Monday, August 27, 2012

ጭንቅላታቸው የተነጠቁ “የስቶክሆልም ሲንድሮም” ሰለባዎች

NEWS

(*1) የመለስ ዜናዊ ሞት የዜናን አዋጅ አስመልክቶ “እንኳን ሞተ፤ ጨካበር”  ማለስሜቷን የገለጸች ኢትዮጵያዊት ወጣት  ከአሜሪካ ለጉብኝት ሄደው  ወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ  እየተናኑ ባሉበት ካፍቴሪያ ውስጥጠርሙስ ጭንቅላቷን በመፈንከትደላት መሆኑን ታማኝ ዘገባ ያመለክታል ።

(*2) ይህ በእንዲህ እንዳለ “ገዛ ተጋሩ” እየተባለ የሚጠራው የወያኔዎች መጮህያ ፓል ቶክ አስተዳዳሪ ነች የምትባል በቅጽል ስም “ሕድያት ትግራይ” ወይንም “ገዛ” በመባል የምትጠራ አክራሪ የወያኔ ጀሌ የመለስ ዜናዊ ሞት አስመልክታ እምባዋን እያፈሰሰች በፓል ቶኳ ክፍል ይሁን ወይንም በሌላ ፓልቶክ ውስጥ ትግርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋ በተደበላለቀ ንግግር ያስተላለፈቺው የተቃዋሚዎች “ጥርሶቻችሁ እንደመስሳቸዋለን”፡ ”ትግራዋይ ኩሉ ሓዊ እዩ ኣትዩዎ” (ትግሬዎች እሳት ሆነናል ተጠንቀቁ”) እኔ ከጀግኖች አካባቢ የተወለድኩ ነኝ፤ ከማን ማህፀን እንደወጣሁ ማወቅ አላባችሁ፤ማን መሰላችሁ ያሳደገኝ የትግራይ ማህፀን እኮ ነው” እናንተ ፈሳሞች፤ሯጮች፤ ከአላጄ (የቀዳማይ ወያኔ ጊዜ ማለቷ ይመስላል)ከዓድዋ፤ አስወጥተን ያሯሯጥናችሁ” *ሁሉም ተቃዋሚ “ደርግ” ብላ በመሰየም”  የዛተችበት ዛቻ ኢትዮጵያውያን አድማጮች የቀዱት ድምፅ በኢመይል እየተላለፈ ነው። ሴትዮዋ ይህን ዛቻ ያስተላለፈቺው ባንድ አፍሪካ አገር ውስጥ  ሆና (ኤንጂኦ ሰራተኛ ሳትሆን አትቀርም) እንዳስተላለፈቺው እራሷ በተቀዳው ደምፅ ተናግራለች። ስለዚህ በማንኛውም ተቃዋሚ ላይ “ሕሊናው እንደሳተ የተለከፈ ውሻ የዱርየነት ባሕሪ” በሚያስፋፉት ላይ የተቀናጀ ትኩረት እና የሕግ ክትትል ማድረግ ያስፈልጋል። (ኢትዮጵያን ሰማይ)     
 
Meles Zenawi designer of Fascist flags in Ethiopia for his Ethiopia dismemberment agenda
TPLF cult musicians fainting with grief in Mekele Tigray
ጭንቅላታቸው የተነጠቁየስቶክሆልም ሲንድሮም”  ሰለባዎች
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ)  getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com


Tigrayan musicians who benefited from the system are devastated by their fascist leader's death. They didn't know that what he designed for them is dangerous future with his fascisitic ethnnic policy.
The above government document showed that every one in the University of Gonder must attend the replica funeral of Meles Zenawi. What a shame! the document was sent to me by cercular emails from a friend.

 ጽሑፌ መጀመር የምፈልገው በሚከተለው በአንድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር  ትንቢታዊ ንግግር ነው። ወቅቱ ሐምሌ በ1984 ዓ.ም ነው። ትንቢታዊ ንግግር ነው። ። ውይይቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በመለስ ዜናዊ ሰብሳቢነት መካካል የተደረገ የምሁራን ሚና ውይይት በኢትዮጵያ ነው። መለስ ዜናዊን አዳራሹ ውስጥ በሰብሳቢነት ተገኝቶ ከምሁራኖቹ ጋር ሲወያይ ወጣቱ ብልህ መምህር  አንዲህ ብሎ ለመለስ ዜናዊ ተንብዮለት ነበር።

“አሁን ወደ ሗላ/ ‘ባክ ቱ ስኩዌር ዋን/ back to square one’ ተመልሼ እንዲህ አይደለም ፤ኤትኒክ ፖለቲክስ ያጠፋናል ፤ምናምን ወደ ሚለው ክርክር አሁን አልሄድም። because it is too late! I think it is too late. ምንድነው ማድረግ የምንችለው አሁን? ኳሷ በእርስዎ ቁጥጥር ስር ናት እና ምንድነው ማድረግ የምንችለው? እኔ የምለው “ቅንነት” ነው የሚያስፈልገው የሚመስለኝ። እርስዎ “ቅን” ብቻ እንዲሆኑ ብቻ ነው የምመኘው።  በቅንነት ብቻ ነው እንዲመሩን የምመኘው አሁን።ምክንያቱም እዚህ አገር ሌላ multiparty system ተቋቁሞ እንዳሉት እርስዎ ገበሬ ውስጥ ገብቶ ፋይዳ ያለው ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ፓርቲ አይኖርም፡ ፤እርስዎ እያሉ! አይኖርም! ምክንያቱም እንዳይኖር “You make sure it doesn’t exit. You have been successful so far, and you will be for the next twenty years, “I give you”!! I am not a fortune teller, but, I can see it. እና አሁን ልል የምችለው እኔ፤ እንደ ትንሽ ትል እዛ እንደሚንከባለል creature ማለት የምችለው፡  ‘የዚች አገር fate በእርስዎ ቁጥጥር ስር ስለሆንን “ቅንነትዎ እንዳይለየዎት” ብቻ ነው፤ ልል የምችለው፤ ተስፋ ላደርግ የምችለው። እኔ በግለሰብ ስለማምን ወይንም theoryየ የተሳሳተ ስለሆነ ወይንም ምናምን….. well, …. ያም ቢሆን አንደገና ልክ እንደርስዎ perception በtime የሚታይ ነው የሚሆው። እንጂ እዚህ ጋ አርስዎ መልስ የሚሰጡኝ ስሕተቴን እንዲነግሩኝ አይደለም። ምን እንደሚሉኝ አሁን አውቃለሁ፡ሳይነግሩኝ፡ ስለዚህ አይንገሩኝ። (ጸጥ ብሎ መምህሩን ሲያዳምጥ የነበረው ተስበሳቢ በድንገተኛ የመምህሩ አስገራሚ ሙግት ሳቅ በሳቅ ሆኖ ይደመጣል)። አመሰግናለሁ።”

ሲል መምህሩ የተነበየውን የመለስ ዜናዊ የሃያ አመት ስልጣን ማብቃያ ትንበያ በጣም አስገራሚ ነው። ከዚህስ ወዲያ ወዴት ነን” የሚለው ሌላ ቀን ስለምንወያይበት በፈጣሪ ውሳኔ ከኢትዮጵያ ጫንቃ በወረደው የመለስ ዜናዊ ሞት ምክንያት የተሰማቸው ሐዘንተኞች ባቀረብኩት ርዕስ ላይ እንቀጥል እና እንወያይ። 

የሰመኑ ዱብ ዕዳ፤ የመለስ ዕረፍት ያስከተለው የድንጉጥ ልቦች ዋይታ፤የልብ ስብራት፤ ሐዘኔታ እና ድንጋጤ የታዘበ አውሮጳ አገር የሚኖር አንድ ወዳጄ ፤ደውሎ “ጌታቸው እንዴት ነው ነገሩ? ይህ ሕዝብ አይተህልኛል? ገርሞኛል፤ እውን አዝኖ ነው? እንዴት ትመለከተዋለህ? አለኝ። ከዚያ በፊት ግን አገር ውስጥ የሚኖር ሌላ ወዳጄ  “መለስ መሞቱን ከሰማሁ ወደ ማታው አካባቢ ምን ወሬ አለ?” ብየ ብለው “ሕዝቡ እዝኗል።” አለኝ። እኔ ደግሞ “ምን ሆኖ? አልኩት “በጠ/ሚ ሞት ምክንያት”፤ አለኝ። እኮ ምን ሆኖ ነው/ የሚደበድበው እንዳያጣ? አልኩት። ነገሩ ገብቶት “ምን ታደርገዋለህ” ብሎኝ ተሰነባበትን።
The stalin of Tigray Melese Zenawi honored like the Stalin od USSR

እኔም አሁን ይሁን ማታ፤ ነገ ይሁን ለከርሞ፤ ሟች ነኝ። እኔ እማ የተጎዳ ሰው ሳይ “እምባ ነው የሚቀድመኝ”” ከደንጉጥም የጃጃ የዋህ ድንጉጥ ልብ ነው ያለኝ።ፍርድ ቤት ዳኛ ሆነህ ፍረድ ብቱልኝ በጨካኞች ላይ ተገቢውን ቅጣት የምፈጽመው አይመስለኝም። ሌላ እንዲፈጽመው ማየት ካልሆነ በቀር። ምላሴ እና ልቤ ግን ለየብቻ ነው፡ የሚያውቁኝ ያውቁኛል። በመለስ ዜናዊ ሕልፈት ግን ሆዴ ድንጋይ ገብቶበታል።ለምን ቢሉ ከፋሺስታዊ የጎሳ አስተዳደር ቀያሺነቱ እና የባሕር በራችንን ለእናቱ ዘመዶች ለኤርትራኖቹ ወግኖ ካለ ድርድር በነፃ ከመሸለም ጀምሮ …….ለመዘገብ ከሚያታክቱ እልፍ ወንጀሎቹ ምክንያት አንጀቴ ከባድ ድንጋይ በመቋጠሩ ሓዘን የሚባል አልዞረብኝም። ይህ ባደርግ ደግሞ አገሬ ኢትዮጵያ ትታዘበኛለች።
The above lady is known by Asli Oromo. It is widely believed that she is been the participant of the massive ethnic cleansing murder while she was OLF guerrilla fighter. She is been sentenced to death by TPLF judges and released after many years in prison. She is still giving interviews after she started to live abroad as a refugee and seems she still is not learning. Her words and threats of tones are very much concerning for many Ethiopian political observers. Insiders say, It is believe that her name is been registered in the Human Rights law sue as one of the participant of the ethnic cleansing. This OLF cult is most respected and loved by similar OLF cults.  
(This Amhara single father who his wife murdered by the OLF thuggish guerrila fighters is a living testimony of Meles Zenawi's policy.  The killing  was perpetrated by TPLF ethnic policy. All These photos showed the crime of ethnic cleansing by TPLF system and OLF thuggish guerrilla fighters who committed murder indiscriminately against Amharic speaking poor farmers and teachers living and intermingled with Oromo population for generation.)
የ1928 ዓ.ም የጎሳ የፋሺስቶች ትምህርት በመላ አገሪቱ እና በወጣቱ ትውልድ ተቀባይነት እንዲኖረው በማስፋፋት ያገሪቱ አንድነት በከባድ ውጥረት ውስጥ ለአደጋ አጋልጦ ለሄደ  የውስጥ ጠላትና የፋሺስቶች መሃንዲስ ማልቀስ፤ማዘን ከበሬታ መስጠት ማለት፤ ተቆጥቶ ከቀሰፈው ፈጣሪ ጋር ግጭት መፍጠር ነውና፤ ወደ ቅድሙ ጓደኛየ ለጠየቀኝ ጥያቄ  ተመሳሳይ ጥያቄ ላላችሁ ሰዎች ለትኖሩ ስለምትችሉ በአኔ እይታ ምን ዓይነት አዛኞች ናቸው በመለስ ሞት መራራ ሃዘን የተሰማቸው? ለሚለው ባጭሩ እንመልከት።



መጠለያ የሌላቸው፤ የተጣለ ቆሻሻ ለቃቅመው የሚመገቡ በልመና የሚኖሩ ጎዳና አዳሪዎች  በእምባ ሲያለቅሱለት ሰምተናቸዋል። መለስ ሲሞት ምን ይዋጥን ሲሉ ያለቀሱ ለማኞች በማን ግፊት እንደሆነ ማወቁ አያስቸግርም። እነኚህ ዓለም የከዳቻቸው ለማኞች፤ በመሰሪ የወያኔ ካድሬዎች ግፊት ለፕሮፓጋንዳ ጠቀሜታ ሲባል እንዲያለቅሱ በዜና ማስተላለፈ ሓጢያት የማይፈራው ወያኔ ከአልቃሹ ብዛት ውስጥም ደምሩልኝ። ይህ ፋሺሰት ቡድን ለማኙንም አልማረውም።አንድ በሉ። ብዙ ሕዝብ ሲያለቅስ መረዳት ያለብን ነገር በወላጆቻችን በትግርኛው ምሳሌ እንደተባለው ምክንያት እንደሆነም ልብ እንበል። እንዲህ ይላል፡ “ዘለላ ወይኒ ብፆታ ክሓማ ምስራአየት ትሓምም” (ጤናማ የነበረቺው የወይን ዘለላ አጠገቧ ያሉት (ወዳጆ) ዘለላዎች ሲታመሙ/ሲጠቁሩ አይታ እሷም ልታመም ብላ ታመመች) የሚባለው ምሳሌ ስንመለከት “የሚያለቅስ ሲያይ አብሮ የሚያለቅስ ለመሰስ ያለቀስ ሁሉ ድምር ውስጥ አስገቡ። በዛው ላይ የታጋዩ ብዛት እና ቤተሰብ ደምሩበት። አንሮም የፋሺሰት ግንጣላ እና ባንዴራ የተለገሰላቸው የጎሳ ፖለቲካ ጀሌዎች እና ቤተሰቦቻቸው ሲደማመር ብዙ ነው። ነገር ግን ይህ የሕዝብ ብዛት ስርዓቱን የወደደ ቢሆንም ፤ የዛው ያህል አስር እጅ እጥፍ ፈግሞ ተቃዋሚ እንደሆነ በምርጫ 97 ሰላማዊ  ሰልፍ ጠቃሚ ትምህርት አስታውሱ። መለስ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰበሰበ ሲባል በማግስቱ የተቃዋሚው ሕዝብ ብዛት ምን ያህል አብዮት አደባባይ እንዳጥለቀለቀው. ትምህርትና መረጃ ይሁናችሁ።

ሰው ሰው በመሆኑ “ብቻ” ከዚህ ዓለም በመለየቱ “አዝነናል” የሚሉን ደጋጎች፤ ልነግራቸው የምፈልገው ነገር፤ ሰው ማለት ተግባሩ እንጂ ምንም ማለት አይደለም። መጥፎ ተግባር ትቶ ለሄደ ሰው ከእንሰሳ ሥጋና ደም የሚለየው መለያ ባሕሪ ስለማይኖረው ቆሻሻ ለተጫነ ስጋ  ግብአተ መሬቱ ሲፈጸም “የሚያዝኑ” ፍጡራን የሚጽፉት የአዘኔታ ጽሑፍ ምን ማለት እንደሆነ አልገባኝም።  ለውሻ፤ ለድመትም እኮ ይለቀሳል። (የብርሃኑ ዘሪሁን መጽሐፍ ተዋናይ የወሎው የድርቅ ሰለባው አያዋ ሙሄ ላሜ ቦራዋ “ላሚቱ” ስትታረድ/ስትሞት አላስችል ብሎት የሃዘኔታው መራራነት ላነበባችሁ ምን እንደነበር ታስታውሳለችሁ) ግን ውሻ ሰው ስለሆነች፤ ድመት ሰው ስለሆነች ሳይሆን ፤አልቃሹ/አዛኙ ከሟቿ ድመት ጋር ቁርኝት ስለበረው ፤በአንዳች ምክንያት (ስትጠፋም ፤ስትሞትም) ቁርኝቱ ሲበጠስ ልቡ አብሮ ይሰበራል/ያዝናል። ግብረ ከይሲ የተጫነ ሰው ሲሞት ግን ሰው ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የሚያዝኑት “የመሞቱ” ጉዳይ ካራሳቸው/ከሐዘንተኞቹ ጋር አንዳች ነገር የሚያቆራኛቸው ነገር ከሌለ አያዝኑም።      
Photo below - The Amhara Children evicted from Gurda Ferda Woreda in Beji Maji South by Meles acknowledgment for being the children of Amhara.

ti is a curse to Ethiopa as well to Tigyans musicians for betraying justice grieving for fascist and divisive leader's death. The breed of new ethno centric musicians are highly destructive for the well being of the future Ethiopia. They need to read more the different between Democracy and ethno fascist federal implemented and currently at work by their fascist ideologue, 
የማያውቁት ሰው ሰው ስለሆነ ብቻ “ሞተ” ሲባል ሲያዝኑ አይታዩም/አይጽፉም። ምክንያቱም በየሰኮንዱ ለሚለይ ሚሊዮን ሟች ሕዝብ ሲያዝኑለት/ሲጽፉለት አይታዩምና  ነው። ሲያዝኑ የሚደመጡት “ሟቹ ሰው ስለሆነ ሳይሆን” ስለሚያውቁት ብቻ ነው። ቁርኝቱ ነው ለሃዘኔታው መገናኛ ክሩ። ዞሮ ዞሮ “ለሰው ሞት አነሰው” ብሏል አይደል ወላጆቻችን። ታዲያ ሰው ሞት ካነሰው ለመለስ ዜናዊ ሞት  ይነሰው? ብለው ለጠየቁ ምን ወቀሳ ያስፈልጋል? ሕያው ስርዓቱ ሳይሞት አንዳንድ ምሁራን ተብየዎች እና ታዋቂ ሰዎች እማ እንግዲህ መለስ ሞቷል  ‘ሙት አትውቀሱ” ወይንም “የወቀሳ ጊዜ ወቅቱ አሁን አይደለም ይሉናል። አመጉሱት ማለቱ ያፈሩ ይመስላል እንጂ በተዘዋዋሪ ልናሞግሰው እየፈለጉ ይመስለኛል። ያውም አሁንም ጋዜጠኞች እያሳደደ እያሰረ ያለው የፋሺስት መንጋ ስልጣን ላይ እያለ እኰ ነው ወቅቱ አሁን አይደለም የሚሉን።
 የጎሳ ፖለቲካ ለተከታተላችሁ ሁሉ እንደምታውቁት ወያኔዎች ለሁለት ሲሰነጠቁ አብዛኛው የትግራይ ተወላጅ ፡ለማን ጅብ ጥላችሁን ልትሄዱ ነው! መሬት ተደረመሰብን” እባካችሁ ለጣለት ሰጥታችሁን አትሽሹ፡ እግዚኦ ፤መሬት ጨለመብን፡ እያሉ ሲጮሁ ሁለቱም ቡድኖች የተደናገጠትን የትግራይ ተወላጅ ለማረጋጋት እና ወደ እየ እራሳቸው ጎራ ከማስኰብለል ይጥሩ እንደነበር እና አሁን ሁኔታው ከዚያ ያልተለየ እንደሆነ መረዳት ትችለላችሁ። ጐሰኛ ሠራዊት መሪው ሲነጠልበት መሬት ይጨልምበታል። እነኚህ  የRepressive Admitance syndrom በተለከፉ የሕሊና ሙርኞች በሌላ የምርምር ክፍል አስቀምጠን እስቲ የሰፊው ሕዝብ ሐዘን ከልብ ይሁን ወይንም ካንዳች ነገር በተገናኘ ሲንድሮም (ልክፍት) ምክንያት የምናየው ልቅሶ እና ሐዘን ከምን የመነጨ እንደሆነ ለመገመት እንዲያስችለን አንዳንድ ታዋቂ ሰዎች የተሰማቸው ሐዘን ለምን ለመግለጽ እንደፈለጉ አንመለክት። የታዋቁ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች የሚባሉ እነ ስየ አብርሃ፤ ብርቱካን መዲቅሳ፤ ከምሁራን ደግሞ ዶ/ር ገላውዴዎስ አርአያ፤ ከጋዜጠኞች ደግሞ እነ አማረ ዓለማዮሁ ፤ከዘፋኞች ደግሞ እነ ሰለሞን ተካልኝ፤ ቢንያም ከበደ…….ወዘተ ወዘተ….. የመሳሰሉት አንደ ናሙና ብንመለከት፤ በመለስ ዜናዊ ሞት ተጠይቀውም ሳይጠየቁም የተሰማቸው ሞት ሲገልጹ የሃዘናቸው አገላለጽ ደረጃ እና መጠን ይኑረው እንጂ፡  “ሁሉም” “የመረረ ሃዘን” እንደተሰማቸው ገልጸዋል”። ሰለሞን እና የሪፖርተሩ አማረን ሳንጨምር የተቀሩት ጥቂቶቹ ለሃዘኔታቸው ምክንያት “ጠ/ሚትሩ ሰው በመሆናቸው” ምክንያት” የተሰማኝ ሃዘን ብርቱ ነው።ሲሉ ተደምጠዋል። እውን መለስ ሰው በመሆኑ ብቻ ነው “ከልብ የመረረ ሐዘን የተሰማቸው”

እስኪ በመርህ ደረጃ እምባ በማቅረር ሐዘናቸውን በመግለጽ የመለስ ዜናዊን መርህ መከተል እንዳለባቸው እና የመለስ መሞት ለጠላት ክፍት ሆነው ለድክመት እንዳይጋለጡ እና እንዳይበታተኑ ስልጣን ላይ ላለው ቀሪው  በሚያዘጋጁት ሚዲያ በኩል “ለፋሺስቶች መንጋ” ጥብቅ ተማጽኖ ካስተላለፉት ከአማረ አለማዮህ ከሰለሞን ተካልኝ እና ቢኒያም ከበደ ጋር የሚከተሉት ሁለት ታዋቂ ሰዎች ማለትም ከእነ ስየ እና ብርቱካን አንድ የሚያደርጋቸው “ሲንድረም” (ልክፍት) ካለ በመረጃ እንመርምር። በእኔ ግምገማ “ስቶክሆልም ሲንድሮም/ (የሕሊና ውዥምብር ሰለባ) ተብሎ በሚታወቀው ያስተሳሰብ ውዥምብር ከተቃዋሚውም ሆነ ከስርዓቱ ደጋፊዎች በኩል በዓንድ  በተመሳሳይ ልክፍት የተለከፉ መሆናቸውን በመለስ ዜናዊ መርዶ ለምን ድንጋጤ ወይንም ሐዘን እንደተሰማቸው እንመልከት። እንኚህ ታዋቂ ኢትዮጵያዊያን ግለሰዎች  በምሳሌ ስንወስዳቸው በሚሊዮን የሚቆጠር የመለስ ሐዘንተኞች ከነዚህ የተለየ እንዳልሆነ ለመረዳት መረጃዎችን በእነዚህ ሰዎች ላይ እንመለክት።

በሪፖርቱ አዘጋጅ  በአማረ አለማዮህ የስቶክሆልም ሲንድረም ልክፍት መረጃ ልጀምር። የኢትዮጵያን ፈረስት ዌብ ሳይት ቢኒያም ከበደም እራሱ ከአማረ ጋር ያደረገው ውይት ስለ መለስ ዜናዊ ስርዓት እንዴት እንደወገዙት አብረን እንመልከት እና ዛሬ ደግሞ ሲንድረሙ አንዴት የሕሊና ድኩማን አድርጎ ለስርዓቱ መሃንዲስ ሞት ሃዘኔታቸው እንዲገልጹ እንዳስገደዳቸወ እናያለን። አማረ አለማዮህ የወያኔ ታጋይ የነበረ ፤እውቅ ጋዜጠኛ እና የወያኔ የፖለቲካ፤የሕዝብ ግንኙነት እና ወዘተ.. ወዘተ… አገልጋይ የነበረ ነባር ታጋይ ነው። አማረ ብዙ አመት በረሃ ውስጥ በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ እስር ቤት ገብቶ ብዙ ስቃይ እንዳየ አንዳንድ ማሕደሮች ተመልክቻለሁ። የቅርብ ዘመዱም ስለስቃዩ ሲናገርም ሰምቻለሁ። አገር ውስጥ የሚገኝ የገዛ ወንድሙ ለምን ወያኔን እንደሚደግፍ አማረን እንደሚሰድበው ሰዎች ይናገራሉ። ከብዙ እስራት ጊዜ መለስ ዜናዊ የወያኔ ምሁራን እሰር ይብቃችሁ ብሎ “ ባለማስተዋላችን በመታሰራችሁ ከፍተኛ ሀዘን እና ይቅርታ እንጠይቃችሗለን፤እንግዲህ በመቻቻል አዲስ ጎዳና አብረን እንቀጓዝ” ብሎ መለስ ሲፈታቸው፤ አማረ አብሮ እንደተፈታ መረጃዎች አሉ።

ወያኔ በ1983 ግንቦት ወር አዲስ አበባ ተቆጣጥሮ መንግስት ሲሆን፤ አማረ አለማዮህ ከአሳሪው ከመለስ ዜናዊ ጋር እሙን ጋዜጠኛ ሆኖ በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ፤ በደ/ር መኮነን ቢሻው (የቀድሞው ዩኒቨርሲቲ እውቅ ተማሪዎች መሪ) እና በመለስ ዜናዊ መካከል የክብ ጠረጴዛ የወዳጅነት አግባቢ ውይይት መድረክ አወያይ ሆኖ ውይቱን በመምራት የመለስ የዜና አውታር ታማኝ ሰው ሆኖ ያገለገለ ነው።እንደምታውቁትም ከዚያ ወጥቶ እንደገና የሪፖርተር መጽሔት በማቋቋም  ለፍትሕ የቆምኩ “ጋዜጠኛ” ነኝ ይበል እንጂ የመለስ አፈቀላጤ ሆኖ ከመጀመሪያ ጀምሮ ጋዜጠኞችን ተቃዋሚውን ሲዘልፍ ሲያንኳስስ መለስን ሲያወድስ እንደነበረ የሚታወቅ ነው።

የመለስ ዲሞክራሲ እና ፍትሃዊነት ሲሰብክ በነበረበት አንደበት በድንገት በዳሸን የቢራ  ፋብሪካ ሾፌር በታጁሮች/ሃብታሞች ትዕዛዝ ከአዲስ አበባ ወደ ጐንደር እጁ በካቴን ታስሮ የዜግነትና የሰብዕናው መብት ተገፍፎ  በፖሊስ ሳይሆን በሲቪል ሾፌር አሳሪና ጠባቂነት ታስሮ የደረሰበት የመብት ረገጣ ካንደበቱ እንዲህ ሲል የገለጸው የስድስት ቀን የጎንደር እስራቱ ልጥቀስ እና ወደ ስቶክሆልም ሲንድሮሙ ጉዳይ እገባለሁ።

ቢኒያም ከበደ (ኢትዮጵያን ፈረስት)“ -ጥያቄ

አቶ አማረ እስቲ በዚህ በገጠምህ አሳዛኝ ጉዳይ ጋር አስመልክቶ አንደ ጋዜጠኛ ሳይሆን እንደ ዜጋ ምን እንደተሰማህ ግለጽልን?

አማረ አለማዮህ፦ 
በእውነቱ በጣም ነው “ወሪ” እንድሆን ያደረገኝ (ያሳሰበኝ) ። ካሁን በሗላ …… (?) የሰው ስም ወይንም የድርጅት ስም ማጥፋት  ፍትሐብሔር አንጂ ወንጀል አይደለም ብሎ ፓርላማ ሕግ ካወጣ በሗላ ግለሰቦች ስማችን ጠፍቷል ብለው በወንጀል ተከሰሃል ተብለህ ታስረህ ስትሄድ ለጋዜጠኛ ወይም ለፕሬስ ሰው የሚመጣ ወሪ (የሚያሳስብ ጉዳይ ማለቱ ነው) ሳይሆን፤ አጠቃላይ “ሩል ኦፍ ሎው፤ “ክራሽ” የሚያደርግ ነው። መጥሪያ ሳይደርስህ የተከሰስክበት ምክንያት ሳይነገርህ እና ሳታወቅ ወደ 750 ኪ.ሜ  ርቀት ወደ አለው ከሳሽህ ተወስደህ ስትታሰር “ያገሪቱ ሩል ኦፈ ሎው” (የሃገሪቱ ሕግ እና ስርዓት አተገባበር) ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ እርምጃ ነው።  “እራሱ ከስሶ፤ በራሱ ፖሊስ ለሆቴል ወጪ አበል እየከፈለ ከ750 ኪ.ሜትር ርቀት የሚኖር ድርጅት/ፖሊስ እየበረረ መጥቶ ጠያቂ የሌለው አስሮ እና ጠልፎ ሲወስድህ፤ አማረ እንደዚህ ሆነ ወይንም ፕረስ/ጋዜጠኛ እንደዚህ ሆነ የምትለው ሳይሆን “ኢንስቱሽን ኦፍ ሎው፤ ፍትሕ ባጠቃላይ ባገራችን ምን ይመስላል? ብልህ እንድትጠይቅ እና ባጠቃላይ ዜጎች ጥቃት እንዳይደርስባቸው የሚከላከልላለቸው ሕገመንግሥት አለ ወይ? ብየ ካለፈው ለየት ባለ ሁኔታ ራሴን እንድጠይቅና ቆም ብየ እንዳስብ በጣም ፤ በጣም “ወሪ”  እንድሆን አድርጎኛል።

ቢኒያም ከበደ (ጠያቂ)፡
 በእውነቱ አቶ አማረ ጭንቀቱ ባንተ ብቻ አይደለም (እኔኑም አሳስቦኛል) ። ውጭ ጋር ሆነን ስንኖር፤ ያንተ ሪፖርትር “ውጭ ዲያስፓራ የምትኖሩ ዜጎች ስለ አገር ብላችሁ አገራችሁ ግቡ እና እንቬስት አድርጉ፤ ኢትዮጵያን “ብራንድ” እድርጛት፤ አዲሱ ሚሊየነም ነው፤ ( ሰርዓቱን እናጠናከር) ብዙ ብዙ ብለን ነበር፡ ስለ አውነት ነው የምለው። እውነት ያ ሳስበው በቅርቡ   በእውነቱ አቶ አማረ ያንተን የመታሰር ዜና በቅርቡ ከተከታተልኩ በሗላ፤እንዴት ነው ወደ እዚህ አገር ነው ወይ የምገባው ብየ እራሴን ጠየቅኩኝ። እውነት ይሄ ስለ ጋዜጠኛነት አይደለም የምለው፡ሳስበው ስለ እራሴ ምንድነው ጋራንቲዬ (ዋስትናዬ ምንድ ነው)? እኔ ኮንስትትሺኑ (ሕገ መንግስቱ) ነው ጋራንቲየ ተከላካየ) ብየ አምናለሁ። ምንም ላድርግ ምንም፤ መጥፎም ላድርግ በጐ  “ኮነንስትትሺን” (ሕገ መንገስት) ይፍረድብኝ ነው የምለው”” ነገር ግን መጥርያ ሳይሰጥህ፤የሆነ ሰው ጠልፈፍ አምጣልኝ ብሎ የሚወስድህ ከሆነ፤ የዜጎች ዋስትና (በዚህ ስርዓት ውስጥ) የቱ ላይ ነው? በማለት ራሴን እንድጠይቅ አድርጐኛል” (ቢኒያም ከበደ)

ሲሉ ሁለቱም በስርዓቱ ስርዓተ አልባነት ተስማምተዋል። የወያኔ ታጋዩ አማረ አለማዮህ ከአዲስ አበባ መስሪያቤቱ በአንድ ፋብሪካ  ተቀጣሪ ሲቪል ሾፌር (ልብ በሉ ፖሊስ አይደለም) ተጠልፎ በካቴና የፍጢኝ ታስሮ “አቤት” ቢልም የአዲስ አበባ ፌደራል ፖሊሶች አናድንህም ብለውት፤ አማረ  6 ቀን  የደረሰበት የጎንደር አሰቃቂ  እስራት እና የመብት ጥሰቱ ስርዓቱን ሲያወግዙት አንብባችሗል። አማረ በረሃ ላይ ለብዙ አመት ታስሯል። በሗላም ጭንቅላቱ ላይ እንደማይተርፍ ሆኖ ተደብድቧል።ከላይ ባየነው ሁኔታም እንዲሁ በተራ ሾፌር በካቴና የፍጢኝ ታስሮ ወደ ጎንድር ተወስዶ ታስሯል። ያ ሁሉ ውርደት ግን “ስርዓቱ ባለማደጉ እንጂ ለራሰችን ደህንነት አሳቢ ነው፤ አሁንም ሊከላከልን ይችላል…..” በሚል ሲንድረም/የሕሊና ውዥምብር በመለከፋቸው፤ዛሬም  ሙሉ በሙሉ  መለስ ከሞተ በሗላ በሰርዓቱ ላይ ያላቸው እምነት እና ለመለስ ያለላቸው ሃዘኔታ በይፋ ገልጸዋል።  በእንዲህ ያለ ሁኔታ ስብእናው ሲገፈፍ አሁንም እዛው ለመጠለል እና ለመንበርከክ ያስገደደው  ሲንድረም/ልክፍት ለምን እንዲህ እንዲያስቡ ሕሊናቸው እንደሚነግራቸው ወደ ሗላ በሳይንሳዊ ትንተና እንመለከተዋለን።

ለምሰሌ በዚህ ሰሞን የሪፖርተር አምዱ እንዲህ ሲል ስርዐቱ ተማጽኗል። ስለ ተቃዋሚዎች እንዲህ ይላል
 let them be loyal oppositions”
መለስ ትቷቸው ለሄደው አሽከሮቹ ደግሞ  እንዲህ ሲል ተማጽኗል። 
The death of Prime Minister Meles, however, does not only evoke sorrow. It also begs the question “What next?” and already has. This topic is the import of this editorial………. we also desire the ruling party to be strong. The four member parties of the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) must do the country proud by proving in deed to the people of Ethiopia that they will not break up, squabble or trip up each other in when they are confronted by seemingly insurmountable challenges. The Front’s enemies are maintaining that its members are feuding. They should dispel this by demonstrating to the public that they are united and committed to stand by it. The sooner the better!”

በማለት አማረ አለማዮህ “ስርዐቱ የዜጎች መብት “ክራሽ” (የሚድጥ) በሚያደርጉ ሰዎች የሚመራ ነው” ባለበት አንደበቱ  ዛሬ ተመልሶ ጠላት እንዳይገባባችሁ፣ ነፋስ እንዳታስገ፣ በማለት አደራውን ሲገልጽ።  ቢኒያም ከበደም “የዜጋ መብት ወደ ሚረገጥበት እንደዚህ ዓይነቱ አገር ነው ወይ የምገባው፤ ኢንቨስት የማደርገው?” ብሎ ለከሰሰው ስርዓት ተመልሶ ፣ስለ መለስ ዜናዊ መሞትና እና ስርዓቱ ያለው ጥልቅ የሃዘን ስሜት ገልጿል።


the leader whose heart splitted for two flags the future Tigray Tigringi flag he designed  and Ethiopian flag.

የወያኔ ጦር መሪ የነበረ፤ የስየ አብርሃ ሲንድሮም፡-
የስየ አብርሃ ሕግ ተብሎ በሚታወቀው የመለስ ዜናዊ የብቀላ ሕግ የተጠቃ 6 ዓመት ከባድ እስር ያሳለፈ ከፍተኛ የወያኔ የጦር መሪ እና የድርጅቱ አማራር አባል የነበረ የመለስ ዜናዊ የቅርብ ጓደኛ ነው።መለስ በመሞቱ የተሰማው ሃዘን ሲገልጽ “ክው” ብሎ ደንዝዞ እንደቀረ፤ የተሰማው የሃዘን ስሜት በትግርኛም ባማርኛም በእንግሊዝኛ ሚዲያዎች ተመሳሳይ ስሜቱን ገልጿል።  

ዳኛ ብርቱካን መዲቅሳ፡_የፖለቲካ ልምድ ሳታካብት ባጭር ወራት የፓርቲ አባል ሆና ታዋቂነትን ያተረፈች በአንዳርጋቸው ጽጌ (በትናቸው ጽጌ በመባል የታወቀው የዛሬው የግንቦት 7 አመራር) እና “አምታታው በከተማ” ተብሎ በቅጽል የሚታወቀው ብርሃኑ ነጋ አንዲሁም በመሳሰሉ ተንኮለኞች ተገፋፍታ ለቅንጅት መሰነጣጠቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገች፤ የተንኮለኞች ሰለባ ናት። በመለስ ዜናዊ የግል ቂም ያለ ሕግ ለእስር ተዳርጋ ብዙ መከራዋን ያየች ፤ በመጨረሻ አገር ጥላ በመውጣት በፈረንጆቹ ወጪ በጎ አድራጊነት አንዳንዶቹ “የቀረጻ ትምህርት”/ስኮላር…ወዘተ… ይሉታል  አሜሪካ አገር በመከታተል ላይ ያለች “ተማሪ ብርቱካን ”  በተደጋጋሚ የመለስ ዜናዊ ሰለባ ብትሆንም፤ በመለስ ዜናዊ ሞት ደጋግማ (ብዙ ጌዜ) ሃዘኗን መግለጿን (በማጠቃለያው ላይ በጥሩ ድምዳሜ ብትቋጨውም ቅሉ)  ስንመለክት፤ ሁሉም የተጠቀሱት የስርዓቱ ሰለባዎች (ቪክቲም) ስብእናቸው እንዲያ ለገፈፋቸውና ላዋረዳቸው ግለሰብ ሞት የመረረ ሃዘን እንደተሰማቸው ሳይደብቁ መናገራቸው “ስልጡን ፖለቲካ” የሚሉት ወይንም “ጨዋ አስተሳሰብ” የሚባሉ አጣፋጭ ሐረጎች ተመርኩዘው ሳይሆን ፈረንጆች “ሄት ኤንድ ላቭ/ጥላቻና ፍቅር” ወይንም “ስቶክሆልም ሲንድሮም” በሚባለው የሕሊና ውዥምብር የፈጠረው አስተሳሰብ እና ሃዘኔታ እንደሆነ እና ብዙዉን አልቃሽ እና ሃዘኔታ አቅራቢ በዛ ልክፍት የመለከፋቸው መረጃ ነው።
ተገዶ ሄዶም ለጠላቱ/ለሟቹ እምባ የሚያፈስ አለ። በስርዓቱ የተጠቀመ ጥቅመኛም ከልቡ የሚያለቅስ አለ። ከአርቆ ነገሮችን የማገናዘብ እና ያገር ሁኔታ ከማገናዘብ የማሰብ ችሎታ ዝቅተኛ ንቃት የተነሳ መሪው ጤነኛ እንደነበር አምኖ የሚያዝን ገራገር አልቃሽ እና አዛኝም አለ። ባህሪያዊ ነው። ነገር ግን ኤክሰፕሽን (በልዩ መነፅር) የሚገመገሙ ሰዎችን ለሃዘኔታቸው ምክንያት ስንመለከት፡  ይህ ሁሉ ከምን የተነሳ ይሆን ብለን ብንጠይቅ ለምሳሌ ብርቱካን ከመታሰሯ በፊት ከወያኔ ስርዓት ጋር “ላንፋታ ተጋብተናል” ብላ ቃል ኪዳን ገብታ አዲስ ትግል ጀምሬአለሁ ብላ እንደነበር ታስታውሳላችሁ። ቃሉ ግን በወያኔ ስርዓት ሞገደኛነት ተሰብሮ ከስርዓቱ ጋር ተፋትታ ‘ለፍች” ተዳርጋ “እሰር ገባች”። ልቧ ተሰበረ።  “የላንፋታ ተጋብተናል” ጋብቻ የሰበረው የስርዓቱ መሪ መለስ ዜናዊ  ድንገት በሞት ሲለይ ሃዘኗ ጥልቅ ሆነ። ምንም በቂም በቀል ቢያስራት እና ቢያሰቃያትም፤ ሕሊናዋ በሰቶክሆልም ሲንድሮም መዓበል ስለዋለለ ከውስጥ የተሰማት ሃዘን ፈንቅሎ ሳትደብቅ “በጨዋነት” አገላለጽ ገልጻዋለች። ስየ አብራሀም ሆነ ሌሎቹ የስርዓቱ ሰለባዎች ተመሳሳይ ስሜት እንዴት ድንገት በሃዘን አንዲዋጡ ተገደዱ? ያውም አንዳንዶቹ ከሐዘኔታቸው አልፈው ለስርዐቱ ጥብቅና ወይንም ላሰቃያቸው ሰው እና ስርዓት ወይንም በጦርነት ተማርከው የሗላ ሗላ ከማረካቸው ጦር ጋር ሆነው  ሕይታቸው በመስጠት ጥብቅና እስከመቆም ያደረሳቸው ውጥረት ምን ይሆን ለሚለው ጥያቄ መልሱ ከሕክምና/ኣእምሮ ሊቃውንት ትንተና ልውሰዳችሁ እና ልሰናበታችሁ። ይህ ለኛ ጥሩ ምንጭ መሆኑን አምናለሁ እና በጥሞና አንብቡት።

Stockholm syndrome, or capture-bonding, is a psychological phenomenon in which hostages express empathy and have positive feelings towards their captors, sometimes to the point of defending them. These feelings are generally considered irrational in light of the danger or risk endured by the victims, who essentially mistake a lack of abuse from their captors for an act of kindness. The FBI’s Hostage Barricade Database System shows that roughly 27% of victims show evidence of Stockholm Syndrome.

Stockholm syndrome can be seen as a form of traumatic bonding, which does not necessarily require a hostage scenario, but which describes "strong emotional ties that develop between two persons where one person intermittently harasses,
beats, threatens, abuses, or intimidates the other."

Battered-wife syndrome is an example of activating the capture-bonding psychological mechanism, as are military basic training, fraternity bonding by hazing, and sex practices such as sadism/masochism or bondage/discipline.In clinical practice, some of the most surprised and shocked individuals are those who have been involved in controlling and abusive relationships. When the relationship ends, they offer comments such as “I know what he’s done to me, but I still love him”, “I don’t know why, but I want him back”, or “I know it sounds crazy, but I miss her”. Recently I’ve heard “This doesn’t make sense. He’s got a new girlfriend and he’s abusing her too…but I’m jealous!” Friends and relatives are even more amazed and shocked when they hear these comments or witness their loved one returning to an abusive relationship. While the situation doesn’t make sense from a social standpoint, does it make sense from a psychological viewpoint? The answer is — Yes!
 
On August 23rd, 1973 two machine-gun carrying criminals entered a bank in Stockholm, Sweden. Blasting their guns, one prison escapee named Jan-Erik Olsson announced to the terrified bank employees “The party has just begun!” The two bank robbers held four hostages, three women and one man, for the next 131 hours. The hostages were strapped with dynamite and held in a bank vault until finally rescued on August 28th.

 
After their rescue, the hostages exhibited a shocking attitude considering they were threatened, abused, and feared for their lives for over five days. In their media interviews, it was clear that they supported their captors and actually feared law enforcement personnel who came to their rescue. The hostages had begun to feel the captors were actually protecting them from the police. One woman later became engaged to one of the criminals and another developed a legal defense fund to aid in their criminal defense fees. Clearly, the hostages had “bonded” emotionally with their captors.

While the psychological condition in hostage situations became known as “Stockholm Syndrome” due to the publicity, the emotional “bonding” with captors was a familiar story in psychology. It had been recognized many years before and was found in studies of other hostage, prisoner, or abusive situations such as:
  • Abused Children
  • Battered/Abused Women
  • Prisoners of War
  • Cult Members
  • Incest Victims
  • Criminal Hostage Situations
  • Concentration Camp Prisoners
  • Controlling/Intimidating Relationships
  • In the final analysis, emotionally bonding with an abuser is actually a strategy for survival for victims of abuse and intimidation. The “Stockholm Syndrome” reaction in hostage and/or abuse situations is so well recognized at this time that police hostage negotiators no longer view it as unusual. In fact, it is often encouraged in crime situations as it improves the chances for survival of the hostages. On the down side, it also assures that the hostages experiencing “Stockholm Syndrome” will not be very cooperative during rescue or criminal prosecution. Local law enforcement personnel have long recognized this syndrome with battered women who fail to press charges, bail their battering husband/boyfriend out of jail, and even physically attack police officers when they arrive to rescue them from a violent assault.
በጣም ይገርማል። እውን ይኼ ሕዝብ ከልቡ ነው ለመለስ ያለቀሰለት ብለህ ስልክ ደውለህ ለጠየቅከኝ ወዳጄ መልሱ ከዚህ እንዳገኘኸው ተስፋ አደርጋለሁ።  ጭንቅላታቸው የተነጠቁ የስቶክሆልም ሲንድሮም ሰለባዎች ይህን ይመስላ። ለመሆኑ ወንድሞቼ/እህቶቼ ይህ ሁሉ ካን ዛሃ የተሰራ ከሰል የሚመስል ጥቁር የሃዘን ሸሚዝ እና ቀሚስ/ደምብልብስ ከመቸ ተሰፋ እና ተሰራጨ? የሄ ቻይና የሚሉት አገር ሰንት ገንዘብ ሰርቶብን ይሆን? ወይ ጉድ!ጉዳችን አያልቅም።  አመሰግናለሁ።

ጌታቸው ረዳ (አትዮጵያን ሰማይ የህዋ ሰላዳ አዘጋጅ) getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com vistit my new facebook. It is posted to the right of this weblog all the way to the bottom.