቤ ሕጎቹ ሌባውን/ጋንጎቹን (ወመኔዎቹ) በነፃ እንዲለቀቁ ያደርጋሉ። ሌባ/ጋንግ/ወመኔ ላጭር ጊዜ ታስሮ እንዲፈታ ሲደረግ -የፖለቲካ ተቃዋሚ ሆነ በጥርጣሬ ሲያዝ ግን እንግልቱ ከባድ እና አስቸጋሪ እንደሆነ ታወቋል። የዮሓንስ የአሉላ አገር ባሕሯ ተዘግቶባት በታሪካዊ ጠላቶቿ እጅ ወድቃ ካንዱ ወደብ ወዳንዱ በኪራይ ስትንከዋለል የዮሓንስ ከተማም ወረበላዎች ሲርመሰመሱባት ማየት እጅግ አንጀት ያበግናል፤ያሳዝናል! አይ ወያኔ መጨረሻ ምን አድርገኸን ትሄድ ይሆን? getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com or Google search (Ethiopian Semay)
